805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
#በመንፈስ_ቅዱስ_ያለ_ሕይወት
አንድ ስው በመንፈስ ቅዱስ ያለ ሕይወት ሲኖረው እንዚህ ምልክቶች ይታዩበታል።
1 የፅድቅ ስራ (1ዮሐ 2:29)
2 በኃጢአት መኖር ማቆም (1ዮሐ 3:9)
3 እውነተኛ ፍቅር (1ዮሐ 4:7)
4 ትእዛዙን መጠበቅ ( 1ዮሐ 5 :1-3)
5 አለማዊነትን የማሸነፍ ጉልበት (1ዮሐ 5:4)
6 ክርስቶስን መውደድ (ዮሐ 8:42)
7 የእግዚአብሔር ቃል ረሀብ (1ጴጥ 2:2)
8 የማይሰለች የፀሎት ሕይወት (ሮሜ 8:26)
አንድ ሰው #ከመንፈስ_ቅዱስ ከተቀበለው ሕይወት ሲጎድል ቀስ በቀስ ብዙ ነገር በማጣት እነዚህ ምልክቶች ይታዩበታል።
1 ለእግዚአብሔር ቃል መታዘዝ እየቀነስ መሄድ #ለቃሉ_ጉጉት_ማጣት (መዝ 51:12)
2 መንፈሳዊነትን በማያሳድግ ስፍራ መገኘት (ማቴ 24:12)
3 ለሰዎች እንቅፋት የሚሆንን ነገር #በግድየለሽነት ማድረግ ። (ሮሜ 14:15)
4 አለምን የመውደድ ዝንባሌ ማሳየት #የዓለም_ፍቅር (1ዮሐ :15)
5 ለፀሎት ያለ ፍላጎት ማጣት
እነዚህና እነዚህን የመሳሰሉ ብዙ ምልክቶችን በሕይወታችን ስናይ። #መንፈሰ_ቅዱስን ልንፈልግ ይገባናል። መንፈስ ቅዱስ ሁሉን የሚያስተካክል ኃይል አለው። #በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት_ያስፈልገናል። ያለበለዚያ ልማዳዊ ክርስትና ነው የምናከናውነው።
@eccrm
@eccrm
#በመንፈሳዊ_ሕይወት_ማደግ
“ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ #እንደግ፤”
— ኤፌሶን 4፥15
✅ #እድገት የማያቋርጥ የሕይወታችን ሂደት ነው። ነገር ግን በምን እያደግን ነው በክፉ ወይስ በመልካም? ሰው ላያውቀው ላይረዳው ይችላል እንጂ ወይ በክፉ ወይም ደግሞ በመልካም እያደገ ነው። ሕይወት ያለው ገገር ሁሉ ከእድገት ውጪ ሊሆን ሰለማይችል። ክፉም ሆነ መልካም እድገቱ እድል አግኝቶ ሲገለጥ የትኛውን ጉዞ እየተጓዘ እንደነበረ ያስታውቃል።
✅ እግዚአብሔር አባት መልካም አባት ስለሆነ ሁልግዜ ከልጆቹ መልካም እድገት ይጠብቃል። እግዚአብሔር ለእድገት የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ #በቃሉ_እና_በመንፈሱ ውስጥ አቅርቦልናል። አሁን እግዚአብሔርን ሳይሆን የምንጠብቀው እግዚአብሔር ነው እኛን የሚጠብቀው ለምን ለእድገት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ስለሰጠን።
“የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3
✅ አሁን የተሰጠን ነገር ስለሆነ የተሰጠንን ተጠቅመን እንድናድግ ይጠበቅብናል። አንዳንድ ሰው ለማደግ የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ ይላል ይህ ትክክል አይደለም የስንፍና ቋንቋ ነው። እግዚአብሔር እንድናድግ ስለፈለገ ነው ለእድገት የሚያስፈልገውን ሁሉ የሰጠን ስለዚህ እግዚአብሔር ፈቅዷል ማለት ነው። #አሁን_እድገት_በእኛ_ምርጫ_ላይ_የተወሰነ_ነው። ላለማደጋችን ምንም አይነት ምክንያት ልናቀርብ አይገባንም። #ኃላፊነቱ_የእኛ_ነው።
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
— ሮሜ 12፥2
#ለእድገት_አስፈላጊ_ነገሮች
1 ለቃሉ የሚገባውን ትኩረት መስጠት ቃሉን ማጥናት
2 የየዕለት በመንፈስ የሆነ የፀሎት ሕይወት
3 ውሳኔ እና ቁርጥ ፈቃድ ማድረግ
#የቱጋር_እንዳለን_ራሳችንን_እንመርምር
🙏🙏🙏
@eccrm
@eccrm
#በመንፈሳዊ_ሕይወት_ማደግ
“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
— ሆሴዕ 4፥6
👉እግዚአብሔር እርሱ ያለውን ነገር ሁሉ እኛ እንድናውቅ ይፈልጋል። ለዚህም ነው ቃሉን የሰጠን በቃሉ ወስጥ እርሱን እናገኛለን። የእግዚአብሔርን ቃል ብናውቅ እና ብናደርገው ከስህተት እና ከውድቀት ሕይወት እንድናለን። #አንድ_ሰው_አወቀ_የሚባለው_ያወቀውን_እውቀት_በትክክል_ሲጠቀምበት_ነው። አዳም ያወቀውን እውቀት አለመጠቀሙ ነው ውድቀት ውስጥ የከተተው እንጂ እግዚአብሔር አስቀድሞ ምን ውስጥ ሕይወት እና ሞት እንዳለ አሳውቆት ነበር። ኢየሱስም በሰይጣን ተፈትኗል ነገር ግን እውቀቱን ተጠቅሞ ፈተናውን አሸነፈ። (ማቴ 4:4 ) አንተም በቃሉ ማሸነፍ ትችላለህ
👉 ለሰይጣን ትልቁ መጠቀሚያ መሳሪያ አለማወቃችን ነው ባለማወቃችን ይገለጥብናል። ስለዚህ ሰይጣንን አለማጥፋት ባንችል አለማወቃችንን ግን ማጥፋት እንችላለን። በሁሉ አቅጣጫ እግዚአብሔር በነገረን ቃል ማወቅ ብንችል ማደግ ይሆንልናል። #ማደጋችን ደግሞ የሰይጣንን በሮች ሁሉ እንዘጋለን። #ስለዚህ_ክርስትና_በእግዚአብሔር_ቃል_በማደግ_ውስጥ_ያለ_አስደሳች_ሕይወት_ነው።
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
በምን አቅጣጫ እያደግን ነው ራሳችንን እንጠይቅ?
አሁን የከበዱን ነገሮች በማደግ መፍትሔ ያገኛሉ።
#የተባረከ_ቀን 🙏🙏🙏
@eccrm
@eccrm
#በመንፈሳዊ_ሕይወት_ማደግ
“ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ #ጸጋና_እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 3፥18
👉 እድገት የሌለው ነገር ሁልግዜ #ፍሬ የለውም የማያድግ ሰው ሁልግዜም ህፃን ነው። የማያድግ ወይም ደግሞ ህፃን የሆነ ያልበሰለ ሰው ሁሌም የሚጎዳውን ነገር ሲያደርግ ይኖራል። መንፈሳዊ እድገት በእድሜ ቁጥር ብዛት አይመጣም። መንፈሳዊ እድገት ከእግዚአብሔር ቃልና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የምናደርገው ሕብረት ውጤት ነው። አብዛኛው በሕይወታችን ውስጥ ያሉ ችግሮች ሰዎች ወይም ደግሞ ሁኔታዎች ያመጡብን ሳይሆን እኛ ባለማደግ ወይም ደግሞ በቸልተኝነታችን የመጣብን ነው።
ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል።
²⁵ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።
²⁶ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል።
²⁷ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ።
👉 ለሁለቱም የመጣው #ፈተና ተመሳሳይ ነው ነገር ግን #ውጤቱ የተለያየው የተመሰረቱበት የተሰሩበት ሁኔታ ነው። ስለዚህ ማንኛውም ችግር ያንተን እድገት ነው የሚፈትነው። ስለዚህ ዛሬ ራስህን ጠይቅ ምን ላይ ተመስርቻለው አሁን ምንድነው ፋርሀቴ ምንድነው ስጋቴ ብለን እንጠይቅ? አንዱ የእድገት መንገድ ራስን መመርመር ነው። ራስህን የቱጋር ታገኘዋለህ። #አለማደግን የምናጠፋበት መንገድ በማደግ ብቻ ነው። ሌላ መንገድ የለውም።
#ለመንፈሳዊ_እድገትህ_ይጠቅሙሀል_እና_ራስህን_እነዚህን_ጥያቄዎች_ጠይቅ።
1 #ለእግዚአብሔር_ቃል በቀን ምን ያህል ግዜ ሰጥተሀል?
2 በቀን ምን ያህል ሰዓት #የፀሎት_ግዜ_አለህ?
3 ረጅም ግዜህን የምታጠፋበት ግዜ ከስራ ወይም ደግሞ ከትምህርት ውጭ ያለው ሰዓት መንፈሳዊነቴን የሚያሳድግ ነው ብለህ ታስባለህ?
4 ረጅም ግዜህን ከምን አይነት ሰዎች ጋር ታሳልፍለህ? ለመንፈሳዊ እድገትህ ይጠቅማሉ ? ካልሆነ ይሉኝታ አይያዝህ ለመለየት ሞክር መፅሐፍ ቅዱስ ከአሮጊቶች ከሚመስል እርባና ቢስ ወሬ ራቅ ብሎ ይመክራል።
5 #ሶሻል_ሚዲያ_አጠቃቀምህ ምን ይመስላል? ሰሜትህን የሚገዛ ወይስ መንፈሳዊነትህን የሚያሳድግ? መልሱ ቀላል ነው። #_ለራስህ_ታማኝ_ሁን።
ስለዚህ አነኚህ ጥያቄዎች ለራስህ ጠይቅና እግዚአብሔር ያዘጋጀልህን #መልካም_እና_አስደሳች ሕይወት መኖር ትችላለህ። ያለበለዚያ ግን አረፋት የሌለው የተቅበዘበዘ ልማዳዊ ቤተክርስቲያን ተመላላሽ ሰው ትሆናለህ። #ንቃ #ንቃ #ንቃ ሕይወት ከክርስቶስ ጋር በጣም አስደሳች እና ቀላል ነው።
#ስለራስህ_ሕይወት_ራስህ_ሀላፊነት_ውሰድ።
🙏🙏🙏
@eccrm @eccrm
@eccrm @eccrm
የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች በቀጣይ ሳምንት እሁድ 25/04/13 ጀምሮ ፕሮግራም የምናደረግበት ቦታ ጎተራ በሚገኘው #ዶንቦስኮ_የፀሎት_ቤት ይሆናል። ላልሰሙ በመንገር እንድትተባበሩን በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን። ፕሮግራም የሚጀምረው 9:00 ሲሆን
ለሰሚናር ተማሪዎች 7:30 ይጀምራል።
ውስጣዊ ንስሐ
🙏 እንድንለወጥ እና #ንስሐ እንድንገባ የቀረበው የኢየሱስ ጥሪ ከእርሱ በፊት እንደነበሩት ነቢያት ጥሪ በመጀመሪያ ደረጃ ማቅ በመልበስ አመድ በመነስነስ እንዲሁም በጾምና ተጋድሎ ላይ የሚያተኩር ውጫዊ ሳይሆን ልባዊ ወይም ውስጣዊ መለወጥን የሚጠይቅ ነው። ያለዚህ ንስሐ ፍሬ ቢስና ከንቱ ይሆናል ይሁን እንጂ ውስጣዊ መለወጥ ገሀድ በሆኑ ምልክቶች እንቅስቃሴዎችና #የንስሐ ስራ መገለጽ ያሻዋል።
“ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ።”
🙏 ውስጣዊ ንስሐ የመላ ሕይወታችን ስርነቀል ለውጥ ፣ ፀፀት በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር መመለስ የኃጢአት ማክተሚያ የፈፀምናቸውን መጥፎ ተግባራት በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው። ይህ ሁኔታ በእግዚአብሔር ምህረት ተስፋ በማድረግ እና በፀጋው ድጋፍ በመተማመን ሕይወትን #የመለወጥ_ምኞትና ውሳኔ ያስከትላል።
“የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።”
— መዝሙር 51፥17
“በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።”
— መዝሙር 51፥7
@eccrm
@eccrm
#በአዲስ_ፍጥረት_መኖር
“እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።— ዮሐንስ 17፥3
#ውስጣዊ_ጥንካሬህ_የውጫዊ_ማንነትህ_መሰረት_ነው ።
በክርስቶስ ማን መሆናችንን ማወቃችን ዋና ነገር ነው። ባወቅነው ነገር ማደጋችን ሌላኛው ዋና ጉዳይ ነው። #ያልሆነውን_በመልቀቅ_ናችሁ_የተባልነውን_አጥብቆ_በመያዝ_የአሸናፊዎች_ሕይወት_ልንኖር_ይገባል። ታዲያ በክርስቶስ ናችሁ የተባልነው ምንድን ነው?
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።”— 2ኛ ቆሮ 5፥17
✍ እኛ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ነን የተባልን ሰዎች ነን። #ይህን_እውነት_የሚነግረን_ደግሞ_የእግዚአብሔር_ቃል_ነው። ይህ ቃል ደግሞ የታመነ ነው። ስለዚህ ለዚህ እውነት ልንገዛ ይገባናል። አሮጌውን ሰው እና ሀጢአትን ለማጥፍት በኢየሱስ ስም እያሉ መታገል አያስፈልግም። ማድረግ የሚጠበቅብን የአዲሱን ፍጥረት ኑሮ ምልልስ መከተል ነው። #አዲሱ_ፍጥረት_የሚፈልገውን_መፈፀም_ነው። የብዙ ሰው ችግር በአሮጌው ሰው መመላለሱ ነው። ይሄ ነው እንግዲህ ያልሆነውን መኖር ማለት። ስለዚህ የአዲሱን ሰው ሕይወት ለመኖር ምን ይጠበቅብናል?
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
✍ ለቃሉ የሚገባውን ክብር እንስጥ አዲሱ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ይፈልጋል። አዲሱ ሰው ቃሉን እየተመገበ ያድጋል። #ሰውነታችንን_በሕይወት_የሚያቆየው_ምግብ_እንደሆነ_ሁሉ_አዲሱ_ሰው_ሕይወቱን_የሚቀጥለው_በእግዚአብሔር_ቃል_ነው። ስለዚህ ቃሉን ልንመግበው ይገባል። ኢየሱስም ለዚህ ነው ይህን ቃል የተናገረው
“እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።”— ማቴዎስ 4፥4
✍ ወንድሜ ያለ እግዚአብሔር ቃል እየኖርክ ከሆነ ምንም ክርስቲያን ብትሆን አሮጌው ሰው ነው የሚገለጥብህ ይህ ማለት የስጋ ስራ ማለት ነው። ስለዚህ ይህን ተረድተን #ቃሉን_በመመገብ_የአዲሱን_ሰው_ሕይወት_ማስቀጠል_አለብን። እንደ ቃሉ መኖር እንድንችል ጌታ ፀጋውን ያብዛልን።
#ይቀጥላል
#የተባረከ_በአዲሱ_ሰው የምንመላለስበት ቀን ያድርግልን!!!
@eccrm
@eccrm
“የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤”
— ቆላስይስ 3፥16
ክርስቲያን ሁልግዜ በእውነተኛ ደስታ እና አእምሮን በሚያልፍ ሰላም መኖር የሚችለው ከቃሉ ጋር የተጣበቀ ሕይወት ሲኖረው ብቻ ነው። እግዚአብሔር ቃሉን ሲሰጠን ራሱን ነው የሰጠን።
“በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” — ዮሐንስ 1፥1
ቃሉን ስንፈልግ እግዚአብሔርን እንፈልጋለን ማለት ነው። እርሱን ስናገኝ ሁሉ ነገር ሙሉ ይሆንልናል። የእግዚአብሔር ቃል የሕይወታችን መመሪያ ልናደርገው ይገባል። #ቃሉ_የምድርን_ነገር_አስረስቶ_በሰማያዊ_ክብር_የሚያኖረን_መሳሪያችን_ነው። የእግዚአብሔር ቃል ያለው ሁሉ ነገር አለው።
አዋጅ
#ቃልህን በየእለቱ እመገባለው
#ቃልህ ፈውሴ ነው
#ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሀን ነው።
#በቃልህ በየዕለቱ እታደሳለው
#ቃልህ ትዝታዬ ይሁን
#በኢየሱስ_ስም!!!
👇👇👇👇👇👇
@eccrm
@eccrm
#እግዚአብሔር_ስላጸደቀን_ማንም_ሊኮንነን_አይገባም
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ እንግዲህ ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? #እግዚአብሔር_ከእኛ_ጋር_ከሆነ ማን ይቃወመናል?
³² ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም?
³³ #እግዚአብሔር_የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው?
³⁴ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ #ስለ_እኛ_የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።
✍ ቃሉ በግልጽ እንደሚያስተምረን በሞተልን #በክርስቶስ_በመጽደቃችን_ሊፈረድብን_እንደማይገባ_ነው። ምክንያቱም ኩነኔ የማይኖርብን ከእግዚአብሔር ዕቅድ ስለምንካፈል ሕግ ሊኮንነን ስለማይችል ነው። ስጋን አሸንፈን ለእግዚአብሔር እንድንኖር #የእግዚአብሔር_መንፈስ_ስላለን_እዳ_የለብንም የተባረከ ተስፋችን በሆነው በክርስቶስ መመለስ የእግዚአብሔር ክብር እንካፈላለን። የእግዚአብሔር ፍቅር ስለምንለማመድ ከፍቅሩ የሚለየን የለም። (ሮሜ 8:35) የክስ ትልቁ ስራ ፍርድ በተከሳሽ ላይ ቀጥሎም ቅጣት እንዲፈጸም ነው። ቅጣቱ ለዘለዓለም ከፈጣሪው መለየት ነው። ሆኖም ግን ክርሰቲያን ከፈጣሪ ተለይቶ ለዘላለም እንደማይኖር ሐዋርያው ጳውሎስ ከፈጣሪ አብሮነት ከክርስቶስ ስለእኛ መሞት አምላካችን እኛን በማጽደቁ እና በክርስቶስ ስራ ምክንያት እኛ ከፈጣሪ #ልንለይና_ሊፈረድብን_እንደማንችል ያስረዳል።
✍ እግዚአብሔር ለወፍች እና ለሜዳ ሳር አበቦች ግድ ካለው #ለእኛማ_የበለጠ_እንዴት_ግድ_አይለው እግዚአብሔር የእርሱ ከሆኑት ጋር ያለው ተዛምዶ ሕግን የተመረኮዘ ሳይሆነ #በቀራኒዮ_ጸጋው_ላይ_የተመሰረተ_ነው። እግዚአብሔር የራሱ ለሆኑት ሁሉ ሁሉን በነጻ ይሰጣል።
✍ እኛ በክርስቶስ የተመረጥን #በክርስቶስ_ተቀባይነት_ያገኘን_የእግዚአብሔር_ምርጦች_ነን። እርሱ ራሱ ስላጸደቀን እግዚአብሔር እኛን አይከሰንም። እርሱ የሚከሰን ከሆነ የሰጠን ደኅንነት ዋጋ ቢስ ሆነ ማለት ነው። እኛ ራሳችንን እንከስ ይሆናል ሰዎችም ሊከሱን ይችላሉ። እግዚአብሔር ግን በፍጹም ሊከሰን አይችልም #የልጁን_የኢየሱስ_ክርስቶም_ደም_ዋጋ_ያውቃል።
✍ ክርስትና ለተረዳው #የእረፍት_ስፍራ_ነው
#የደስታ_ሀሴት_የምናደረግበት_ሕይወት_ነው
#የጽድቅ_የቅድስና_መገኛ_ነው
ስለዚህ ይህን እውነት ተረድተን እግዚአብሔር በመረጠልን በሰማያዊ ስፍራ ከክርስቶስ ጋር በቃሉ እና በመንፈሱ ውስጥ በህልውናው ውስጥ ደስ ብሎን ተደላድለን ልንኖር ይገባል።
#ሰላም_ለኢትዮጵያ በኢየሱስ ስም!!!❤❤❤
