805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 አሮጌው አልፎ ሁሉ አዲስ እንዲሆን
✅በውስጣችን
✅በቤታችን
✅በአከባቢአችን
✅በሀገራችን
...
አሮጌው የክፋት የሀጢአት ዘመን አልፎ በጌታ ክርስቶስ አዲስ እንዲሆን በህብረት እንፀልያለን
📖 2ኛ ቆሮንቶስ 5
17፤ ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለመተከል
✅ ለሁሉነገር መፍትሄ እና መልስ ላለው
✅ወደ እውነት ሁሉ ለሚወስደው እና ህይወት ሰጪ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃልን መሻት , ማንበብ እና እርሱ ላይ መተከል የሚያስችልን ፀጋ እንዲበዛ እንፀልያለን
📖 የማቴዎስ ወንጌል 7
24፤ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል።
25፤ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌የእግዚያብሄር ን ምህረት በምድራችን እንዲወርድ
✅ ሀገራችንን ና አለማችነን ይዘን በአባታችን ፊት እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 69
16፤ አቤቱ፥ ምሕረትህ መልካም ናትና ስማኝ። እንደ ርኅራኄህም ብዛት ወደ እኔ ተመልከት፤
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ከእግዚያብሄር መንፈንስ የሆነ ነፃነት
✅ ከሀጥያት አስራር ነፃ አውጥቶ በአባታችን ላይ ብቻ የሚሳርፍውን የነፃነት መንፈስ
በሰዎች ላይ እንዲመጣ በህብረት እንፀልያለን
📖 2ኛ ቆሮንቶስ 3
17፤ ጌታ ግን መንፈስ ነው፤ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 100
1፤ ምድር ሁሉ፥ ለእግዚአብሔር እልል በሉ፥
2፤ በደስታም ለእግዚአብሔር ተገዙ፥ በሐሤትም ወደ ፊቱ ግቡ።
3፤ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ እወቁ፤ እርሱ ሠራን እኛም አይደለንም፤ እኛስ ሕዝቡ የማሰማርያውም በጎች ነን።
4፤ ወደ ደጆቹ በመገዛት፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፤ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፤
5፤ እግዚአብሔር ቸር፥ ምሕረቱም ለዘላለም፥ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ስለተአምራት
✅ በኛ , በቤተሰቦቻችን , በወዳጆቻችን , በቤተክርስቲያን, በሆስፒታሎች እና በሀገራችን ላይ
ተአምራቱ እንዲገለጥ
✅ ተአምራቱም ከእርሱ ብቻ እንደሆነ ታውቆ ለእርሱ ክብር እንዲሆን
እኛ ልጆቹ በህብረት ለተአምራት እንፀልያለን
📖 ትንቢተ ዳንኤል 6
27፤ ያድናል ይታደግማል፥ በሰማይና በምድርም ተአምራትንና ድንቅን ይሠራል፥ ዳንኤልንም ከአንበሶች አፍ አድኖታል።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ሰለ እምነት
✅ሁሉን አዋቂ,ሁሉን ቻይ ,በሁሉም ቦታ የሚገኝ እና አፍቅሪ አምላክ እንዳለን አውቀን በምንም ሁኔታ ላይ ብንግኝ በእርሱ ላይ እምነታችን ጥለን
✅እርሱን ማስደሰት እንችል ዘንድ መንፈሱ እንዲረዳን እንፀልይለን
📖ወደ ዕብራውያን 11
6፤ ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ከእግዚአብሔር ከሆነው ስለ እውነተኛው ጥበብ
✅ ንፁህ , እርቅን የሚሻ, ገር , የሚታዘዝ
✅ምህረት እና በጎ ፍሬ የሚያፈራውን
✅ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለበትን
ወደ እውነት የሚወስደውን ጥበብ በሁሉም ላይ እንዲሰፍን በእየሱስ ስም እንጠይቃለን
📖 የያዕቆብ መልእክት 3
17፤ ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 በዛሬው ቀን ግንቦት (6/2012 ዓ. ም. )የዓለም ሕዝብ በጸሎት
መተባበርን ጥሪ እኝም እንካፈላለን
በመላው ዓለም የሚገኙ የልዩ ልዩ እምነት ተከታዮች በአንድ መንፈስ ሆነው ግንቦት 6/2012 ዓ. ም. በሚደርግ ዓለም አቀፍ የጸሎት ሥነ ሥርዓት የሚተባበሩ መሆኑ ታውቋል። ሁሉም የሐይማኖት ተቋማት በመተባበር፣ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያስከተለውን መከራ ማለፍ የሚቻልበትን ኃይል ከእግዚአብሔር የሚለምኑ መሆኑን ታውቋል። በዚሁ የጸሎት ሥነ ሥርዓት ላይ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ከአምስቱም አህጉራት ከተወጣጡ የሐይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በጸሎት የሚተባበሩ መሆናቸው ታውቋል።
✅በሕብረት የሚደረግ የጋራ ጸሎት ዋና ዓላማ ዓለማችንን እያጠቃ የሚገኘውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እግዚአብሔር በኃይሉ እንዲያስወግደው በጸሎት የምንጠይቅበት፣ በቀጣዩ ዘመናችንም የወንድማማችነትን እና አብሮ የመኖር መልካም እሴቶቻችንን ለማሳደግ መሆኑ ታውቋል።
📖 መዝሙረ ዳዊት 133
1፤ ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌የኛ እና የክርስቲያኖች ሁሉ ንግግር በጨው የተቀመመ በፀጋ ንዲሆን
✅ ሞት እና ህይወት በምላስ ላይ ስለሆነ(
መጽሐፈ ምሳሌ 18: 21)
✅ በምላሳችን ትንሽ ሆኖ ትልቅ እሳት ሊያመጣ ስለሚችል ( ያዕቆብ 3:6)
በአምላካችን ፊት ቆመን ንግግራችንን ለበጎ ብቻ የምንጠቀምበትን ፀጋ እንዲያበዛልን እንለምነዋለን
📖 ወደ ቆላስይስ 4
6፤ ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌የመንፈሳዊ አይኖች እና ጆሮዎች እንዲከፈቱ
✅ የተጠራንበትን ክብር እንድናወቅ
✅የእግዚአብሄርብን ፍቅር እና ምህረት እንድንረዳ
✅ ከክፋት መንገዶች እንድንመለስ
✅ሌሎችን አምላክ እኛን እንደሚያየን እንድናይ እና እንድንሰማ
አይኖች እና ጆሮዎች እንዲከፈቱ በህብረት እንፀልያለን
መጽሐፈ ምሳሌ 20
12፤ የሚሰማ ጆሮንና የሚያይ ዓይንን፥ ሁለቱን እግዚአብሔር ፈጠራቸው።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 ኦሪት ዘጸአት 15:2
ጕልበቴ ዝማሬዬም እግዚአብሔር ነው፥ መድኃኒቴም ሆነልኝ፤ ይህ አምላኬ ነው አመሰግነውማለሁ፥ የአባቴ አምላክ ነው ከፍ ከፍም አደርገዋለሁ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ስለእናቶች ሁሉ
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ስለእናቶች ሁሉ
✅ በህይወት ላሉ እና ለሌ ሁሉ
ባሉበት ሰላም እንዲሆኑ
✅ እንደ እናት ሆነዉ ላሳደጉን
የእግዚአብሔር መንፈስ በአዲስ መልኩ እንዲነካቸው ለውለታቸው ሁሉ እያመሰገንን በፀሎት በጌታ ፊት እናቀርባቸዋለን
📖 መጽሐፈ ምሳሌ 23
25፤ አባትህና እናትህ ደስ ይበላቸው፥ አንተንም የወለደች ደስ ይበላት።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 በሁሉም ክርስቲያኖች ላይ የህይወት ውሃ ወንዝ ከውስጣቸው እንዲፈልቅ
✅ መፍትሄ ለመሆን
✅በረከት ለመሆን
✅እውነተኛ ደቀመዝሙራን ለመሆን
በክርስቶስ በሚያምኑት ሁሉ ላይ ይህ እንዲሆን እርሱን ለማያውቁ ለተጠሙትም ወደእርሱ መመለስ እንዲሆንላቸው በህብረት እንፀልያለን
📖 የዮሐንስ ወንጌል 7
38፤ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል፡ ብሎ ጮኸ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 በሀገራችን ያለውን በሽታ እና የተለያዩ የጠላት ስራዎችን መቃወም
በተሰጠን የልጅነት ስልጣን በህብረት ሆነን የጠላትን ስራ እናፈርሳል ከእግዚአብሔር የሆነውን እናውጃለን
📖 ትንቢተ ኢሳይያስ 54
17፤ በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም፤ በፍርድም በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ። የእግዚአብሔር ባሪያዎች ርስት ይህ ነው፥ ጽድቃቸውም ከእኔ ዘንድ ነው፥ ይላል እግዚአብሔር።
📌 በተለያዩ መከራ ውስጥ እያለፉ ላሉ ሰዎች
✅ ካሉበት መከራ እግዚአብሔር በፍጥነት እንዲያወጣቸው
✅ በመከራቸው ውስጥ ትእግስትን እና ተስፋን እንዲያገኙ
በጌታ ፊት በህብረት እናቀርባቸዋለን
📖 ወደ ሮሜ 5
3-4፤ ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን መከራ ትዕግሥትን እንዲያደርግ፥ ትዕግሥትም ፈተናን ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን፥ በመከራችን ደግሞ እንመካለን፤
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ፍፁም ፍቅር ልቦችን እንዲገዛ
✅ፍርሃት ከሰዎች እንዲርቅ
✅ ከፍፁም ፍቅር የወጣ አገልግሎት እንዲሰፍን
ፍቅር የሆነውን ጌታ ወደ እኛ እና ወደ ሰዎች ልብ እጋብዘዋለን
📖1ኛ ዮሐንስ 4
18፤ ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 118
28፤ አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ክርስቲያኖች ሁሉ የምድር ጨው እንዲሆኑ
✅ የሰዎችን ህይወት እንድናጣፍጥ
✅ መፍትሄ ሰጪዎች እንድንሆን
እግዚያብሄርም ለዚህ ጥሪያችን የሚያበቃ ፀጋን እንዲሰጠን በእየሱስ ስም እንፀልያለን
📖 የማቴዎስ ወንጌል 5
13፤ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።
“ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?”
— ያዕቆብ 2፥14
ወጥ በጨው እንደሚጣፍጥ ክርሰትናም በተግባራዊ ሕይወት ይጣፍጣል ይህ ግዜ ደግሞ በተግባራዊ ክርስትና እንድንገለጥ እድል ሰጥቶናል በእድሉ እንጠቀም ።
በቤታችን ያሉ ትርፍ #ልብሶችን እንለግስና የበረዳቸውን እናሙቃቸው።
የልብስ ልግስና ተጀምሯል ጌታ ይባረክ የማያሳፍር የታመኑበትን የሚታመን ጌታ አለን ኢየሱስ ስምህ ይባረክ!!!
