en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
ኤፌሶን 5:2/ቆላስያስ 3:12-14 ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ። እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ። እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ። በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት። አሜን የተጠራነው በፍቅር ለፍቅር ነው! የተጣበቅነው መሐሪ ሩህሩህ ቸር ትሁት የዋህ ትእግስትን የተሞላ ከሆነው ኢየሱስ ነው ! የተወለድነው ነቀፌታን ከማያውቅ ይቅር ባይ ቸር በከፍታ ላይ ካለው ፍቅር ከሆነው አባታችን እግዚአብሔር ነው!!! ይቅር ማለት ግድ ይለናል የዘር ግንዳችን ይቅር ባይ ነው እና!!! እርስ በርሳችን መዋደድ መፋቀር መተሳሰብ ግድ ይለናል የዘር ግንዳችን ፍቅር ነው እና!!! መሀሪነት ቸርነት ለጋስነት የዋህነት ትእግስተኛነት እድል ፈንታችን ነው የእግዚአብሔር ልጆች ነን እና!!! ይህንን ሁሉ ክብር በሙላት ያወረሰን አምላክ እና አባታችን ክብር ምስጋና አምልኮ ስግደት ይሁንለት!!! አሜን 🙏🏽

እናመሰግንሃለን አባ ከምህረትህ ብዛት የተነሳ ቀናችንን በድል አሳልፈን በብዙ ምስጋና እፊትህ ቀርበናል ስላሳለፍነው የሱባኤ ሳምንታት እጅግ አድርገን እናመሰግንሃለን ! ለምድራችን እናት ትሆነን ዘንድ እነሗት እናታችሁ ብለህ የሰጠኸን ብፅዕት ሩህሩህ ትሁት አዛኝ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በልጇ ቀኝ ሆና ስለምድራችን የምታነባው እምባ የምትቃትተው መቃተት ለአገራችን ሰላምን ስላወረደልን ምስጋና ይድረሳት! በነገውም እለት የምናከብረው የእናታችን ኪዳነምህረት በአል አንተ የምትከብርበት ስምህ ከፍ ብሎ የሚገንበት ሰላምህ ለአገራችን የሚፈስበት መንፈስ ቅዱስ በድንቅ አገላለጥ የሚገለጥበት በየቤታችን በመንፈስህ እሳት የምንዳሰስበት የምንጥለቀለቅበት ቅዱስ ጊዜ እንዲኖረን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንለምንሃለን ስለምትሰማን ስለሚሆንልን እጅግ አድርገን እናመሰግንሃለን ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ለእግዚአብሔር ወልድ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይሁን !!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ መንፈስስ አንድነት ✅ መለያየት ቀርቶ የክርስቶስ አካል ሁሉ በሰላም ✅በመንፈስ አንድ ሆነን ማምለክ እና ማገልገል እንዲሆንልን በህብረት እንፀልያለን 📖 ወደ ኤፌሶን 4:1 እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ 2፤ በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤ 3፤ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።

ወደ ዕብራውያን 4 16፤ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ። ወደ ጸጋው ዙፋን ስር በእምነት እንቅረብ ኢየሱስ በድካማችን የሚራራልን ጸሎታችንን የሚሰማ የሚመልስ ከፈለግነውና ከጠየቅነው በላይ አብልጦ የሚሰጥ አባት አለን ስሙ ይባረክ:: የእግዚአብሔርን የጸጋ ዙፋን በህልውናው በመገኘቱ ፍቅር ምህረት እርዳታ ሰላም እረፍት ይቅርታ መንፈስን የሚያድስ ሀይል የመንፈስ ቅዱስ ሀይል ሙላት መንፈሳዊ ስጦታ መንፈሳዊ በረከት በማንኛውም ጊዜ የምንፈልገውን ሁሉ የምናገኝበት የእግዚአብሔርን ጸጋ ዙፋን ሀሌሉያ በእምነት እንቅረብ አሜን!!! እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት በሚያስፈልገን ጊዜ የሚያስፈልገንን ወገኖቻችንን ይዘን ቀርበናል ስለ ሁሉ በመሉ ልባችን ሁሉንም ሰብስበን ኢትዮጵያን ያለውን ሁኔታ ሕዝቦችዋን መሪዎችዋን የአብያተ ክርስትያናት መሪዎች ወጣቶችን ወታደሩን ገበሬውን የታመሙትን አስታዋሽ የሌላቸውን አዛውንቶች በችግር በመከራ በጭንቀት ያሉትን ሕጻናትን በጎዳና ያሉትን መጠለያ የሌላቸውን የተራቡትን ሁሉ ሁሉን ማድረግ ወደምትችለው መፍትሄ ወዳለህ ፈጣሪያችን አምላካችን አባታችን በጸጋው ዙፋን ስር አመጣናቸው ሁሉን በጊዜው ውብ ስለምታደርግ ሁሉን መልካም በጎ ደስ የምታሰኝ ስለሚሆን ማዳንም አብልጠህ ስለምታደርግ እናመሰግንሀለን:: አሜን!!!

🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏 ✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏 📖 ትንቢተ ሕዝቅኤል 33 11፤ እኔ ሕያው ነኝና ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት ዘንድ አልፈቅድም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ተመለሱ፥ ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ፤ ስለ ምንስ ትሞታላችሁ? በላቸው።

እናመሰግንሀለን በእልልታ በምስጋና በደስታ በሀሴት በመገዛት ወደ ማደሪያህ ወደመገኘትህ እንገባለን:: እናመሰግንሀለን አምላክ ስለሆንክ ጌታ ስለሆንክ ሰማይን ምድርንም በቃልህ የፈጠርክ ሁሉ በአንተ ሆነ ከሆነውም እንክዋን እንዳች ያለአንተ አልሆነም ፍጥረት ሁሉ ያመሰግኑሀል :: ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔር ያመስግን ይለናል:: እኛም ዛሬ በዚህ ምሽት የመኖራችን ዋስትና ከአንተ ሆነልን በአንተ ሰላም እንኖራለን ስምህ ይመስገን እናመስግንሀለን ይገባሀልና ምስጋና እናመሰግንሀለን ለአምላካችን ለአባታችን የሚገባውን ምስጋና እንሰጥሀለን እናመሰግነዋለን ይገባዋልና ምስጋና አምላክ ነውና ጌታ ነውና ንጉስ ነውና ያለና የነበር ለዘለአለም የሚኖር አቻ የሌለው የሁሉ የበላይ በሰማይም በምድርም እሱ ብቻ ሁሉን ማድረግ የሚችል ሁሉን የፈጠረ ሁሉ በእርሱ የሆነ ክብር ለስሙ ይሁን እናመሰግነዋለን እናከብረዋለን በሁሉ ነገራችን እናመልከዋለን እንገዛለታለን አሜን!!! መንፈስህ ምሽታችንን ይቆጣጠር መገኘትህ ይሙላን መንፈስ ቅዱስ ግዛን የማቴዎስ ወንጌል 17 2፤ በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። አሜን ዛሬም ብርሀንህ እንደጽዳል በሀገራችን በኢትዮጵያ በሕዝባችን በቤተክርስቲያናት በቤተሰባችን ሁሉ ላይ ይብራ ይህ የአንተ የሚያበራው የፊትህ ብርሀን በትውልዱ ልብ ላይ ሁሉ ይብራ በእያንዳንዳችን ልብ የህይወትህ ጸዳል ብርሀን በዝቶ ይብራ አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌እየሱስ እንደ አዲስ መስማት እንዲሆንልን ✅ትእዛዙን መስማት መተግበ እንዲሆንልም ፀጋው እንዲበዛልን በህብረት እንፀልያለን 🙏 📖 የማቴዎስ ወንጌል 17 1፤ ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። 2፤ በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። 3፤ እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። 4፤ ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን፡— ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ፡ አለ። 5፤ እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው፡— በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት፡ የሚል ድምፅ መጣ።

ኤፌሶን 2:8 ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ አሜን አሜን አሜን ቅዱስ አባታችን ፀጋህ በእምነት አድኖናልና ከእኛ የሆነ ምንም የለ ከአንተ በሆነልን ስጦታ ሃይላችን አንተ ብርታታችን አንተ ብቃታችን አንተ ሆነህ ያበረታኸንና ያቆምከን ጌታ ተመስገን በሆነልን ሁሉ ወደአንተ መቅረብ ይሁንልን የሚያሰናክሉንንና በአንተ ፊት ነውር የሆነውን ሁሉ አስወግድልን በቃልህ ብቻ ፀንተን የምንቆምበት ሃይልና ፀጋ ይብዛልን በጌታ እየሱስ ክርስቶስ ስም 🙏🏾🙏🏾🙏🏾

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ፀንቶ መቆም ✅ በራሳችን ሀይል እና ብርታት እንዳልቆምን እንድንረዳ ✅ዛሬም እንደሁሌው የእርሱ ፀጋ ብቻ ስለሆነ የኛ ብቃት በትህትና ወደእርሱ ቀርበን ሳንሰናከል እንድንቆም ሊያርገን ወደሚቻለው ወደ እርሱ ፀንተን መቆም እንዲሆንልን ፀጋው እንዲበዛል እስካሁንም ስላቆመን ምስጋጋን ይዘን እንቀርባለን 📖 የይሁዳ መልእክት 1: 24-25 ሳትሰናከሉም እንዲጠብቃችሁ፥ በክብሩም ፊት በደስታ ነውር የሌላችሁ አድርጎ እንዲያቆማችሁ ለሚችለው፥ ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 96 10፤ በአሕዛብ መካከል፡— እግዚአብሔር ነገሠ፡ በሉ። እንዳይናወጥም ዓለሙን እርሱ አጸናው፥ አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል።

መዝሙረ ዳዊት 145 15፤ የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ። 16፤ አንተ እጅህን ትከፍታለህ፥ ሕይወት ላለውም ሁሉ መልካምን ታጠግባለህ። 17፤ እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ ነው በሥራውም ሁሉ ቸር ነው። 18፤ እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፥ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው። 19፤ ለሚፈሩት ምኞታቸውን ያደርጋል፥ ልመናቸውንም ይሰማል ያድናቸዋልም። አምላካችን ሆይ አንተ ቸር ነህ ከአንተ በቀር ቸር አምላክ የለም በስራህ ሁሉ ቸር ነህ ከቸርነትህ የተነሳ ፈጥረኸናል ከአንተ በቀር መሀሪ ይቅርባይ ለልጆቹ የራራ አባት የለም አለቅነት ሁሉ የአንተ ነዉ የሁሉ አይን ልብ አንተን ተስፋ ያደርጋልና እግዚአብሔር ሆይ በዚህ ምሽት ለወገኖቻችን በተለያየ በሽታ የታመሙትን በተለይ ደግሞ በኮረና ቫይረስ የተያዙትን ሁሉ ይዘን የምህረትህን የፈውስህን የማዳንህን በር እናንካካለን: : በታመሙት ላይ እጅህን እንድትዘረጋ እንጠይቅሀለን ቃልህ እንደሚለው እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው ልመናቸውንም ይሰማቸዋል ያድናቸውማል ይላልና እኛም እንደቃልህ እንጠራሀለን በፈውስህ እለፍ የተጨነቁትን ሸክማቸው ህመም የሆነባቸውን ሁሉ በኢየሱስ ስም አድናቸው ድረስላቸው የስጋም የነፍስም ፈውስ ያግኛቸው የእግዚአብሔርን ክንዶች ተነስ በሽታ ከእነሱ ይነቀል ልባቸው በአንተ መንፈስ እረፍት ይሞላ:: ትንቢተ ኢሳይያስ 53 4፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። 5፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ዛሬም ለእኛ ሲል ሕመማችንን የተሸከመው የቆሰለው የደቀቀው የታመመው በቆሰለው የእኛን በደል ሀጢያት በእርሱ ላይ ያኖረው ኢየሱስ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን አሜን ዛሬም ህያው የሆነው የኢየሱስ ስጋ ዛሬም የሚፈውሰው የኢየሱስ ደም በሁሉም ላይ እንጠራለን:: ህይወት ያለው የኢየሱስ ደም ህይወትን አዲስ የምታደርግ የኢየሱስ ደም በሽታ ሁሉ የታጠበ ይሁን ከኢየሱስ ደም የተነሳ በደም ውስጥ ያለ በሽታ ሁሉ ይታጠብ ስጋቸው ሁሉ ከኢየሱስ ህያው ስጋ የተነሳ ስጋቸው ሁሉ ይፈወስ ደምስሮቻቸው መተንፈሻ አካላቸው በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ይፈወስ አተነፋፈሳቸው ሁሉ በመንፈስህ ሀይል ይስተካከል ልባቸው በመንፈስ ቅዱስ ሰላም የተገዛ ይሁን የአንተን ፈዋሽነት አዳኝነት ሁሉን ቻይነት የበላይነት ትልቅነት አብሮነትን እንዲያሰላስሉ ጸጋህን ስጣቸው የአንተ መገኘት ይሰማቸው ሁለንተናቸውን የአንተ መንፈስ ይግዛ:: ስለሰማኸን እናመሰግንሀለን!!!

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ቅዳሜን ስለፈወስ ✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች ✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል 🙏 📖 የያዕቆብ መልእክት 5 14፤ ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። 15፤ የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።

ያዕቆብ 5:14-15 ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። ኤርምያስ 30:17 እኔ ጤናህን እመልስልሃለሁ ቍስልህንም እፈውሳለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ማንም የማይሻት፥ የተጣለች ጽዮን፥ ብለው ጠርተውሻልና። የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል። አሜን አሜን አሜን አባ ተባረክ ተቀደስ ስለቀናችን ተመስገን ምሽታችንንም ስለባረክህልን ተመስገን ክበር ክበር እያልን በህብረት በፊትህ እንቀርባለን በተለያዩ የሱስ እስራት ውስጥ ያሉትን ከአንተ ፍቃድ ውጪ በአጋንንት እሠራር የተያዙትን የምናውቃቸው የማናውቃቸው በአገራችን በዓለማችን ያሉትን የአንተ ፍጥረት ሁሉ እንደቃልህ ጤንነታቸው እንዲመለስላቸው ከደዌያቸው እንድታድናቸው አንተን ብቻ የማመን ፀጋ እንዲበዛላቸው የፈውስ ዘይትህ እንዲፈስላቸው እኛ ልጆችህ በአንድነት በፊትህ እንወድቃለንጩኽታችንን ሰሚ አባታችን ስለስማኸን እናመሰግንሃለን ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን🙏🏾🙏🏾🙏🏾

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 በተለያዩ የሱስ እስራት ውስጥ ስላሉ ወጣቶች ነፃ መውጣት እንዲሆን የእግዚአብሔርን ፀጋ እንዲያገኛቸው በህብረት እንፀልያለን 🙏 📖 ወደ ቲቶ 2 11፤ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤

ትንቢተ ኢሳይያስ 57:15 ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል፡የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ። አሜን ጌታ ሆይ አልፋ እና ኦሜጋ ስምህ ቅዱስ የሆነ በከፍታ ላይ ያለህ ሕያው አምላክ እና አባታችን ክብር ለአንተ ይሁን! ያዘኑትን ታፅናናለህ የታመሙትን ትፈውሳለህ የተሰበረውን እና የተቀጠቀጠውን ልብ ትጠግናለህ የተዋረደውን መንፈስ በከበረ ከፍታህ ታስቀምጣለህ ሁሉን ትችላለህ ሀሳብህ አይከለከልም ሁል ጊዜ አትቆጣም ምህረትህ ሃያል ነው መንገድን ትመራለህ የሚያለቅሱትን እንባ ታብሳለህ አንተ ሰላም ነህ ሰላምን ትሰጠናለህ ቤታችንን ሰፈራችንን መንደራችንን ክልሎቻችንን ከተሞቻችንን አገራችንን ሁሉ በሰላምህ ትሞላለህ የአለም ሰላም ከንቱ ነው የአንተ ሰላም ግን የእውነት ሰላም ነው እረፍት የሆነ ፍቅር የሞላበት በበረከት የተሞላ በሀሴት የታጀበ የእውነት ሰላም !!! ሃሌሉያ ሰላማችን ደስታችን መፅናኛችን መመኪያችን ከፍታችን በረከታችን አንተ ነህ አባ ተመስገን!አባ ተባረክ ! አባ ክበር !!! ሃሌሉያ !!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ስለመፅናናት ✅ በሀዘን ውስጥ ስላሉ ሁሉ የእግዚአብሔርን መንፈስ ባሉበት እንዲያፅናናቸው ወደ ርህራሄ አባት ወደ መፅናናትን ሁሉ አምላክ ፊት እናቀርባቸዋለን 🙏 📖 መዝሙረ ዳዊት 34 17፤ ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው። 18፤ እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።

ጌታ ሆይ አንተ ታላቅ በሀይል ታላቅ ነህ ስምህም ታላቅ ነው ስራህም ታላቅ ነህ ይህ ታላቅነትህ ይህ ንግስናህ ይህ ጌትነትህ ይግዛን ይቆጣጠር ወደንና ፈቅደን ለአንተ ለመንግስትህ ለጌትነትህ ለንግስናህ እራሳችንን እናስገዛለን በአንተ በመገኘትህ መኖር መልካም ነው ያማረ ነው "ገመድ ባማረ ስፍራ ወደቀችልኝ እድሌም ተዋበችልኝ " እንዳለው ቅዱስ ዳዊት እኛም ህይወታችን በአንተ ህይወት ተቀየረ ታሪካችን ተለወጠ ህይወታችን በአንተ አማረልን "ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሀን " አመጣኸን ወደ ልጅህ መንግስት አፈለስከን "በህያውና ለዘለአለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ዳግመንኛ ወለድከን " እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሀለን ክበርልን አሁንም በህይወታችን አንተ ታይልን እናመሰግንሀለን መገኘትህ ይግዛን መንፈስ ቅዱስ በሀይሉ ይሙላን አሜን:: በሰጠኸን ነጻ ህይወት በተከፈለልን ዋጋ እንድኖር ጸጋህን አብዛልን :: አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 እግዚአብሔርን በሁሉ ነገራችን ሁሉ ማምለክ ✅ በስራችን በቤተሰባችን በአገልግሎታችን በህይወታችን ሁሉ እግዚአብሔርን ብቻ እየመረጥን የምናመልክበትን ፀጋ እንዲበዛልን በህብረት እንፀልያለን 🙏 📖 መጽሐፈ ኢያሱ 24 መጽሐፈ ኢያሱ 24 15 የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።

ኢሳይያስ 54 ; 10-15 ተራሮች ይፈልሳሉ፥ ኮረብቶችም ይወገዳሉ፤ ቸርነቴ ግን ከአንቺ ዘንድ አይፈልስም የሰላሜም ቃል ኪዳን አይወገድም፥ ይላል መሐሪሽ እግዚአብሔር። አንቺ የተቸገርሽ በዐውል ነፋስም የተናወጥሽ ያልተጽናናሽም፥ እነሆ፥ ድንጋዮችሽን ሸላልሜ እገነባለሁ፥ በሰንፔርም እመሠርትሻለሁ። የግንብሽንም ጕልላት በቀይ ዕንቍ፥ በሮችሽንም በሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ዳርቻሽንም ሁሉ በከበሩ ድንጋዮች እሠራለሁ። ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል። በጽድቅ ትታነጺያለሽ፤ ከግፍ ራቂ፥ አትፈሪምም፥ ድንጋጤም ወደ አንቺ አትቀርብም። እነሆ፥ ይሰበሰባሉ፥ ነገር ግን ከእኔ ዘንድ አይሆንም፤ በአንቺም ላይ የሚሰበሰቡ ሁሉ ከአንቺ የተነሣ ይወድቃሉ። አሜን አሜን አሜን ሃሌሉያ ጌታ አባታችን ተመስገን ስለውሎአችን ስለምሽታችን ሁሉ ተመስገን መልካም አባት ስላለኸን ሰላማችን ከአንተ መዳናችን ከአንተ እረፍታችን ከአንተ ፈውሳችን ከአንተ የሆነልን ልጆችህ ምህረትና ቸርነትህ ስለበዛልን ሰለመልካምነትህ ከላይ የተባለው ሁሉ ለአገራችን እንደሚሆን በመተማመን እናመሰግንሃለን እናከብርሀለን ንገስ ተወደስ እንላለን አሁንም አብሮነትህ ከእኛ ጋር ሰላለ ጥበቃህን በየእለቱ ሰለበዛህልን በሆነልን ሁሉ አባ አባ ብለን ደግመን ደግመን እንጠራሀለን እናመሰግንሃለን አሁንም አገራችንን ካለባት ጭንቅና መከራ ከአስከፊው በሽታ ሁሉ እንድታድናት ሁሉንም ለታማኝ እጆችህ አስረከብን በጌታ እየሱስ ክርስቶስ ስም 🙏🏾🙏🏾🙏🏾

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 5 11፤ በአንተ የሚታመኑት ሁሉ ግን ደስ ይላቸዋል፤ ለዘላለሙ ደስ ይላቸዋል፥ እነርሱንም ትጠብቃለህ፤ ስምህንም የሚወድዱ ሁሉ በአንተ ይመካሉ። 12፤ አንተ ጻድቁን ትባርከዋለህና፤ አቤቱ፥ እንደ ጋሻ በሞገስ ከለልኸን።