805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
#በክርስቶስ_በሰማያዊ_ስፍራ_ተቀምጠናል
“በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።”— ኤፌሶን 2፥6-7
❇️ ይህ ክፍል ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ ሐጢአተኛው ሰው ሲናገር ቆይቶ ወደ እግዚአብሔር ዘወር የሚልበት ክፍል ነው። እግዚአብሔር ከኀጢአት መዘዝ ሰዎች ለመታደግ ያደረገውን ስራ የገለጠበት ነው።
“ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥— ኤፌሶን 2፥5
❇️ በኃጢአታችን ሙታን በነበርን ግዜ ሕይወትን ሰጠን። እግዚአብሔር ይህንን መንፈሳዊ ትንሳኤ ያከናወነው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው። መንፈሳዊ ትንሳኤያችን ከክርስቶስ ጋር አንድ ስለሚያደርገን የላቀ ስፍራ የሚሰጠው ነው። #እግዚአብሔር_ከክርስቶስ_ጋር_ሕይወትን_ሰጠን። የአካሉ ክፍሎች እንደመሆናችን ከእርሱ ጋር ተሳሰርን።
ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
❇️ ግልጽ ባለ ሁኔታ #የተወደድን ፣ #ሕይወት_የተሰጠን፣ #እና_ከፍ_ከፍ_የተደረግን ነን። ነገር ግን ልክ እኛ እንዳመጣነው አድርገን በዚህ ማንነታችን እንዳንመካ እግዚአብሔር ብርቱ ማስጠንቀቂያ በጳውሎስ በኩል ይነግረናል። #የእግዚአብሔር_ስጦታ_ነው_እንጂ_ከእናንተ_አይደለም ማንም እንዳይመካ ከስራ አይደለም።
#የክርስቶስ_ምስክሮች_ነን
“ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ #ኃይልን_ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ #ምስክሮቼ_ትሆናላችሁ አለ።”
— ሐዋርያት 1፥8
✅የመንፈስ ቅዱስ መምጣት ከኃይልና ከምስክርነት ጋር ተያይዞ ቀርቧል። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ስለሚቀበሉት ኃይል ሲነግራቸው ከምድራዊ እና ከፖለቲካው ስልጣን ጋር አያይዞ ሳይሆን የትኩረት አቅጣጫው #ስልጣኑ_የወንጌል_ምስክረነት_ነበር።
“ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው።”— ሐዋርያት 1፥3
✅ኃይል ለመቀበል ዝግጅነትን አሳያቸው። አስተማራቸው። በዚህ ምክንያት በጌታ ላይ ባላቸው እምነት #የማያመነቱ ፣ #ጀብደኞች፣ #ቆራጥ አና #ድል_አድራጊዎች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የእርሱ አብሮነት ማመናቸው #ስብከታቸውን_ድንቅ_ኃይል_አላብሶታል።
በኃይል ሰለመጠመቅ ነገራቸው።“ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ #በመንፈስ_ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አለ።”
— ሐዋርያት 1፥5
ይህ የእግዚአብሔር ተስፍ ቀድሞውኑ የተሰጠ ነው። (ኢሳ 44:5 ኢዩ 2:28) ክርስቶስም ቃል ገብቶላቸው ነበር።
✅ የኀይሉ ምንጭ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ይነግራቸዋል በተለይ ቁጥር 8 ኃይልን መቀበል ከነውጤቱ አስቀምጦላቸዋል። #የእርሱ_ምስክሮች_መሆን_እንዴት_እንደሚቻል እና የተቀበልነውን ለሌላ እንዴት መመስከር እንደሚቻል ለእኛም አረጋገጠልን።
✅ከመንፈስ ቅዱስ የተቀበልነው ኃይል #ተዓምራዊ_ኃይል፣ #ድንቅ_ችሎታ፣ #የተትረፈረፈ_ጉልበት፣ #ኃይለኛ_አስደናቂ ብቃት ነው። የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ታላቅ ስራ የሚሰራ ሁሉን የሚችል ነው። ያለዚህ ኃይል ምስክር መሆን አይቻልም። በዚህ ኃይል አማካኝነት #ያለ_ፍርሀት_በድፍረት_መመስከር_እንችላለን።
🙏#የአዲስ_ኪዳን_ቤተመቅደስ
✅ ክርስቲያኖች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስምና በአምላካችን መንፈስ #ጸድቀው ፣ #ተቀድሰው እና ቅዱሳን ለመሆን ተጠርተው የመንፈሰ ቅዱስ #ቤተመቅደስ ሆነዋል።
“ከእናንተም አንዳንዶቹ እንደ እነዚህ ነበራችሁ፤ ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ #ታጥባችኋል፥ #ተቀድሳችኋል፥ #ጸድቃችኋል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥11
✅መንፈስ ቅዱስ በመነፈሳዊ ለውጥ አማካኝነት ውስጣችንን ያድሳል በጎነት፣ #ጽድቅና እውነት በሆነው ሁሉ አማካይነት እነደ ብርሀን ልጆች እንኖር ዘንድ ያግዘናል።
“የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤”
— ኤፌሶን 5፥9-10
#ፍሬ_ልናፈራ_የተሾምን_ነን
“እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና #ፍሬ_ልታፈሩ_ፍሬአችሁም_ሊኖር_ሾምኋችሁ።”
— ዮሐንስ 15፥16
✅ በሐዋርያው ዮሐንስ መልዕክት ውስጥ እኔ መረጥኳችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም የሚለው ሀሳብ አንድ የሚነግረን ሀሳብ አለው። የተመረጥነው በማን እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያስቀምጥልናል። አስገራሚው ደግሞ ባልመረጥነው መመረጣችን ነው። በአይሁድ ልማድ ለራስ መምህርን መምረጥ የተለመደ ጉዳይ ነው። ኢየሱስ ግን በተገላቢጦሽ ደቀ መዛሙርትን የመረጣቸው እርሱ ራሱ ነው። ኢየሱስ መርጠነው ሳይሆነ መርጦን ነው የተከተልነው። ጥሪው ለሁሉ ቀርቧል። #ለመከተል_እና_ላለመከተል_ምርጫው_በእኛ_ላይ_ነው። የወይን ግንዱ ላይ የተጣበቅነው በእርሱ ምርጫ ነው። #በግንዱ_ላይ_መቆየት_ግን_በኛ_ፈቃደኝነት_ላይ_የተመሰረተ_ነው። (ዮሐ 15:6)
✅ የተመረጥነው የተሾምነው #ፍሬ_ለማፍራት መሆኑ መዘንጋት የለበትም። የትኩረት አቅጣጫችን ሹመት ላይ ሳይቀር #ፍሬ_ማፍራት ላይ መሆን አለበት። ሹመት ያለ #ፍሬ ጥቅም የለውም።
አዋጅ 🎷🎷🎷
#በኢየሱስ #ተመርጫለው
#ኢየሱስን #እከተላለው
#ፍሬ #በማፍራት #እመላለሳለው !!!
ሰላም ለኢትዮጵያ ❤❤❤
መዝሙር 52
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ፤ ለዓለምና ለዘላለም በእግዚአብሔር ምሕረት ታመንሁ።
⁹ አድርገህልኛልና ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፥ በቅዱሳንህም ዘንድ መልካም ነውና ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ።
#የእውነተኛ_የወይን_ግንድ_ቅርንጫፎች_ነን
“እውነተኛ #የወይን_ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው።”— ዮሐንስ 15፥1
“እኔ #የወይን_ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ #ፍሬ ያፈራል።”
— ዮሐንስ 15፥5
✅ እግዚአብሔር እውነተኛ #የወይን #ግንድ አስፈልጎታል #ወይን የአሁን ግዜ በሚያመላክት ሁኔታ #ኢየሱስ_ክርስቶስን የሚያሳይ ሆኖ ቀርቧል። እውነተኛ #የወይን_ግንድ ኢየሱስ ነው። የእውነተኛው የወይን ግንድ ቅርንጫፎች #እውነተኛ_ክርስቲያኖች ናቸው።
✅ #የወይን_ግንዱ የክርስቲያኖች በረከት ሁሉ ምንጭ ነው። የወይን ግንዱ ኢየሱስ ሲሆን ክርስቲያኖች ደግሞ ቅርንጫፉ ሆነን ከክርስቶስ ጋር #ልዩ_የሆነ_መንፈሳዊ_ህያው_ግንኙነት_አለን።
✅ ክርስቲያን #ከወይኑ_ግንድ በሚቀበለው የማያቋርጥ አቅርቦት (ማዕድ) ላይ የተመሰረተ ሕይወት አለው። ቅርንጫፍ የሕይወት ተቀባይ ብቻ ነው። ካልተቀበለ ሕይወት የለውም ሕይወት ከሌለው ይደርቃል። ስለዚህ በሕይወት ለመቀጠል ከግንዱ ለሚመጣው እንክብካቤ ምቹ ሁኔታ መፍጠር አለብን። ክርስቲያኖች ከእውነተኛው ግንድ እስካልተለየን ድረስ ፍሬ ማፍራታችን ይቀጥላል። ለሕይወታችን የሚያስፈልገንን #የመንፈስ_ፍሬ #ፍቅር፣ #ሰላም፣ #ደስታ.... የምናገኘው ግንዱ ላይ ተጣብቀን ብቻ ነው። ስለዚህ ከጌታ ጋር ያለንን ሕብረት ይበልጥ ልናጠናክር ይገባናል። ገበሬውም በፍሬው ደስ እንዲሰኝ ያደርገዋል። ተቀብሎ ለመስጠት ግንዱ ላይ እንጣበቅ።
✅ ግንዱ ላይ ተጣብቀን መኖር የምንችለው ከቃሉ እና #ከመንፈሱ ጋር ትክክለኛ ሕብረት ሲኖረን ነው። ስለዚህ #ለቃሉ_ክብር እየሰጠን በመንፈስ ቅዱስ ልንመራ ግድ ይለናል።
🎷🎷🎷🎷አዋጅ
#ቃሉን_በቀንም_በለሊት_አሰላስላለው
#ቃሉ_ፈውሴ_ስለሆነ_የሚገባውን_ክብር_አሰጣለው
#መነፈስ_ቅዱስ_አንዲመራኝ_እፈቅዳለሁ
#በመንፈስ_ፍሬ_እገለጣለው
#ለዘላለም_ከግንዱ_ጋር_ተጣብቄ_እኖራለው
#በኢየሱስ_ስም!!!
ሰላም ለኢትዮጵያ ❤️❤️❤️
#የዓለም_ብርሀን_ናችሁ!!!
“እናንተ የዓለም #ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። — ማቴዎስ 5፥14
✅ ክርስቲያኖች የዓለም #ብርሀን ተብለን ተጠርተናል። እግዚአብሔር በትዕዛዝ ከለያቸው ነገሮች መካከል #ብርሀንና ጨለማ ይገኙበታል (ዘፋ 1:4) በብርሀን መልካምነት እግዚአብሔር ደስም ተሰኝቷል። በቀንና በለሊት እንዲሰለጥኑ ስልጣን የተሰጣቸው ሁለቱ ናቸው። ጨለማ የገዛው #ብርሀን ባልነበረበት ወቅት ብቻ ነው። ጨለማ መሰልጠን የሚችለው #የብርሀን አለመኖርን ጠብቆ ነው። ጨለማ ማለት #የብርሀን አለመኖር ነው።
✅ እኛ ክርስቲያኖች የዓለም #ብርሀን ናችሁ ተብለናል። ታዲያ ዛሬ የጨለማ ስራ ይህን ያህል ተገልጦ ሕዝባችንን እስኪጨርስ ድረስ የእኛ #ብርሀን እንዴት መገለጥ አቃተው። “ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና።”— 1ኛ ዮሐንስ 2፥11
ዛሬ ወንድም በወንድሙ ላይ ሲነሳ ክርስቲያኖች የት ገቡ አያስብልም? ክርስትናችንን ልንፈትሽ ይገባል እያንዳንዳችን እውነት የክርስቶስ ተከታዮች ነን? ምልክታችን ምንድን ነው? ቃሉ የሚለው “እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ #ደቀ_መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።”— ዮሐንስ 13፥35
✅ በጨለማ የመኖር ሌላው ትልቁ ክፍት መልካምን ነገር እንኳን ለክፉ ማድረጉ ነው። በተቃራኒው #የብርሀን ጥቅም ክፉን ነገር መልካም የማድረግ አቅም አለው። በጨለማ የሚመላለስ ሰው ሁልግዜ የሚሰናከል ነው።
1ኛ ዮሐንስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ ወንድሙንም የሚወድ #በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም፤
¹¹ ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጨለማ የኀጢአት መንገድ (ኤፌ 5:11) መከራና ጭንቀት (ሮሜ13:12) አላዋቂነት(1ዮሐ 2:8-11) ሞትን (እዮብ 10:21-22) ሲዖልን (ማቴ 22:13) አመላካች ተደርጎ ቀርቧል።
✅ ጨለማ መኖር የሚችለው #ብርሀን ሳይኖር ሲቀር ነው። በሌላ በኩል እኛ እራሳችን ጨለማ እንደነበርን ሁሉ #አሁን_ግን_በክርስቶስ_ብርሀን_ሆነናል (ኤፌ 5:8) ። ይህን #ብርሀን ደግሞ እንድናበራ ኢየሱስ ራሱ በቃሉ ነግሮናል። #ብርሀናችሁ_በሰው_ሁሉ_ፊት_ይብራ። #ብርሀን የክርስቶስ ኢየሱስን ማንነት ወካይ ነው። የተለወጡ ክርስቲያኖች መገለጫም ነው።
“ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤”— ኤፌሶን 5፥8
✅ የብርሀን ቀዳሚ ዓላማው በተገኘበት ቦታ ሁሉ ጨለማን ማባረር እና መግለጥ ነው። #ብርሀን ባለበት ስፍራ ጨለማ በፍጹም አይገኝም እንዲሁ ጨለማ ባለበት ስፍራ ብርሀን አይገኝም። ሁልግዜም በሁለቱ መካከል ስምምነት የለም ሁሌም ጨለማ ይሸሻል ይሸነፋል ። በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ትንሽ #ብርሀን ብትገኝ ለአካባቢው ተስፋን እንደምትሰጥ እኛም ክርስቲያኖች በተገኘንበት ስፍራ ሁሉ በመልካም ስራ ጨለማን ገፈን #ብርሀናችንን ማሳየት ለሌሎች ሕይወት እና ተስፋ ልንሆን ይገባል።
#በብርሀናችን_ጨለማውን_ልንገፍ ተጠርተናል
#ለጨለማ_እድል_ልንሰጠው አይገባም።
#በጨለማው_ላይ_ልንገለጥ_አሰፈላጊዎች ነን።
#በኢየሱስ_ስም_ለሀገራችን_ብርሃን ይሁን!!!
#ኢትዮጵያ_ሰላምሽ_ይብዛ ❤️❤️❤️
#የምድር_ጨው_ነን
“እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።”— ማቴዎስ 5፥13
በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በመጠን ጥቃቅን በአገልግሎታቸው ትላልቅ ስራ የሚሰሩ ነገሮች መካከል ሁለቱ ማለትም ጨውና እርሾ ይገኙበታል። ሁለቱም ትልልቅ አገልግሎት ያላቸው ኃይላት ናቸው። በተጨመሩበት ሁሉ ስራቸውን ሳያከናውኑ አይቀሩም። ስለዚህ እኛም ለዚህ ዓላማ ተጠርተናል።
#ጨው በትንሹ ሶስት ባሀሪያት አሉት። #ጣዕም መስጠት፣ ጥምን መቀስቀስ እና ፣ ከመበስበስ መጠበቅ። ምድር ያለ ክርስቲያኖች ጣዕም አልባ አልጫ ናት። እውነተኛ ክርስቲያኖች በሌሎች ዘንድ #የፅድቅን ጥም የመቀስቀስ አቅም አላቸው። ጳውሎስ እና ሲላስ በወህኒው ጠባቂ ሕይወት ላይ #ፅድቅን እንዲጠማ አድርገው እርሱና ቤተሰቡ እንዲተርፉ አድርገዋል (ሐዋ 26:25-34) በክርስቶስ የሆኑ ክርስቲያኖች በኀጢአት ምክንያት እየተበላሸች ያለችውን ዓለም ከመበስበስ የሚታደጓት መሆን አለባቸው። አማኞች ከተኙ ምድር ተስፍ የላትም ስለዚህ ልንነቃ ይገባናል። እግዚአብሔር የሚሰራው ካመኑበት ጋር ነው።
ጣዕማችን በሌሎች ዘንድ ሊታወቅ ይገባል። በሕይወታችን #የፅድቅን ጥም በሌሎች ዘንድ መቀስቀስ አለብን። ሕይወታቸውን በሕይወታችን ከብልሽት መታደግ ይጠበቅብናል። #ጨውነታችን ካልተገለጠ ከክርስቶስ የተቀበልነውን ማንነት በሚገባ አለመኖራችንን የሚያሳይ ነው።
#የጨው መገኛው በማንኛውም ሰው ቤት ነው። ጥቅሟም ራስዋን መስዋዕት በማድረግ #ጣዕምን መስጠት ነው። አማኞች ለዚህ ዓለም በተለይም አሁን ላለህበት ቦታ #ጣዕምና_ፈውስ እንድንሆን ነው የተጠራነው።
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
— ኤፌሶን 2፥10
እግዚአብሔር ችግርን እነድናስተጋባ አልጠራንም ለችግሩ መፍትሔ አምጪዎች እንድነሆን ነው የጠራን። ስለዚህ #ንቁ ብሎ መፅሐፍ ቅዱስ መክሮናል ልንነቃ ይገባል እንደ #ክርስቲያን እንኑር። ማንን እያገለገልን ነው? እናስተውል ጥሪያችንን እንለይ ከወገንተኝኘት አስተሳሰብ ራሳችንን ልናፀዳ ይገባል እግዚአብሔር የሁሉ ሰው አምላክ እና አባት ነው። ለሰው ፊት አያደላም እግዚአብሔር #ፅድቅን ብቻ ነው የሚተባበረው። በኑሮዋችን እውነተኛ ቅድስናን እንያዝ።
“ዳሩ ግን፦ እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 1፥15-16
#ኢየሱስ
ምሳሌዬ አንተው ነህ በምግባርህ የማውቕ
ንግግርህ ከሩቅ ይጠራል ጨዋነትን ተላብሰሃል
ከውስጤ ገብተህ ቀርተሃል ማን ቢፈለግ ይተካሃል
ጥበብ ፍቅርም በአንተ ይለካል አዋቂነት ከአንተ ይቀዳል
አለቅነት በአንተ ያምራል አስተዳደር በአንተ ይሰላል
መታገስህ ሁሉን ያልፋል መቼ ፍርድህ ቀድሞ ያውቃል
የሊቅ ጥጉ መደምደሚያ የትሁት ልብ ማሳረጊያ
ፍትህ ሚዛኑ በአንተ ከወጣ ዳኝነቱም ከአንተ ይምጣ
#ሰላም_ለኢትዮጵያ ❤️❤️❤️
#ሁሉ_ተደርጎልናል_ሁሉ_ተሰጥቶናል
🙏🙏🙏 #እግዚአብሔር_ይመስገን_በዚህ_ማለዳ_ደስ_የሚል_ዜና_አለን
✅ #ተፈላጊዎች ነን ተቀባይነት አግኝተናል። የደኀንነታችን ዋስትና የተጠበቀ ነው ይሄ ብቻ ሳይሆን #ዋጋ_ያላቸው_ተፈላጊዎች ነን። ተፈላጊዎች የተደረግነው በክርስቶስ ስራ ነው። የምናስፈልገው #ለመንግስቱ ስራ ነው። አሁን ትጥቃችንን ይዘን ለስራ የምንነሳበት ጊዜ ነው። ትጥቃችን ሰማያዊ ሁሉን የሚያሸንፍ ነው።
“እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤”
— ኤፌሶን 6፥14-15
✅ #በክርስቶስ ሊለካ የማይችል #ፍቅር ፣ ሊደመሰስ የማይችል #ፅድቅ ፣ ሊረበሽ የማይችል #ሰላም፣ ሊታወክ የማይችል #ዕረፍት፣ ሊጠፍ የማይችል #ደስታ፣ ሊደበዝዝ የማይችል #ተስፈ ፣ ሊቀንስ የማይችል #ክብር፣ ሊጨልም የማይችል #ብርሀን፣ ሊያልቅ የማይችል #በረከት፣ ሊሸጥ የማይችል #ጥበብ አግኝተናል።
✅ በእግዚአብሔር በኩል ሁሉ ነገር ስጦታ ነው። ከእኛ በኩል ሁሉ ነገር #መቀበል ነው። ተስፋው አንድ ግዜ በነፃ ተሰጥቷል። እንዲሁ ደግሞ በነፃ ይፈፀማል። #ፀጋውን ለመቀበል ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም። እርሱ ሁሉ ነገር የሚያደርገው #ፍቅር አስገድዶት ነው። #የተሰጠንን_ተረድተን_መኖር_የእኛ_ድርሻ_ነው።
#ከፍ_ያለ_መንገድ_ከፍ_ያለ_ሀሳብ
ኢሳይያስ 55
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና፥ ይላል እግዚአብሔር።
⁹ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው።
✅የእግዚአብሔር ሀሳብ ሁሌም ከፍ ያለ ነው ዝቅተኛ የሚባል የሕይወት ደረጃ ላይ ልትገኝ ትችል ይሆናል። የትኛውም ነገር ላይ እንገኝ ትልቅ ማሰብ እንችላለን። አንድ ማሰብ ያለብን ነገር ከእግዚአብሔር ጋር የሚሰሩ ሰዎች የትልልቅ አሳብ ባለቤት መሆናቸው ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ስንውል ትልልቅ ነገሮችን ማሰብ እንለማመዳለን። ሰዎች እንኳን ትንሽ ነገር እንስራ ሲሉን ይከብደናል።
✅ከእግዚአብሔር ጋር እስከሰራን ድረስ ትልቅ ነገር #እናስብ። እግዚአብሔር በምድር ቆይታችን ትልቅ ነገር ለአገራችን ትተን ብናልፍ በእኛ ደስ ይሰኛል የተጠራነውም ለዚሁ ነው። የትኛውም ሁኔታ እንዲያስቆማችሁ አትፍቀዱለት። ዙሪያችሁ ካለ ሁኔታ በላይ ሁሉን ማድረግ የሚችል #መንፈስ_ቅዱስ_በውስጣችሁ_አለ።
✅ምንም እንኳን አሁን ያለንበት ብዙ ችግር ቢኖርም ኢትዮጵያ ግን እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ ተሃድሶ ሆኖላት በአዲስ አስተሳሰብ የሰላም የፍቅር የመተሳሰብ ሀገር ሆና የምናይበት ግዜ ሩቅ አይሆንም ለዚህ ተሀድሶ ግን እኛ በጣም አስፈላጊዎች ነን #አንድ_ተብሎ_ተጀምሮ_ነው_አንድ_መቶ_ሚሊዮን_የሚቆጠረው በአንድ ሰው ውስጥ እግዚአብሔር ትልቅ ኃይል አስቀምጧል 12 ሆነው የተነሱ ሐዋርያት ናቸው በዓለም ሁሉ የሰላምን ወንጌል ያደረሱት።
✅ስለዚህ ፍፃሜያችሁን የሚያሷያችሁ የምታስቡት ሀሳብ ነው። #የታቀፍችሁት_ሀሳብ_ነው_የምትፈለፍሉት። በዕምነት የእኔ ስራ ለሀገሬ ሰላምን የሚያመጣ እግዚአብሔር የሚፈራ የተባረከ ትውልድ እንዲፈጠር ነው ብላችሁ በእምነት ይታየኛል ማለት ትችላላችሁ።
2ኛ ነገሥት 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ኤልሳዕም፦ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነገ በዚህ ጊዜ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸመታል አለ።
² ንጉሡም በእጁ ተደግፎ የነበረ አለቃ ለእግዚአብሔር ሰው መልሶ፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በሰማይ መስኮቶች ቢያደርግ ይህ ነገር ይሆናልን? አለው። እርሱም፦ እነሆ፥ በዓይኖችህ ታየዋለህ፥ ከዚያም አትቀምስም አለ።
✅እግዚአብሔር የተማመነ ሰው የሚናገረው #የእምነት_ንግግር ብቻ ነው። ሀሳባችሁን የሚቃወሙ ሰዎች ቢኖሩም እናንተ ግን በእምነታችሁ ፅኑ ፍፃሜውን ማየት ከፈለጋችሁ እግዚአብሔር ከእናነተ ጋር ይቆማል። ኤልሳ የተናገረው ከፍተኛ ረሀብ እና ችግር ውስጥ በነበሩበት ግዜ ነው እንጂ የሚበሉት በእጃቸው ገብቶ አይደለም። እምነት ማለት ይሄ ነው። ተስፍ ያደረግነውን ነገር እንዳገኘነው የሚያስረዳን ኃይል ነው።
🎷🎷🎷🎷🎷አዋጅ የእምነት ንግግር
#ለሀገሬ_የተትረፈረፈ_ሰላም_ይሆናል
#ለሀገሬ_ብልፅግና_ይሆናል
ለሀገሬ እረፍት ይሆናል
#ለሀገሬ_ደስታ_ይሆናል
#እንባችንን_እግዚአብሔር_ያብሰዋል
#ከዚህ_በኃላ_ራስ_እንጂ_ጅራት_አንሆንም በኢየሱስ ስም !!!
#እግዚአብሔርን_መስማት
“የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል።”— ምሳሌ 1፥33
እግዚአብሔርን አለመስማት ዋጋ ያስከፍላል #እግዚአብሔርን_መስማት እረፍት ያመጣል። እግዚአብሔርን መስማታችንን ከምናውቅበት መንገድ አንዱ ውስጣችን ሰላም ይሰማናል። እግዚአብሔርን አለመስማት ትርፉ አለመረጋጋት ነው። ስንሰማው ብቻ ዕረፍት አለን። ዲያቢሎስ ሁሌም ፍላጎቱ እንድንናወጥና እንድንረበሽ ነው። የዲያቢሎስን ዕቅድ የምናፈርሰው #እግዚአብሔርን_በመስማት ነው። አዳም ከእግዚአብሔር ይልቅ የሚስቱን ቃል ሰምቶ ነው እርግማን ያመጣው ሚስቱም ሄዋን ሰይጣንን ሰምታ ነው ባሏን ያሳተችው። #እግዚአብሔርን_የሚሰማ ሰው ግን ለትውልድ በረከት ይሆናል። ዛሬ ብዙ የሚሰማ ነገር አለ ወንድሜ ምን እየሰማህ ነው? እህቴ ምን እየሰማሽ ነው? #በረከትን የሚያመጣ ወይስ ሌላ? መልሱን ለራሳችን እንመልስ። ግን እንደ ክርስቲያን የተጠራነው #ለበረከት መሆኑን ግን አስረግጬ እነግራችኋለው። ስለዚህ ያለን አማራጭ እግዚአብሔርን በመስማት #በእርጋታ መቀመጥ ነው። በነውጥ ውስጥ የሚያረጋጋ አባት አለን።
🎷🎷🎷🎷 #አዋጅ
#እግዚአብሔርን እሰማለው
#እኔ_ለህዝቤ_በረከት_እንጂ_እርግማን አልሆንም
#መልካምን_ነገር አስባለው
#መልካምን_ነገር እናገራለው
#በመልካም_ስፍራ እገኛለው
#ፅድቅ_ያለበትን ወሬ አወራለው
#ጌታ_ኢየሱስን እከተላለው
#ውስጣዊ_ሰላም_ፍርሀትን_አስወግዶ_እረፍትን_ያመጣል
✅ውስጣዊ #ሰላም ማጣት #ፍርሀትን፣ መረበሽን፣ ለተቃውሞ መነሳትን እና ሌሎች ብዙ ችግሮችን ያስከትላል።
የልብ #ሰላም ያለውን ነብዩ ዳዊትን እንመልከት
“ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚህ እተማመናለሁ።”— መዝ 27፥3 ዳዊት ይህንን በልቡ ውስጥ ያለውን የእምነትና የድፍረት ቃል እግዚአብሔርን በመተማመን የተናገረው ነው። ይህ መገለጥ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን ሕብረት ያመለክታል።
የእኛስ የበለጠው ሕብረታችን ከምን ጋር ነው ከሚዲያ ጋር ወይስ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ሁሉቱም ፍሬያቸውን በልባችን ውስጥ ያስቀምጡልናል። ወይም #እረፍት ይሰጡናል ወይም #ፍርሀት ይለቁብናል። መፅሐፍ ቅዱስ የሚሻለውን ፈትናችሁ ያዙ (ፊሊ1:9-11) ብሎ ምርጫውን ለእኛ ትቶልናል።
“በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።”— መዝሙር 23፥4
✅ዳዊት ምንም ብላቴና ቢሆንም እንኳን የእምነት #ደፍር_ልብ ነበረው። ዙሪያው ያሉ ታላላቅ ወንድሞቹ ሳኦልን ጨምሮ #በፍርሀት ውስጥ ነበሩ። ንጉስ ሳኦልም እንኳን " አንተ ገና ብላቴና ነህና እርሱም ከብላቴናነቱ ጀምሮ ጦረኛ ነውና ይህን ፍልስጤማዊ ለመውጋት ትሄድ ዘንድ አትችልም።" አለው። ነገር ግን ጠንካራ ኃይለኛ እና ደፍር ልብ ያለው ዳዊት "ስለ እርሱ የማንም ልብ አይውደቅ እኔ ባሪያህ ሄጄ ያንን ፍልስጤማዊ እዋጋዋለው።" ዳዊትም ለሳኦል የነበረውን ልምምድ ነገረው
1ኛ ሳሙኤል 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁴ ዳዊትም ሳኦልን አለው፦ እኔ ባሪያህ የአባቴን በጎች ስጠብቅ አንበሳና ድብ ይመጣ ነበር፥ ከመንጋውም ጠቦት ይወስድ ነበር።
³⁵ በኋላውም እከተለውና እመታው ነበር፥ ከአፉም አስጥለው ነበር፤ በተነሣብኝም ጊዜ ጕሮሮውን ይዤ እመታውና እገድለው ነበር።
³⁶ እኔ ባሪያህ አንበሳና ድብ መታሁ፤ ይህም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያውን አምላክ ጭፍሮች ተገዳድሮአልና ከእነርሱ እንደ አንዱ ይሆናል።
³⁷ ዳዊትም፦ ከአንበሳና ከድብ እጅ ያስጣለኝ እግዚአብሔር ከዚህ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያስጥለኛል አለ። ሳኦልም ዳዊትን፦ ሂድ፥ #እግዚአብሔርም_ከአንተ_ጋር_ይሆናል አለው።
✅ዳዊት በእግዚአብሔር ኃይል ስለተመካ ኃይለኛ የተባለውን ጎልያድን አልፈራውም ነበር ዳዊት "ሰይፉ የእግዚአብሔር ነው አለ" “ዳዊትም ፍልስጥኤማዊውን አለው፦ አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው በእስራኤል ጭፍሮች አምላክ ስም በሠራዊት ጌታ #በእግዚአብሔር_ስም እመጣብሃለሁ።”— 1ኛ ሳሙኤል 17፥45
እንዴት ያለ በእግዚአብሔር ስራዎች እና በጥበቃው መታመን ነው። ዳዊት ፈፅሞ #አልፈራም እምነቱን የእግዚአብሔርን ስም በጦር ሜዳ ስፍራው ከፍ አድርጎ አወጀ። ዳዊት እግዚአብሔር ከጎልያድ እና በምድር ላይ ካሉ ኃይሎች ሁሉ እጅግ ታላቅ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር ስለዚህ "ስለ እርሱ የማንም ልብ አይውደቅ ሲል አረጋገጠላቸው።" (1ሳሙ 17:32)
✅ #ሰላም በአንድ ሰው ልብ ውስጥ በነገሰ ግዜ ያሰው የሚተማመን እና #ሰላማዊ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ልብ ውስጥም ሰላማዊነትንና ድፍረትን የሚያሰራጭ ይሆናል። ስለዚህ እኛም #ሰላምን ለሌሎች ለማሰራጨት ልንተጋ ይገባል።
የክርስቶስ #ሰላም በእኛም በአገራችንም ይግዛ!!!
#በክርስቶስ_የሆነውንና_የሆነልንን_ማወቅ
👉ለአለቅነትና ለስልጣንም ሁሉ በእርሱ ሆኜ ተሞልቻለው (ቆላ 2:10)
👉በክርስቶስ ህያው ነኝ (ኤፌ 2:6)
👉በክርስቶስ ከኃጢአት ህግ ነፃ ነኝ (ሮሜ 8:2)
👉በክርስቶስ ከእግዚአብሔር ተወልጃለሁ ክፉው አይነካኝም (1ዮሐ 5:18)
👉በክርስቶስ ቅዱስና ነውር የሌለኝ ሆኛለው (ኤፌ 1:4)
👉የክርስቶስ ልብ አለኝ (1ቆሮ 2:16)
👉በክርስቶስ አዕምሮን የሚያልፍ ሰላም አለኝ (ፊሊ 4:7)
👉በክርስቶስ እውነተኛ ደስታ አለኝ (ፊሊ 4:4)
👉ክርስቶስ በእኔ ውስጥ ስለሆነ በእኔ ያለው በአለም ካለው ይበልጣል። (1ዮሐ 4:4)
👉በክርስቶስ በኩል በሕይወት ነግሻለው (ሮሜ5:17)
👉በክርስቶስ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ ተቀብያለው። (ኤፌ 1:17-18)
👉በክርስቶስ በበሽታና በአጋንንት ላይ ስልጣን ተሰጥቶኛል (ማር 16:17)
👉በክርስቶስ አሮጌውን ሰው ከስራው ጋር አስወግጄዋለው ቆላ (3:9-10)
👉ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለው (ፊሊ 4:13)
👉በክርስቶስ ከማይጠፋ ዘር ተወልጃለው (1ጴጥ 1:23)
👉መልካም ስራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጥሬአለው (ኤፌ 2:10)
👉በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ነኝ (2ቆሮ 5:17)
👉በክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆንኩ ወራሽ ነኝ የእግዚአብሔር የሆነው ሁሉ የእኔ ነው (ሮሜ 8:17)
👉በወደደኝ በክርስቶስ ከአሸናፊዎች በላይ ነኝ (ሮሜ 8:37)
👉በክርስቶስ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነው ነገር ሁሉ ተሰጥቶኛል (2ጴጥ 1:3-4)
👉ስለ ክርስቶስ መልዕክተኛ (አምባሳደር ነኝ) (2ቆሮ 5:20)
👉በክርስቶስ የተመረጠ ትውልድ የንጉስ ካህን ለርስቱ የተለየ ወገን ነኝ (1ጴጥ 2:9)
👉በክርስቶስ የእግዚአብሔር ጽድቅ ነኝ (2ቆሮ 5:21)
👉የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነኝ የራሴ አይደለሁም (1ቆሮ 6:19)
👉በክርስቶስ የዓለም ብርሃን ነኝ (ማቴ 5:14)
👉በክርስቶስ ከእርግማን ተዋጅቻለው ነፃ ነኝ (ገላ 3:13)
👉በመገረፉ ቁስል ተዋጅቻለው (1ጴጥ 2:24)
👉ከክርስቶስ ጋር ተነስቼ በሰማያዊ ስፍራ ተቀምጫለሁ (ኤፌ 2:6)
ይሄ ሁሉ የሆነው ክርስቶስ ስለእኛ ባለው ጥልቅ #ፍቅር መሆኑን ተረድተን #በደኅንነት ያገኘናቸውን ፀጋዎች በሙሉ ተረድተን መልካም እና የተባረከ ሕይወት ለመኖር የቃሉን በረከት አሜን!!! ብለን ልንቀበል ይገባናል። እኛ ሰዎች እንዳሉን ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል ያለንን ነን። እግዚአብሔር ከአንደበታችን ቃል ጋር ይሰራል የአንደበት ቃል ለክፉም ለመልካምም ነገር እንደሚሰራ ተረድተን በአንደበታችን መልካምን ነገር አንናገር በኢየሱስ ስም!!!
🙏 #በጥበብ መመላለስ
✍ #ጥበብ አንድ ማድረግ ለምንፈልገው ነገር ውጤታማ እና ፍሬያማ የሚያደርገን ኃይል ነው።
#ጥበብን ከምንም ስጦታ በፊት ምንም ነገር ከማድረጋችን በፊት ልናስቀድም ያስፈልጋል።
✍ በጊዜያዊ ስሜት መኖር የለብንም። በዚህ ስሜት የሚኖር ሰው #ጥበብ የጎደለው ብቻ ነው። #ጥበበኛ የሆነ ሰው ግን የወደፊቱን በሚገባ ያውቃል። በጊዜያዊ ስሜት አይኖርም ወይም አይመራም። #ጠቢብ ግቡን ጠንቅቆ ያውቃል። ጠቢብ እንዳጋጣሚ የሚኖር ሰው አይደለም። #በጥበብ የተሞላ ሰው በእግዚአብሔር ሃሳብ ውስጥ ብቻ ነው የሚኖረው። ስለዚህ #በጥበብ እንደተሞላ ሰው መኖር አለብን። #በጥበብ የሚኖር ሰው መንገዱን በሚገባ የዘረጋና መውጫ መግቢያውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ነው።
✍ በትክክለኛ ሕይወት ውስጥ መኖር የሚያስችለን #ጥበብ ብቻ ነው። "በዕውቀት ላይ ራስን መግዛት፣ ራስን በመግዛት ላይ መጽናትን፣ በመጽናት ላይ እውነተኛ መንፈሳዊነትን....እነዚህ ባሕርያት የሌሉት ግን የሩቁን የማያይ ወይም ዕውር ነው፤ ከቀድሞው ኀጢአቱ መንጻቱንም ረስቶአል።" 2 ጴጥሮስ 1:6 , 9። ከእውቀት መጒደል ዕውር ከማድረግም በላይ የሩቁን ማየት አያስችለንምና ከዚህ #ጥበብና ከእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት በፍጹም መጒደል የለብንም።
✍ ሰው #በጥበብ ውስጥ ሲኖር ተገቢ የሆነው ስፍራ ላይ ብቻ ነው የሚገኘው። "በአንድ ከተማ ካሉ ዐሥር ገዦች ይልቅ፣ #ጥበብ ጠቢቡን ሰው ኀያል ታደርገዋለች።"መክብብ 7:19።
"ስለዚህ፣ #“ጥበብ ከኀይል ይበልጣል” አልሁ፤ ሆኖም የድኻው #ጥበብ ተንቆአል፤ ቃሉም አልተሰማም።" መክብብ 9:16።
"እርሱን የሚታዘዝ ሁሉ አይጐዳም፤ #ጥበበኛም ልብ ትክክለኛውን ጊዜና ተገቢውን አሠራር ያውቃል።" መክብብ 8:5።
✍ ስለዚህ #ጥበብ ወደሚገኝበት ወደ እግዚአብሔር ቃል ራሳችንን ያለማቋረጥ ማስገባት አለብን የእግዚአብሔር ቃል #በጥበብ እንድንመላለስ የሚያስችለን መንገዳችን ነው። ከእግዚአብሔር ቃል የጎደለ ሰው #ከጥበብ ይጎድላል። #ከጥበብ የጎደለ ሰው ለራሱም ሆነ ለሌላ ሰው እንቅፋት እና ችግር ፈጣሪ ይሆናል።
ስለ ሀገራችን መሪዎች እግዚአብሔር #ጥበብ እንደሰጣቸው እንፀልይ 🙏
#የእግዚአብሔር ፍቅር
🙏 ለሰው ልጅ የሚጠቅመው የእግዚአብሔር ሃሳብ ብቻ ነው። የእርሱ ፈቃድ ደግሞ መልካም፣ ደስ የሚያሰኝና ፍጹም ነው። ሮሜ 12:2። 'ለእናንተ ያለኝን ዕቅድ እኔ ዐውቃለሁ” ይላል እግዚአብሔር ፤ “ዕቅዱም ፍጻሜው ያማረና ተስፋ የሚሰጥ፣ እናንተንም የሚጠቅም እንጂ የሚጐዳ አይደለም።" ኤርምያስ 29:11። ስለዚህ #እግዚአብሔር_ይወደናል_እኛም_በፍቅሩ_እንኖራለን እንዲሁም እንታመናለን። የሰው ልጅ ሁሉ ጥያቄ መልስ ያለው #በእግዚአብሔር_ፍቅር ውስጥ ብቻ ነው። ሰው አደገ ወይም ተለወጠ የሚባለው #በእግዚአብሔር_ፍቅር ሲኖር ነው። ከእግዚአብሔር ፍቅር ተነስተን ነው መመላለስ እና መኖር ያለብን። ምክንያቱም ሰላም እና መረጋጋት ያለው በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ ስንኖር ብቻ ነው። መረጋጋት ካስፈለገን የእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ መግባት እና እርሱን ማጣጣም አለብን።
ሞኝነት ሆኖ አይደለም ፍቅሩን ቀምሼ ነው
ና ሲለኝ የተከተልኩት ነፍሴ ተማርካ ነው
ጠቢባን ያላዩት ዕውቀት ለእኔ ተገልጦ ነው
የጌታን የማዳን ሚስጢር ነፍሴ ተረድታው ነው
ከወርቅ ከዕንቁ በልጦብኝ ነው
ከማንም በላይ ተመችቶኝ ነው
የቱ ነው ታዲያ ሞኝነቱ
ለእኔ ጥበብ ነው ጌታን ማወቁ ኤሄሄ
አምላኬን ማወቄ
🙏 ፈተናን እንዴት እንለፍ?
እንዴት ክርስትያን ይፈተናል? ከተፈተነስ እንዴት ይለፍ?
👉 በዚህ ምድር እስከኖርን ድረስ በተለያዩ ምክንያቶች ልንፈተን እንችላለን። ነገር ግን ምላሻችን ምን ይመስላል ? ነው ዋናው ነገር ፈተና ሁልግዜ በማስተዋል ከተመለከትነው ያለንበትን የእምነት ደረጃ ይነግረናል። አለት ላይ ነው የተመሰረትነው ወይስ ደግሞ አሸዋ ላይ? ማቴ (7:24-27) ጌታችን ኢየሱስ ብዙ ፈተና ደርሶበት ነበር ሆኖም ያላለፈው ፈተና አልነበረም። እኛም በእርሱ መንገድ እንድናልፍ አሳይቶናል።
👊 ችግር ሰው እየመረጠ አይመጣም፤ ፈተናንም ማለፍ የዕድል ጉዳይ አይደለም። ነገር ግን እግዚአብሔር በበራልን መጠን የእያንዳንዳችን ፈተና ማለፊያ ይለያያል። አንዱ እንደ ሙሉ ደስታ ቆጥሮ በእምነት ሲሻገር ሌላው በተቃራኒ ሀዘንተኛ ሆኖ ሊሻገር ይችላል።
❤ ይህን ዓለም አሸንፈን መኖር የምንችለው የእግዚአብሔር ልጆች ነን። 1ዮሐ 5፡4 ምክንያቱም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን መልካም ሃሳብ እና ፍቅሩን እናውቃለንና። ነገር ግን አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፥ ያደርጋሉም።”— ዳንኤል 11፥32
ፈተናን ለማለፍ፦
✅ 1ኛ የእግዚአብሔርን ፍቅር ማወቅ ያስፈልጋል
ፍቅሩን ስናውቅ እኛ ለሚጎዳ ምኞትና ፍላጎት ተላልፈን አንሰጥም በፍቅሩ እንመላለሳለን። ያዕ 1፡13፣ ያዕ 4፡3፣ ፊል 1፡9 የእግዚአብሔርን ፍቅር መረዳት ሁሉን ነገር የምናሸንፍበት መሳሪያችን ነው። በፍቅር መመላለስ ይገባናል እንጂ ፍላጎት ሁሉ እንዲሟላልን አናስብ። ይልቁንም ክፉውን ሃሳብ ወይም ፍላጎት እናጠፋለን። የተሻለውን ነገር ፈትነን እናውቃለን።
ለበጎ ስራ ሁሉ ፍሬ ለማፍራትና በእግዚአብሔር እውቀት ለማደግ ራሳችንን እናሰለጥናለን። 1ቆሮ 1፡10
✅ 2ኛ ከጠላት ይልቅ ስለ አባታችን ማወቅ አለብን
ሰው ስለጠላቱ ያለውን እውቀት ያክል ስለ እግዚአብሔር ቢያውቅ እንዴት መልካም ነበር።
“ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።”
— ኤፌሶን 3፥18-19
መድረኮቻችን ሰይጣንና ስልቱን ማግነኛ መሆን የለባቸውም። በጠላት ሐይል ሁሉ ላይ ስልጣን ተሰጥቶናል፤ ሊጎዳን አይችልም።
✍እንደ ዳዊት በሞት ጥላ መካከል እንኳን ቢሄድ መንገድ ቀይርልኝ ... ሳይል እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንደሆነ ተረድቶ በአምላኩ ላይ በነበረው መታመን ፈተናውን እንዳለፈ እኛም ያለ ማጉረምረም ሕይወትን ለመምራት የእግዚአብሔርን አብሮነት ተረድተን
እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው! እግዚአብሔር የህይወቴ መታመኛዋ ነው ስለዚህ አልፈራም ምድር ብትናወጥ እኔ በአባቴ ፍቅር ውስጥ ሆኜ እኖራለሁ ብለን እምነታችንን ልንገልፅ ይገባል።
🎷እግዚአብሔርን በማወቅ አድጋለሁ። ወደ ህይወቴ ለሚመጣ ፈተና ሁሉ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት አውጃለው አንተ ተራራ በእኔ ፊት ምንም አይደለህም ብዬ አውጃለው! ልክ እንደ ዳዊት የእግዚአብሔርን ትልቅነት እንጂ የጎልያድን ትልቅነት አላውጅም ፍቅሩን ማወቄና ጸጋው በቂዬ ነው። በኢየሱስ ስም አሜን!!!!
🙏 #የእግዚአብሔር_ኃይል_ለማዳን_ነው
✅ እግዚአብሔር የብርታትና የኃይልና የለውጥ ምንጭ ነው። እግዚአብሔር ኃይሉን ያለ አንዳች ወሰንና ገደብ ለሰው ልጅ ሁሉ ሰጥቷል። ኃይሉ ለሰው ልጆች የተሰጠውም ለማዳን ነው። እግዚአብሔር ጋር መድከም፣ መታከት ወይም ሌላ ነገር ስለሌለ በእኛም ውስጥ ይህን ብርታት ለግሶናል። ይህ ኃይል የተሰጠን በብርታት ላይ ብርታትን እየጨመርን እንድንሄድ ነው። ከእግዚአብሔር ኃይል ጋር በመተባበር በኃይሉ ብርታት መመላለስ እንችላለን። #በምናየውና_በምንሰማው_ነገር_ተጽዕኖ_ውስጥ_መግባትም_ሆነ_መውደቅ_የለብንም። ይልቁንም በእግዚአብሔር ኃይል ላይ በመደገፍ እምነታችንን ልንገልጥ ይገባል። የእግዚአብሔር ኃይል በምንም ሁኔታ የሚቀንስ፣ የሚጠፋ እና የሚደበዝዝ አይደለም። ስለዚህ ኃይሉ አሁንም ይሰራል።
"#በወንጌል_አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ #ለድነት_የሚሆን_የእግዚአብሔር_ኀይል ነው፤ ይህም በመጀመሪያ ለአይሁድ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው።"ሮሜ 1:16።
✅ በእግዚአብሔር ኃይል ላይ የምንደገፍ ከሆነ ያለአንዳች ፍርሀት መኖር እንችላለን። ይህ ሊሆን የሚችለው ግን በእምነት ብቻ ነው። እምነት ማለት በእግዚአብሔር ሃሳብ ላይ በእርግጠኝነት ተደላድሎ መኖር ማለት ነው። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የሚያስፈልገን በእግዚአብሔር ኃይል ላይ መታመን እና መደገፍ ብቻ ነው። እግዚአብሔር ኃይሉን ያለ ገደብ አትረፍርፎ ሰጥቶናል። ነገር ግን ይህን መጠቀም የምንችለው በእኛ ፍልጎትና መሻት መጠን ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ኃይል በትክክል አውቀን ለመኖር ልባችን በእግዚአብሔር ሃሳብ ብርሃን ብቻ ሊበራና ሊሞላ ያስፈልጋል። ይህ ሲሆን በእግዚአብሔር ኃይል ሙላት መመላለስ ብሎም በእርሱ ሙላት መኖር እንችላለን። ማየት የሚገባን ዙሪያችን ላይ ያለውን ሁኔታ ሳይሆን እግዚአብሔር ለእኛ የገለጠውን ኃይል ብቻ ነው። የእስራኤል በፍልስጤማውያን ዛቻ መደንገጥ ምክንያቱ የጎልያድ ድምጽ ነበር ። በእግዚአብሔር ኃይል ላይ መደገፍ ቢችሉ ኖሮ በአንዳችም የውጪ ድምጽ መደንገጥ ባልቻሉም ነበር።
✅ እምነት የማይታየውን ዓለም እውን እንደሆነ የምንቆጥርበት ኃይል ነው። ስለዚህ በእግዚአብሔር ኃይል አማካይነት ማሸነፍ እንደምንችል እርግጠኛ መሆን እንችላለን። ይህም እርግጠኝነት በእግዚአብሔር ኃይል ላይ ያለን መተማመን ነው። አንዳችም ችግር የእግዚአብሔርን ኃይል መወሰን ወይም እንዳይሠራ ማድረግ አይችልም። ስለዚህ ከማናቸውም የምድር ችግሮች በላይ ለመኖር በእግዚአብሔር ኃይል ላይ መታመኑ መልካም ነው። ከእግዚአብሔር አባታችን የተሰጠንን ኃይል መገደብ የምንችለው እኛ ብቻ ነን እንጅ #በዙርያችን_ያለ_ማንኛውም_የውጪ_ተጽዕኖ_አይደለም። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ኃይል ውጫዊ በሆነ ነገር ሊያዝ አይችልምና። ነገር ግን እኛ በምንፈልገው መጠን የእግዚአብሔርን ኃይል በሕይወታችን መግለጥ እንችላለን። በዚህም ችግሮች ብለን ከምናስባቸው በላይ መኖር እንችላለን። የእግዚአብሔርም መሻት እኛ ከችግሮቻችን በላይ እንኖር ዘንድ ነውና። ለዚህም ነው መንፈስ_ቅዱስን የሰጠን። ልባችንን በችግር ብዛት ሳይሆን በእግዚአብሔር እውነት ላይ ነው ማሳረፍ ያለብን። ነፍሳችን በእግዚአብሔር ላይ መደገፍን መልመድ አለባት። ነፍሳችን በእግዚአብሔር ላይ ስትደገፍ በእርሱ ሰላም ትጠበቃለችና።
✅ ኑሯችንን በፍጹም ከእግዚአብሔር ኃይል ውጪ ማሰብ የለብንም። ከእግዚአብሔር ኃይል ውጪ መኖር ማለት በተቃጠለ አየር መኖር ነው። የተቃጠለ አየር በምንም መልኩ ሕይወት መሆን አይችልም። ነገር ግን እኛ ለእውነት ቃል እየታዘዝን በእግዚአብሔር ኃይል ውስጥ መኖር አለብን። ሕይወት የሚገኘው በዚህ ውስጥ ነውና። የእግዚአብሔር ማስተዋል በምንም አይመረመርም። የእግዚአብሔርን ማንነት ማወቅ እንዴት ባለ ደስ የሚያሰኝ የእግዚአብሔር ኃይል ውስጥ መኖርን ያስችለናል!!! እግዚአብሔር ለደከሙት ኃይልን የሚሰጥ አምላክ ነው። ከእርሱ ኃይልን የትካፈሉ ደግሞ ዕድል ፈንታቸው አለመድከና አለመታከት ብቻ ነው። #ኢሳ._40:27-31። የምንኖረው ውስጣችን ከተቀመጠው ኃይል የተነሳ ነው።
✅ ሕይታችንን በእግዚአብሔር ላይ እንጅ በጸሎታችን መልስ ላይ አይደለም ማድረግ ያለብን። በእግዚአብሔር ላይ ትክክለኛ የሆነ መታመን ሊኖረን ያስፈልጋል። ስለ ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ላይ ነው መታመን ያለብን። ይህ ደግሞ በአብርሃም ሕይወት ይገለጣል። እግዚአብሔርን ከመታመን በላይ ምንም የሚበልጥ ነገር የለም። #አብርሃም_ከሁኔታዎች_ይልቅ እምነቱን በእግዚአብሔር_ቃል_ላይ_ነበር_ያደረገው። በእግዚአብሔር ሃሳብ ላይ አርፎ እና ተደላድሎ ነበር የሚኖረው። ከዚህ ሕይወት የሚያስወጣን ደግሞ ፍርሃት ነው። በእምነት መመላለስ ከዚህ በላይ ያደርገናል። እምነት ማለት በጸጥታ መኖር ወይም መመላለስ ነው። አብርሃም በአንዳች ነገር አልደከመም። ይስሐቅን መስዋዕት አድርገህ አቅርብ ሲባል እንኳን እንደሚነሳ እርግጠኛ ነበር። ይህ ደግሞ በእግዚአብሔር ላይ ያለው እምነት ውጤት ነው። እምነት በጤናማ አየር ውስጥ መኖር ነውና።
✅ በእግዚአብሔር ላይ የሚታመን ሰው ለችግሮቹ እና ለፍርሃቱ ሁሉ መፍትሄን ማምጣት ይችላል። የምንድንበትን ኃይል ማግኘት የምንችለው በእግዚአብሔር ላይ ካለን መታመን ተነስተን ብቻ ነው። "#ፍርሃት_በሚይዘኝ ጊዜ፣ #እምነቴን_በአንተ ላይ አደርጋለሁ። #ቃሉን_በማመሰግነው አምላክ፣ #በእግዚአብሔር_ታምኛለሁ፤ አልፈራም፤ ሥጋ ለባሽ ምን ሊያደርገኝ ይችላል?"መዝሙር 56:3 - 4
#ሁኔታዎችን_አይቼ_አልደክምም
#የምበረታበት_ኃይል_በውስጤ_አለ!
#አምላኬ_እግዚአብሔር _ብርቱ_አድርጎኛል!
#ስለዚህ_አልደክምም፣_አልታክትም፣_እበረታለሁ!
#ሁሉን_ቻይአምላክ_ለኔ_አባቴ_ነው!!!
