805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ልመና
ጸሎት ምልጃና ምሥጋና
ለሰዎች ሁሉ እንዲደረግ ከሁሉም በፊት እመክራለሁ
በመንፈሳዊነትና በመልካም ጠባይ እየተመራን
በሰላምና በጸጥታ እንድንኖር በተለይ
ለነገሥታትና በስልጣን ላይ ላሉ ሁሉ ጸልዩ
አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለህዝቤ
የራሴን የግሌን ነገር ትቼ
እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለምድሬ
የራሴን የጸሎት ርዕስ ትቼ
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (2x)
የአገሬ መፍትሄዋ የእንቆቅልሿ መፍቻዋ
ቁልፉ ያለው ሰው ጋር አይደል
ታዲያ ማንም አይታለል
ስለእልቂቷ ወሬን ትቼ ስንበረከክ ተደፍቼ
ይሰማኛል አምነዋለሁ ከዚም በፊት አይቻለሁ
ሁሉም ነገር ያበጀዋል ዝብርቅርቁን ያሳምራል
አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለህዝቤ
የራሴን የግሌን ነገር ትቼ
እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለምድሬ
የራሴን የጸሎት ርዕስ ትቼ
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (2x)
በችግሯ ካሳለች??? ይልቅ እኔ ፊቱ ልውደቅ
በዓለምነው ባልጠይቀው እዳው በእኔ ጫና ላይ ነው
መፍትሄ ላይሆን ወሬን ትቼ ልንበረከክ ፊቱን ሽቼ
ሰሚ አምላክ እያመንኩኝ ለምን መፍትሄ አጣለሁኝ
እልቅም ለውጥ አመጣለሁ ለምድሬም ፈውስ እሆናለሁ
አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለህዝቤ
የራሴን የግሌን ነገር ትቼ
እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለምድሬ
የራሴን የጸሎት ርዕስ ትቼ
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (2x)
ብለምነው ስለአገሬ ሸክም ቢኖረኝ ለምድሬ
ያለባትን ችግር ሁሉ ይዤው ልቅረብ ከመስቀሉ
ጌታዬ እኮ ያደምጠኛል እንደሃሳቡ ይመልሳል
ሳልታክት ፊቱ እቀርባለሁ ቃሉም ይላል ጸልያለሁ
ሸክሞን ሳሳየው የምድሬን ይፈውሳታል አገሬን
አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለህዝቤ
የራሴን የግሌን ነገር ትቼ
እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለምድሬ
የራሴን የጸሎት ርዕስ ትቼ
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች
ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች
ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (2x)
ኢትዮጵያን ግብኛት ተመልከታት
በቃልኪዳንህ አስባት (4x)
🙏 7 የፆም የፀሎት ቀን ታወጀ
“የኢያሪኮ ቅጥር ሰባት ቀን ከዞሩበት በኋላ በእምነት ወደቀ።” — ዕብራውያን 11፥30
🙏 ውድ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ አሁን በአገራችን ባለው ሁኔታ #የፆም_የፀሎት ጊዜ የታወጀ ሲሆን ይህን ተከትሎ እኛም በፆም በፀሎት በአባታችን ፊት እንድንቀርብ ያስፈልጋል።
👇እንዴት መፆም መፀለይ አለብን
1 በንስሐ መንፈስ
“ነገር ግን የእስራኤል ቤት ሁሉ የጠነከረ ግምባርና የደነደነ ልብ አላቸውና፥ እኔንም መስማት እንቢ ብለዋልና የእስራኤል ቤት አንተን አይሰሙም።”— ሕዝቅኤል 3፥7
የእግዚአብሔርን ምክር የማይሰማ ህዝብ መጨረሻው ጥፋት ነው። እግዚአብሔር በፍቅር እርስ በእርስ እንድንዋደድ ነው የመከረን እኛ ግን እርስ በእርስ እንጠፋፋለን ስለዚህ ከእግዚአብሔር ምክር በመውጣታችን ይህ ጥፋት ደርሶብናል። ስለዚህ አንተን ባለመስማታችን ይቅር በለን ብለን በፊቱ በንስሀ እንቅረብ ህዝባችንን ይዘን።
2 ❤ንፁህ ልብ ይዘን እንቅረብ
“መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን #ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።” — ራእይ 5፥9-10
ይህ እውነት ያልገባው ክርስቲያን ዳግም ያልተወለደ ብቻ ነው።
የእገሌ ወገን በመሆናችን እያለ የሚጮህ ጩኸት በልባችን ካለ መጀመሪያ ከፀሎት በፊት ይህን እናስወግድ ምክንያቱም እንደ እግዚአብሔር ቃል የሆነው ዘር ይሻለናል። ሁሉም ሰው የእግዚአብሔር ክቡር ፍጡር ነው እኛ ደግሞ በክርስቶስ #ተዋጅተናል እያልን ዘር የምንቆጥር ከሆነ ገና ክርሰቲያን አልሆንም። እውነተኛ ክርስቲያን የክርስቶስ ዘር ብቻ መሆኑን የተረዳ ነው። ስለዚህ ሁሉም ደማቸው የሚፈሰው በክርስቶስ ወንድም እህቶቻችን እንደሆኑ እያሰብን እንፀልይ ራሳችንን በቦታው ከተን እንፀልይ
🎷እኔ የክርስቶስ ዘር ነኝ ብለን ራሳችን ላይ እናውጅ
🎷ወንድሜም የክርስቶስ ዘር ነው ብለን እናውጅ
3 በዕምነት መፀለይ
“ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።” — ዕብራውያን 11፥6
ትክክለኛ (እውነተኛ ) #ዕምነት ልብን የሚያሳርፍ ነው
ያላረፈ ልብ #ከዕምነት መጉደል ነው።
ስለዚህ ልባችን #በዕምነት ማረፍ እንዲችል ከፈለግን ልባችንን ልንጠብቅ ይገባል አብዛኛው ክርስቲያን ሚዲያ ላይ ተጥዶ ምን እየሆነ ነው የሚል ከሆነ በፍፁም ይህ ትክክል አይደለም ከእምነት ያጎድለናል። እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ወቅት የበለጠ ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡ መሆን አለባቸው እንጂ በነፈሰበት የሚነፍሱ ሊሆኑ አይገባም። ስለዚህ ልባችንን ወደ እግዚአብሔር ቃል ይዘን በፊቱ መቅረብ አማራጭ የሌለው ግዴታችን ነው።
ራሳችንን እንጠይቅ ምን ያህል ሰዓት ሚዲያ ላይ ምን ያህል ሰዓት የእግዚአብሔር ቃል ላይ እንደምናሳልፍ? ልባችን ይፈርዳል
“አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና።” — ምሳሌ 4፥23
🙏ማታ ልዩ የፀሎት ግዜ ይኖረናል
ሁሉን ማድረግ የሚችለውን የክርስቶስ ኢየሱስን ደም ረጨን በአገራችን ላይ በኢየሱስ ስም!!!
በክርስቶስ የተወዳችሁ ወገኖች ሆይ ስለ ምድሪቱ ስለ ሀገራችን ስለ መንግስት ስለ ቤተክርስቲያን በያለንበት አጥብቀን እንጸልይ። በዚህ ሰአት በጭንቅ ዉስጥ ስላሉ ሕዝቦች እንዲሆም ለኛ አባላት ቤተሰቦች በመቀሌና በአካባቢው ስለሚገኙ ሁሉ ሰላም እንዲሆን እንፀልይ።
“በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።”
— 2 ዜና 7፥14
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 ትንቢተ ኤርምያስ 33
11፤ የሐሤት ድምፅና የደስታ ድምፅ፥ የወንድ ሙሽራ ድምፅና የሴት ሙሽራ ድምፅ፦ እግዚአብሔር ቸር ነውና፥ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና የሠራዊትን ጌታ እግዚአብሔርን አመስግኑ፡ የሚሉ ድምፅ፥ ወደ እግዚአብሔርም ቤት የምስጋናን መሥዋዕት የሚያመጡት ድምፅ እንደ ገና ይሰማል። የምድርን ምርኮ ቀድሞ እንደ ነበረ አድርጌ እመልሳለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር።
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏
📖 ትንቢተ ኤርምያስ 24
7፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ የሚያውቅ ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ በፍጹምም ልባቸው ወደ እኔ ይመለሳሉና ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 136
1፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
2፤ የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።
3፤ የጌቶችን ጌታ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
4፤ እርሱ ብቻውን ታላቅ ተኣምራትን ያደረገ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
5፤ ሰማያትን በብልሃት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
6፤ ምድርን በውኃ ላይ ያጸና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤
#ሀሳብ
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ፥ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ፥ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ እነዚህን አስቡ፤”
— ፊልጵስዩስ 4፥8
#ስለምታስበው ነገር ተጠንቀቅ ሃሳቦችህ ወደ ቃላት ይለወጣሉና
#ስለምትናገረው ነገር ተጠንቀቅ ንግግሮችህ ወደ ተግባር ይለወጣሉና
#ስለምተገብረው ነገር ተጠንቀቅ ተግባርህ ወደ ልማድ (ባህሪ) ይለወጣልና።
#ሰለልማድህ ተጠንቀቅ ልማድህ ፍፃሜህን ይወስናል።
መልካም የተባረከ ቀን🙏
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏
📖 ትንቢተ ኤርምያስ 24
7፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ የሚያውቅ ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ በፍጹምም ልባቸው ወደ እኔ ይመለሳሉና ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ ህይወት በመንፈስ ቅዱስ ሴሚናር
✅ትምህርቱን ለጀመሩ ሰዎች የልቦና አይኖቻቸው እንዲከፈቱ
✅ለአገልግዮች የእግዚአብሔር ፀጋ እንዲበዛላቸው
መንፈስ ቅዱስ በሀይል እንዲገለጥ
እግዚአብሔርም እንዲከብር
በእምነት እንፀልያለን
🙏
📖 ወደ ኤፌሶን 1
17፤ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
18-19፤ ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 1ኛ ዜና መዋዕል 16
34፤ ቸር ነውና፥ ምህረቱም ለዘላለም ነውና: እግዚአብሔርን አመስግኑ።
#በአዕምሮ_መታደስ_የተለወጠ_ሰው
3 #ከመንፈስ_ቅዱስ ጋር ያለውን ሕብረት ይረዳል
“ደግሞም ያተመን #የመንፈሱንም መያዣ በልባችን የሰጠን እርሱ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 1፥22
“እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ #በመንፈስ_ቅዱስ ታተማችሁ፤”
— ኤፌሶን 1፥13
#መንፈስ_ቅዱስ ተቀብለናል። በውስጣችን አለ። በውስጣችን ሆኖ ምስክርነት ይሰጠናል። ምስክርነቱ እውነተኛ ነው። የተከተልነው መንገድ እውነተኛ መሆኑን #መንፈስ_ቅዱስ ዋስትና ይሰጠናል ያረጋግጥልናል። በውስጣችን እየፈሰሰ እንዳናፍር ያበረታታናል። ተስፋችን ተስፋ ብቻ እንዳልሆነ ይነግረናል (ሮሜ 5:5) መንገድ ስተን እንዳንወጣ በፍቅር ይመልሰናል። የማን ወገን መሆናችንን ያሳውቀናል። #በመንፈስ የጀመርነውን ሕይወት በስጋዊነት እንዳናቋርጥ ያነቃናል ይጠብቀናል። (ሮሜ 8:9)
#መንፈስ_ቅዱስ አንድ ቀን ከእርሱ ጋር በመንግስተ ሰማይ እንደምንሆን እና የከበረውን አካል እንደምንለብስ የሚያረጋግጥልን መያዣ ቀብድ ዋስትና ማስተማመኛ ነው።( ኤፌ 1:14) ዛሬም ቢሆን በልባችን በመንግስት ሰማይ ሀሴት እንድናደርግ ያስችለናል።
ዋስትና በሰጪው ማንነት ይወሰናል። የተሰጠን ዋስትና ከሰጪው የተነሳ እጅግ ፅኑ በመሆኑ እኛም እንፀናለን። ተስፋውን የሰጠው የታመነ በመሆኑ ተስፋውን አንጠራጠርም። በተቀባንበት መንፈስ ክርስቶስ እግዚአብሔር አብን ያከብር እንደነበረ እኛም በሕይወታችን እግዚአብሔርን እንድናከብር ይረዳናል (ማቴ 5:16) ዮሐንስም ይህንን ቅባት ከእግዚአብሔር እንደተቀበልን መስክሮልናል። (1ኛ ዮሐ 2:22-27)
#የመንፈስ_ቅዱስ በእኛ ውስጥ መገኘት አሰፈላጊነቱ እኛን በባለቤትነት ማህተም ለማረጋገጥ ነው። (ኤፌ 1: 13-14) ማህተም ባለንብረቱ ማን እንደሆነ የሚጠቁም ነው። ማህተሙን ብቻ መመልከት ባለቤቱ ማን እንደሆነ መለየት ይቻላል። የማህተቡ ባለቤት ማህተሙ ያረፈበት ንብረት ጠባቂና ተከላካይ ነው። ህጋዊ ከለላ ይሰጣል በህግም ያስጠብቃል ኃላፊነትም ጭምር ይወስዳል ተጠያቂነትም አለበት።
እኛ #በመንፈስ_ቅዱስ ታትማችኋል ተብለናል (ኤፌ1፥13) ማኅተሙ ያረፈው እኛ ላይ ነው። የማኅተቡ ባለቤት ኢየሱስ ነው። የታተምነው ደግሞ #በመንፈስ_ቅዱስ ነው። የማኅተቡ ባለቤት ጠባቂያችን ነው። እንደንብረቱ ይከላከለናል። ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ንብረት ነን። በዋጋ ተገዝተናል የራሳችን አይደለንም። (1ቆሮ 6:19-20) ስለዚህ ደኅንነታችን ዋስትና ያለው ነው።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ነገ ስለሚጀምረው ህይወት በመንፈስ ቅዱስ ሴሚናር
✅ትምህርቱን ስለሚጀምሩ ሰዎች የልቦና አይኖቻቸው እንዲከፈቱ
✅ለአገልግዮች የእግዚአብሔር ፀጋ እንዲበዛላቸው
መንፈስ ቅዱስ በሀይል እንዲገለጥ
እግዚአብሔርም እንዲከብር
በእምነት እንፀልያለን
🙏
📖 የማቴዎስ ወንጌል 28
19-20፤ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።
#በአዕምሮ_መታደስ_የተለወጠ_ሰው
2 የክርስቶስ #ወዳጅ መሆኑን ይረዳል።
“ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ #ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና።”
— ዮሐንስ 15፥15
ክርስቶስ ደሙን ሲያፈስ እና ሲሞት እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ #እወዳችኋለሁ እያለ ነበር። ይህ ለጠላት የቀረበ የፍቅር ጥሪ ነበር። እግዚአብሔር በፍቅር ጥሪ ካስጠጋን በኋላ #ወዳጆቹ አደረገን።
ኢየሱስ የቀራጮች እና የኃጢአተኞች ወዳጅ ተብሎ ታምቷል። (ሉቃስ 7:34) እርሱም ደቀመዛሙርቱን #ወዳጆቼ ብሎ ጠርቷቸዋል። ዮሐ (15:14) ጠቢቡ ሰለሞን ከወንድም አብልጦ የሚጠጋጋ ወዳጅ (ምሳ 18:24) እኛንም ዛሬ ኢየሱስ #ወዳጆቼ ብሎ ይጠራናል።
እንደ #ወዳጅ መቆጠራችን በእኛ ምንም አይነት ስራ እና ምርጫ አይደለም በእርሱ ተመርጠን ነው። የዋህ በልቡም ትሁት የሆነው ጌታ ምርጫ ውጤት ነን። ስለዚህ ባሪያ በህግ #ወዳጅ ግን በፍቅር የታሰረ ነው። እኛም በፍቅር የታሰርን ወዳጁ ነን።
#ወዳጄ አንተ ነህ #ወዳጄ አንተ ነህ #ወዳጄ
የማትጥል የማትከዳ ሁልጊዜ አንተ ነህ ሁልጊዜ
ኢየሱስ አንተ ነህ ኢየሱሴ አንተ ነህ ኢየሱስ
የማትጥል የማትከዳ ሁልጊዜ አንተ ነህ ሁልግዜ
መልካም #ወዳጅ ስላለን ደስ ይበለን
የምናማክረው #ወዳጅ አጠገባችን አለን
ሚስጥረኛ ከልብ የሆነ #ወዳጅ
#በአዕምሮ_መታደስ_የተለወጠ_ሰው
1 የእግዚአብሔር #ልጅ መሆኑን ይረዳል
“ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር #ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤”
— ዮሐንስ 1፥12
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ሰውና ስለ እግዚአብሔር ግንኙነት ብዙ ተብሏል እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው እኛ ፍጡር ነን እርሱ ሰጪ ነው እኛ ተቀባዮች ነን እግዚአብሔር ገዢ ነው እኛ ተገዢዎች ነን እርሱ እረኛ እኛ በጎቹ ነን ወዘተ ... ሆኖም ከነዚህ ሁሉ የበለጠ እውነት በመካከላችን እንዳለ ቃሉ ይነግረናል። ይህም የእግዚአብሔር አባትነት እና እኛ የእርሱ #ልጆች መሆናችንን። ብዙ ክርስቲያኖች የእግዚአብሔርን አምላክነት ቢረዱም አባትነቱ ላይ መረዳት ጎድሏቸዋል ለዚህም ነው ፀሎት እንኳን ሲፀልዩ እግዚአብሔርን የማይደረስበት እሩቅ የሆነ አምላክ አድርገው የሚመለከቱት። እንግዲህ ለዚህ ነው በቃሉ የታደስ አዕምሮ የሚያስፈልገን።
የእግዚአብሔር #ልጅ የመሆን ስልጣን በክርስቶስ ስራ ያገኘነው ልዩ ስጦታችን ነው።
“እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።”
— ዮሐንስ 1፥13
ከእግዚአብሔር ከተወለድን ልጆች ነን እንጂ ገና የምንጠብቀው ነገር አይደለም። ቤተክርስቲያን ስለሄድን ልጅነትን አላገኘንም ወይም ደግሞ መልካም ስራ ሰርተንም አናገኝም ጥሩም መጥፎም ሰው ስለሆንን አይደለም ነገር ግን ከእግዚአብሔር ስለተወለድን በምንም የማንለውጠውን ልጅነት ተቀብለናል እግዚአብሔር ይመስገን።
ስለዚህ ይህንን ስልጣናችንን በሁሉ ሕይወታችን ላይ ልንጠቀምበት እና ልንገልጠው ይገባናል
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ #አባ_አባት ብለን የምንጮኽበትን #የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።
¹⁶ የእግዚአብሔር #ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።
በየዕለቱ የእግዚአብሔር #ልጅ መሆናችንን እናውጅ
በዚህ ቀንም አዋጃችሁን ተናገሩና እኔ ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የሚችል ለሁሉ መልካም የሆነ ደግ እና ፃድቅ ቸር #አባት አለኝ!!! የእግዚአብሔር #ልጅ ነኝ!!
ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3
1 እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።2 በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም::
9 አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥ 10 የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።
#ሰው_ከነፍሱ_ይልቅ_ለስጋው_ይጠነቀቃል_ለምን?
ነፍሳችን ተርቦ ስጋችን ተመችቶት ይሆን? ስጋችንን በቀን 3 ግዜ እንመግበዋለን እንዲጠነክር አስፈላጊውን ልምምድ እናደርጋለን። ይህን ማድረጋችን ክፋት የለውም። ጤናማ አካል አስፈላጊ ስለሆነ። ይሁን እንጂ ጤናማ ነፍስ የበለጠ አስፈላጊ መሆኑን ተረድተን ስለ ነፍሳችን የምንጠነቀቅ ስንቶች ነን?
ማርቆስ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁶ ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?
³⁷ ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?
የዘመኑ ሰው ለስጋው ተገዢ ሲሆን ለነፍሱ ግን ፍፁም ግድ የሌለው እየሆነ ነው። ጊዜያዊ የሆነውን ነገር ሲያሳድድ ዘላለማዊ የሆነውን ችላ ብሏል። ለስጋው ውበት ሲጨነቅ መንፈሳዊውን ሕይወት ውስጥ ያለውን ውበት ችላ ብሏል። ስጋውን ደስ ለማሰኘት ብዙ ለፍቶ ነገር ግን እውነተኛ ዘላቂ ደስታ አላገኘም። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ መኖር ለብዙዎች ከባድ እና አሰልቺ ሕይወት ውስጥ ከቷቸዋል። እውነተኛውን ደስታ እና ሰላም ሲያጣ በሱስ ለመደበቅ ወደ ሱስ ፊቱን ያዞራል። ይህም ፈጥኖ ይሰለቸውና በሕይወት ከመቆየት ይልቅ ሞትን መመኘት ይጀምራል። ነገር ግን በዚህ ሂደት ውስጥ አይረዳው እንጂ በውስጡ የደስታ ሁሉ ምንጭ የሆነውን ክርስቶስን ይናፋቃል።
ሰው #የታደሰ አዕምሮ ሲኖረው አስተዋይ ይሆናል የተፈጠረውም ከአምላኩ ሸሽቶ ለመኖር ሳይሆን ከእርሱ ጋር የቀረበ ሕብረት እንዲኖረው መሆኑን ይረዳል። ከክርስቶስ ጋር ሕብረት ለመፍጠር ድርሻውን ይፈፅማል። ለነፍሱ የሚገባውን ክብር ይሰጣል። የፅድቅ ሕይወት ምርጫው ያደርጋል። ስለዚህ በታደሰ #አዕምሮ ልንኖር ይገባል።
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
— ሮሜ 12፥2
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌በሚመጣው እሁድ ስለሚጀምረው ህይወት በመንፈስ ቅዱስ ሴሚናር
✅ትምህርቱን ስለሚጀምሩ ሰዎች የልቦና አይኖቻቸው እንዲከፈቱ
✅ለአገልግዮች የእግዚአብሔር ፀጋ እንዲበዛላቸው
መንፈስ ቅዱስ በሀይል እንዲገለጥ
እግዚአብሔርም እንዲከብር
በእምነት እንፀልያለን
🙏
📖 የማቴዎስ ወንጌል 28
19-20፤ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌እረፍት ስላጡ ነፍሶች
✅ከያቆርጠው ፍለጋ ተመልሰው
✅ሰላም ወደሆነው ወደ ነፍሳቸው እረኛ እንዲመለሱ
እንፀልያለን 🙏
📖 1ኛ ጴጥሮስ 2
25፤ እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።
#2013_ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሴሚናር
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ተከታታይ የመፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት ብዙ ሰዎችን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ላይ ለውጥ ያመጡበት ትምህርት ሲሆን ይህ ትምህርት በቀላሉ ምዕመናን እንዲረዱት ተደርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ በምዕመናን ሕይወት ትልቅ ለውጥ ማምጣት መቻሉን አረጋግጠናል ።
🙏 “ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ ሆሴዕ (4:6) በእርግጥም ዕውቀት አንድን ነገር ማድረግ የምንችልበትን አቅም የሚሰጠን ልዩ ስጦታ ነው። ለዚህም ነው እግዚአብሔር እንዳንጠፋ ቃሉን የሰጠን በክርስትና ሕይወት ፋሬያማ እና አስደሳች ሕይወት መኖር የምንፈልግ ከሆነ የግድ የእግዚአብሔር ቃል በግል ያስፈልገናል። ያለበለዚያ ቤተ/ያን ከመመላለስ ውጪ ለውጥ ባለው የእድገት እና የእርካታ ሕይወት መኖር አንችልም።
🙏 “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
— ሮሜ 12፥2
ስለ ሕይወት ተረድተን በተሰጠን ሕይወት በሙሉ አቅማችን መመላለስ የምንችለው ጤናማና ትክክለኛ እይታ በልባችን ሲኖረን ነው። ይህንን ዕይታ የምናገኘው #በአእምሮ መታደስ መለወጥ ስንችል ነው። ስለዚህ አእምሮአችንን በማደስ ልባችንን መለወጥ ወደሚችለው ወደ እግዚአብሔር ቃል ልንቀርብ ይገባናል። ይህን ማድረግ ከቻልን በሕይወታችን ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲከናወን እና ለቃሉ ተገዝተን ትዕዛዙን ጠብቀን መኖር የምንችልበትን አቅም እናገኛለን።
ለዚህ ነው #በአእምሮ መታደስ የሚያስፈልገን።
እነዚህ ጥያቄዎች እርሶ ጋር ካሉ ትምህርቱ ያስፈልጎታል
1 መንፈሳዊ ሕይወቴን እንዴት መለወጥ እችላለው?
2 መፅሐፍ ቅዱስ ባነበውም አልረዳውም እንዴት መረዳት እችላለው?
3 የፀሎት ሕይወቴን እንዴት ማሳደግ እችላለው?
4 እግዚአብሔርን ከማያስከብር ሕይወት እንዴት መራቅ እችላለው?
5 ስለ መንፈስ ቅዱስ አሰራር መረዳት እፈልጋለሁ
ትምህርቱ እነዚህና በዚህ ውስጥ ያልተጠቀሱ ብዙ የምዕመናን ጥያቄዎችን የሚፈታ በመሆኑ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል።
ቦታ: ቅዱስ ሚካኤል በሚገኘው በአ.አ ሀገረ ስብከት ሐዋርያዊ አገልግሎት ጽ/ቤት (ACS) አዳራሽ ዘወትር እሁድ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ
#አዘጋጅ_የኢትዮጵያ_ካቶሊክ_ካርዝማቲክ_እንቅስቃሴ
ለመማር ሲመጡ መፅሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ ደብተር መያዝ አለቦት።
2ኛ ሳሙኤል 22
3፤ እግዚአብሔር ጠባቂዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ፤ ጋሻዬና የረድኤቴ ቀንድ፥ መጠጊያዬና መሸሸጊያዬ፥ መድኃኒቴ ሆይ፥ ከግፍ ሥራ ታድነኛለህ።
እናመሰግንሀለን ጠባቂያችን አለታችን አንባችን መመኪያችን ማምለጫችን ጋሻችን መጠጊያችን ከለላችን መሸሽጊያችን አዳኛችን ፈዋሻችን መድሀኒታችን እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሀለን እናመሰግንሀለን እናመሰግንሀለን::
ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን አመስግኑ ይላል ቃልህ በሁሉም ሁሌም እናመሰግንሀለን:: ይገባሀል ምስጋና ሌላ የምንሰጥህ የለም ተመስገን ስላለፍው ሳምንት ተመስገን ስለአዲሱም ሳምንት ተመስገን ስለውሎአችን ተመስገን በምሽታችንም ተመስገን ከእኛ ጋር ስላለህ እናመሰግንሀለን መገኘትህ ይሙላን ሀይልህ ያበርታን እንደገና በአዲስ ጸጋ ዳሰን መንፈስ ቅዱስ ሁል ጊዜ ሁለንተናችንን ቀድሰን በቃልህ አበርታን የልቦና አይኖቻችንን አብራልን ቃሉን በቀንም በለሊትም የምናሰላስልበት ጸጋህን ስጠን በአንተ ደስ ይለናል በሁሉም ክበር ተመስገን ተወደስ አሜን!!!
