805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ድንበርን ስለሚጠብቁ እና ለሀገር ደህነት ለቆሙ ሰራዊቶች እና ቤተሰባቸውም
✅ሁሉንም ይዘን በፀሎት ሁሉን ቻይ ወደ ሆነው ወደ እግዚአብሔር አባታችን እናቀርባቸውለን 🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 20
1፤ በመከራ ቀን እግዚአብሔር ይስማህ፤ የያዕቆብ አምላክ ስም ያቁምህ። 2፤ ከመቅደሱ ረድኤትን ይላክልህ፥ ከጽዮንም ያጥናህ።
መዝሙረ ዳዊት 127
3፤ እነሆ፥ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፥ የሆድም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።
እግዚአብሔር ሆይ ስለሰጠኸን ነጻ ስጦታ ልጆቻችን እናመሰግንሀለን:: በዚህ ምድር ስንኖር በአደራ የሰጠኸን ናቸውና የአንተው ናቸውና መልሰን ለአንተ ለታመኑት እጆችህ እንድታሳድጋቸው ሰጠንህ ስለተረከብከን እናመሰግንሀለን አሜን!!!
1ኛ ሳሙኤል 1
28፤ እኔም ደግሞ ለእግዚአብሔር ሰጥቼዋለሁ፤ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ይሆናል።
አሜን እኛም እንደሳሙኤል እግዚአብሔር አባት ሆይ አንተ በነጻ የሰጠኸንን ልጆቻችንን ያንተው ናቸውና ከልጅነት እስከእውቀት ለአንተ አስረከብን አዲስ የተወለዱ ልጆቻችንን አለም ሳያያቸው ለአንተ አስገዛናቸው:: በእድሜያቸው ዘመን አንተን እንዲያከሩ የአንተ ብርሀን በእነሱ ላይ እንዲበራ አንተን እንዲያመሰግኑ በፍቅርህ እንዲያድጉ
በአንተ ጥበብ በአንተ እውቀት አንተን በማክበር አንተን በማወቅ እንዲያድጉ በአካልም በመጠንም አሳድገህ መልካም ፍሬ እንዲያፈሩ ለታመኑት እጆችን ላይ አስቀመጥናቸው::
ወደ ዕብራውያን 1
9፤ ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ፥ ይላል።
እግዚአብሔር አባት ሆይ ልጆቻችን አንተን እንዲፈሩ ከሀጢያት እንዲርቁ ጽድቅን እንዲወዱ ከክፋት ከተንኮል ከሀጢያት ሁሉ እንዲርቁ በሰላምና በደስታ አንተን በማክበር እንዲያድጉ በኢየሱስ ስም ጸለይን!!!
ወደ ኤፌሶን 6
18፤ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤
እግዚአብሔር አባት ሆይ ሁል ጊዜ ስለልጆቻችን ወደ አንተ እንጸልያለን መንገድን የምታቀና ህይወትን የምታሳምር የምትባርክ አንተ ነህና የልጆቻችንን ነጋቸው የተዋጀ ይሁን በአንተ ፍቅር ባርካቸው የፍቅር ልጆች እንዲሆኑ ፍቅርህ በልባቸው ይፍሰስ የሚያስተውሉበት ጸጋ ክፉን ከመልካም የሚለዩበት የአንተ ጸጋ ስጣቸው በእምነት እንዲያድጉ መልካም ህይወት በአንተ ፊት ያማረ ህይወት እንዲሆንላቸው ታማኝ ልጆች እንዲሆኑ አንተን እንዲያገለግሉ ወላጆቻቸውን እንዲያገለግሉ ለሀገር ለወገን መልካም ስራ እንዲሰሩ አይምሮአቸውን በጥበብህ ባርክ አስተሳሰባቸው ባርክ አካሄዳቸውን ሁሉ አንተ ተቆጣጠር በአንተ እግር ስር ይደጉ በእግሮችህ ስር አስቀመጥናቸው ለአንተ በመገዛት እንዲኖሩ ማስተዋልን አብዛላቸው በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን!!! ክብርም ምስጋናም አምልኮም ለአንተ ይሁን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌የእግዚያብሄር ስጦታዎች ስለሆኑት ስለ ልጆች
📖 መዝሙረ ዳዊት 127
3፤ እነሆ፥ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፥ የሆድም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።
መዝሙረ ዳዊት 118
28፤ አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ። 29፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ቸር ነውና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ናትና።
እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሀለን አምላካችን ነህ እናመሰግንሀለን እምላካችን ነህ ከፍ ከፍ እናደርግሀለን ጌታችን አባታችን ንጉሳችን አዳኛችን ታዳጊያችን ጠባቂያችን ከለላችን መኖሪያችን ገዥያችን መንግስታችን ነህና እናመሰግንሀለን እናከብርሀለን ከፍ ከፍ እናደርግሀለን:: ሀሌሉያ!!!
በሁኔታዎች ሁሉ እግዚአብሔር ጋርዶናል በቀን ፀሀይ አያቃጥለኝም በሌሊት ጨረቃም በሁሉ እግዚአብሔር ይጠብቀኛል በሽታ ከሞት ይጋርደናል ከችግር ከስቃይ ይጠብቀናል ጥንቃቂያችን አይደለም ያቆመን ጠባቂያችን ስለማይተኛ ነው እግዚአብሔር መውጣትና መግባትህን ሁሉ ይጠብቃል ስለዚህ ዋስትናችን የህይወታችን ዋስትና የህይወታችን መሪ እግዚአብሔር ነው. በእኛ ህይወት ሀላፊ እግዚአብሔር ነው የሚጠብቅ የሚንከባከብ እግዚአብሔር ነው ሰርተን አመጣነው አንልም በረከታችን እግዚአብሔር ነው ያከናወነልን ቸር ነቱ ጠብቆናል ምህረቱ አቁሞናል ስለአመቱ 2012 እናመሰግነዋለን::
የክብሩ ባለቤት የጊዜ ባለቤት የዘመን ባለቤት እግዚአብሔር አንተ ነህ:: እስከ ዛሬ 355 ቀናትና ሰአት በተለያዩ ነገሮች ውጣ ውረድ ሀገራችንንም እኛና የእኛ የሆኑትን ሁሉ ቤተሰቦቻችንን ልጆቻችንን ወገኖቻችንን ከምናውቀው ከማናውቀው መድሀኒት ካልተገኘለት ደዌ ሁሉ ሰውረህ በኢየሱስ ደም ጋርደህ እስከዛሬዋ ቀን በእንክብካቤ ቅጥርህ ቀጥረህ በሰላም በደስታ በእረፍት በመከናወን ስላደረስከን ተመስገን ተመስገን ተመስገን አሁንም ሁሌም ተመስገን እንልሀለን::
በቤታችን እግዚአብሔር ስላደረገው ቸርነት ስለልጆቻችን ያደረገው ቸርነት ስለ ሀገራችን ስላደረገው ምህረት እናመሰግንሀለን::
በተለይ ደግሞ በዚህ ስድስት ወራት ውስጥ ሀገራችንን ከመጥፋት ከእልቂት ከጠላት ሀሳብ ስላሳለፍከን እንደጠላት ሀሳብ ስላልሆነ እናመሰግንሀለን:: በምህረትህና በቸርነትህ አንተ ይዘኸን በዚሁሉ ተሸክመኸን ከእኛ ጋር በመግ ጋዝ ለዚህ አድርሰኸናልና በልጅህ በኢየሱስ ስም እጅግ እናመሰግንሀለን እናመሰግንሀለን እናመሰግንሀለን ክብር ለአንተ ምስጋና ለአንተ ይሁን አምልኮም ስግደትም ከዘለአለም እስከዘለአለም ለአንተ ይሁን አሜን!!!
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 73
28፤ ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።
መዝሙረ ዳዊት 36:7
አቤቱ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ! የሰው ልጆች በክንፎችህ ጥላ ይታመናሉ
ቅዱስ እና ሃያል አባታችን ሆይ እናመሰግንሃለን ከምህረትህ የተነሳ እለተ ሰንበታችንን ባርከህ ፀጋህ በዝቶልን በብዙ ምስጋና ልናመልክህ እፊትህ ቀርበናል!
ቀጣዩን ሳምንት ደግሞ በኢየሱስ ደም እንዋጀዋለን አገራችንን ህዝቦቿን እኛንም የእኛ የሆኑትንም ቤተክርስቲያናትን ካህናትን አገልጋዮችን መሪዎቻችንን ሁሉ በጥበቃህ ጥላ ስር እንድትሸሽገን በልጅህ ደም እንድትሸፍነን ሰላምህን እንድታበዛልን ፀጋህ እንዲከልለን ለታመኑት እጆችህ ይዘን ቀረብን !
ሳምንቱን ሁሉ ደግሞ አንተን እያከበርን አንተን እያነገስን ክብርህን ሞገስህን ተቀዳጅተን ወደ አዲስ ዘመን በሙሉ ደስታ በሙሉ ክብር በሙሉ ሰላም የምንሻገርበት የድል ሳምንት እንዲሆንልን በጌታ በኢየሱስ ስም እንለምንሃለን ስለሰማኸን እናመሰግንሃለን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌 ስለ እግዚአብሔር ጥበቃ
✅እስከ አሁን ሰአት የጠበቀንን እግዚአብሔርን አመስግነን ለሚመጣው ሳምንት ሁሉ ደግሞ ጥበቃው
- እኛ እና የኛ የሆኑት ላይ
-ቤተክርስቲያናችን እና አገልጋዮች
-አገራችን ላይ
እንዳይለየን እንፀልያለን
📖መዝሙረ ዳዊት 17
8፤ እንደ ዓይን ብሌን ጠብቀኝ፥ በክንፎችህ ጥላ ሰውረኝ፥
መዝሙረ ዳዊት 3:8
ማዳን የእግዚአብሔር ነው በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።
አዳኛችን ፈዋሻችን መድህናችን ኢየሱስ ሆይ በተለያዪ በሽታዎች ተይዘው እየተሰቃዩ ያሉትን ወገኖቻችንን በፊትህ ይዘን ቀረብን በተለይም በኮረና ወረርሽኝ ተይዘው በየሆስፒታሉ በየቤቱ በህመም እየተሰቃዩ ያሉትን ሁሉ በፈውስ ጣትህ ትዳብሳቸው ዘንድ ለታመኑት እጆችህ ይዘን ቀርበናል ለሀኪሞች ለሳይንቲስቶች ግራ ያጋባው ይህን ወረርሺኝ ለአንተ እጅግ ቀላል ነውና ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም ተብሎ እንደተፃፈ ጌታ ሆይ ቃልህን ብቻ አውጣ ተናገር ፈውስም ይሆናል በተለይ ከአገራችን ይህንን በሽታ ፈፅሞ አጥፋልን እኛንም ልጆችህን ከፈራነው ከሰጋነው ነገር ሁሉ አስመልጠን !
ክብርህ በኢትዮጵያ ላይ በሃይል ይገለጥ ! የነነዌ ህዝቦችን በምህረትህ እንደጎበኘሃቸው ኢትዮጵያም እጆቿን ወደ አንተ ዘርግታለች እና በምህረትህ ጎብኛት ህዝቧም ህዝቦችህ እርስቷም እርስቶችህ ነንና ህዝብህን አድነን እርስትህን ከክፉ ታደገን ባርከን ፍቅርህ ምህረትህ ፈውስህ ምድራችንን ይሙላት!!!
በጌታ በኢየሱስ ስም !!!
Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ቅዳሜን ስለፈወስ
✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች
✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች
ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል 🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 145
18፤ እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፥ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው። 19፤ ለሚፈሩት ምኞታቸውን ያደርጋል፥ ልመናቸውንም ይሰማል ያድናቸዋልም።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌 ልባችንን የክርስቶስ ሰላም እንዲገዛው
✅ በተለያዩ ሀሳቦች የተያዘውን ልባቻችን ነፃ ወጥቶ በክርስቶስ ሰላም ብቻ እንዲሞላ እንፀልያል
📖 ወደ ቆላስይስ 3
15፤ በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏
📖 ትንቢተ ኢሳይያስ 55
6፤ እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥ ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤ 7፤ ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።
Thank you for your amazing power and work in our lives, thank you for your goodness and for your blessings over us. Thank you that you are Able to bring hope through even the toughest of times, strengthening us for your purposes. Thank you for your great love and care. Thank you for your mercy and grace. Thank you that you are always with us and will never leave us. Thank you for your incredible sacrifice so that we might have freedom and life. Forgive us for when we don't thank you enough, for who you are, for all that you do, for all that you've given. Help us to set our eyes and our hearts on you afresh. Renew our spirits, fill us with your peace and joy. We love you and we need you, this day and every day. We give you praise and thanks, for You alone are worthy!
In Jesus Name Amen🙏🏻🙏🏻🙏🏻
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌 ስለተመለሱ ፀሎቶቻችን ምስጋና
✅ እጅግ ብዙ ስለሆነልን በእርሱ
✅ ስለማይነገው ስጦታው ምስጋና ሁሌም ስለሚገባው የሰማይ አባታችንን እኛ ልጆቹ በህብረት ሆነን እናመሰግነዋለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 116
1፤ እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት። 2፤ ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ እጠራዋለሁ።
እግዚአብሔር ሆይ ስለቃልህ እናመሰግንሀለን!!!
መዝሙረ ዳዊት 119
9፤ ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው። 10፤ በፍጹም ልቤ ፈለግሁህ፥ ከትእዛዝህ አታርቀኝ። 11፤ አንተን እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ። 12፤ አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ፤ ሥርዓትህን አስተምረኝ።
አሜን ጎልማሳ መንገዱን እንዴት
ያንጻል አሁን ባለንበት እግዚአብሔር መፍራት በሌለበት ተጽእኖውን በመቆቃም መንገዱን እንዴት አድርጎ ሊጠብቅ ይችላል የእግዚአብሔርን ቃል በመጠበቅ ነው::
▪️የእግዚአብሔር ቃል እጅግ የከበር መሆኑና ቃል እራሱ እግዚአብሄር መሆኑን የሚሰራ የሚፈጥር ሀይል ያለው ያልነበረን ወደ መኖር የሚያመጣ በመሆኑ በልባችን አጥብቀን መትከል ይሁንልን መንፈስ ቅዱስ ይርዳን::
▪️የእግዚአብሔ ቃል ህይወት ያለው የሚሰራ የሚለውጥ መሆኑን ለነፍሳችን መንገር; "ቃሉ ያለው ህይወት አለው"
▪️የእግዚአብሔር ቃል ከምንም ነገር በፊት በህይወታችን አንደኛ ማድረግ;
▪️የእግዚአብሔር ቃል የሁሉ ነገር መልስ መሆኑን ለልባችን መንገር
▪️ለእግዚአብሔር ቃል እስከህይወት ዘመናችን ታማኝ ሆኖ ለመኖር መወሰን;
▪️ጌታን በጸሎት መፈለግ
▪️በቃሉ መደሰት
▪️ለእግዚአብሔርን ቃል በየቀኑ ጊዜ መስጠት ትኩረት ማድረግ ማንበብ በልባችን ማሰላሰል ማስቀመጥ;
ዛሬም መንፈስ ቅዱስ ይህን ከላይ የዘረዝርናቸውን መንገድን የሚያቀና ስርአትን የሚያስተምረን ህይወትን የሚለውጥ በመልካም የህይወት ጎዳና የሚመራ የእግዚአብሔር ቃል ዛሬም ከመቼውም ጊዜ ይልቅ በልባችን ጽላት ላይ ይታተም በኢየሱስ ክርስቶ ስም አሜን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌 ስለ እግዚአብሔር ቃል
✅ ማንበን ,ማስተውል ,ማሰላሰል
✅ በልባችንም መሰወር እና እንደ ቃሉ መመላለስ እንዲሆንልምበህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን 🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 119
10፤ በፍጹም ልቤ ፈለግሁህ፥ ከትእዛዝህ አታርቀኝ። 11፤ አንተን እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ። 12፤ አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ፤ ሥርዓትህን አስተምረኝ።
ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ በኢየሱስ ማመን ለበጎ አድራጎት ሥራ ሙሉ ትርጉም ይሰጣል አሉ!
ቅዱስነታቸው በወቅቱ ያደርጉት አስተንትኖ (በማቴዎስ ወንጌል 16፡13-20) ላይ በተጠቀሰው ኢየሱስ “እናንተስ እኔን ማን ትሉኛላችሁ?” አላቸው።
ስምዖን ጴጥሮስም፣ “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” በማለት መለሰ።ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፣ ብፁዕ ነህ፤ ይህን የገለጠልህ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም አይደለም። አንተ ጴጥሮስ ነህ፤ በዚህ ዐለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አያሸንፏትም። የመንግሥተ ሰማይን መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር ያሰርኸው ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም የፈታኸው ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል” በሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ መሰረቱን ያደረገ አስተንትኖ እንደ ነበረ የተገለጸ ሲሆን “በኢየሱስ ማመን ለበጎ አድራጎት ሥራ ሙሉ ትርጉም ይሰጣል” ማለታቸው ተገልጿል።
ውድ ወንድሞች እና እህቶች እንደምን አረፈዳችሁ!
ማቴ. 16፡13 - 20 ይመልከቱ ጴጥሮስ በኢየሱስ ያለውን እምነት በመግለጽ የእግዚአብሔር ልጅ እና መሲህ መሆኑን ያረጋግጣል። የደቀመዛሙርቱ ምስክርነት ከእርሱ ጋር ባላቸው ግንኙነት ወሳኝ የሆነውን እርምጃ እንዲወስዱ በሚመኘው በኢየሱስ ራሱ አነሳሽነት የቀረበ ጥይቄ ነው። በእርግጥም ኢየሱስ እሱን ከሚከተሉት ጋር በተለይም በአስራ ሁለቱ ጋር የሚያደረገው ጉዞ ሙሉ በሙሉ እምነታቸው እንዲያድግ ለማደረግ ከማስተማር ጋር የተያያዘ ነው። በመጀመሪያ “ሰዎች የሰው ልጅ ማን ይሉታል?” (ማቴ 16፡13) በማለት ይጠይቁታል። እኛ ሁላችንም እንደምናደርገው ሐዋርያት ስለ ሰዎች ማውራት ይወዳሉ። ሐሜት ማውራት እንወዳለን። ስለ ሌሎች መናገር በጣም የሚያስደስት አይደለም፣ ነገር ግን ይህንን ማድረግ እንወዳለን፣ አልፎም ተርፎም በሌሎች ላይ እናሽሟጥጣለን። በዚህ ረገድ ከሐሜት ይልቅ የእምነት እይታ ቀድሞውኑ ተፈልጓል ፣ እናም እሱ “ህዝቡ እኔ ምን ይለኛል?” በማለት ይጠይቃል። ደቀመዛምርቱም የተለያዩ አስተያየቶችን ለመስጠት በሚመስል መልኩ የመፎካከር መንፈስ በሚመስል ሁኔታ፣ ምናልባትም በጣም ብዙ ነገሮችን በዚህ ጉዳይ ዙሪያ አውርተው ሊሆን ይችላል መልስ ለመስጠት ይጣደፋሉ። እነሱ ራሳቸው ስለሱ ተናግረዋል። እነርሱ ከሌሎች ጋር ሐሳቡን ተጋርተዋል። በመሠረቱ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነቢይ ተደርጎ ይቆጠር ነበር።
በሁለተኛው ጥያቄ ኢየሱስ በጥልቀት ይናገራቸዋል፣ እንዲህም ይላቸውል “እናንተስ? … እኔን ማን ትላላችሁ? ” (ማቴ 16፡15) በማለት ይጠይቃቸኋል።
በዚህ ወቅት እያንዳንዳችን እኛ ኢየሱስን ለመከተል የተጠራን ሰዎች በሙሉ በዝምታ በማዳመጥ ኢየሱስን ልንክተል የተጠራንበት ምክንያት ምን እንደ ሆነ በማሰብ በጥርጣሬ ከልክ በላይ የሆነ ጥርጣሬ ውስጥ እንገባለን። አሁን “ለአንተ ኢየሱስ ማን ነው?” ብዬ ብጠይቅ እንኳ ትንሽ ጥርጣሬ ሊኖር ይችላል። ስምዖን በግልጽ “ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ አንተ ነህ” በማለት በመናገር ሁሉንም ግልጽ አወጣ (ማቴ 16፡16)። ይህ መልስ የተሟላ እና በእውቀት ብርሃን የበራ ከራሱ ፍላጎት የመጣ አይደለም ፣ ምንም እንኳን ጴጥሮስ ለጋስ የነበረ ሰው ቢሆንም ቅሉ፣ በእርግጥ ጴጥሮስ ለጋስ ሰው ነበር- ነገር ግን የሰማያዊው አባት ጸጋ ልዩ ፍሬ ነው። በእርግጥ ኢየሱስ ራሱ “ይህ በስጋ እና በደም አልተገለጠልህም” - ይህ ማለት በባህል ውስጥ ካጠናኸው ነገር ተነስቶ የተገለጠልህ ነገር አይደለም ለማለት ፈልጎ ነው። ነገር ግን “በሰማያት ውስጥ ያለው በአባቴ” (ማቴ 16፡17) ነው የገለጸልህ በማለት ይናገራል። ኢየሱስን መመስከር ከአብ የሚሰጥ ጸጋ ነው። ኢየሱስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው ፣ ቤዛ ነው ፣ እኛም ፣ “አባት ሆይ ኢየሱስን የማመን ጸጋ ስጠኝ” ብለን ልንጠይቀው የሚገባን ጸጋ ነው። በተመሳሳይ መልኩም ጌታ ለስምሪት ተነሳሽነት በማሳየት ስምዖን በሰጠው ፈጣን ምላሽ በመቀበል በታላቅ ድምቀት “አንተ ጴጥሮስ ነህ ፣ እኔም በዚህ ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፣ የገሃነም ደጆችም አያሸንፏትም (ማቴ 16፡18) በማለት ይመልስለታል። በዚህ ማረጋገጫ ኢየሱስ ለእርሱ ለስምዖን “ጴጥሮስ” ብሎ የሰጠውን አዲስ ስም ትርጉሙን እንዲያውቅ ያደርገዋል ፣ አሁን ያሳየው እምነት የእግዚአብሔር ልጅ ቤተክርስቲያኑን ለመገንባት ማለትም ማሕበረሰቡን ለመመስረት የሚያስፈልገውን ዓይነት የማይናወጥ “ዐለት” መሆኑን እንዲገነዘብ ያደርገዋል። እናም ቤተክርስቲያን ሁል ጊዜ በጴጥሮስ እምነት መሠረት ትጓዛለች፣ ይህም ማለት ጴጥሮስ ለኢየሱስ እውቅና በሰጠው እና የቤተክርስቲያኒቱ ራስ አደረገው በሚለው እምነት ቤተክርስቲያን ትመራለች፡፡
ዛሬ ኢየሱስ ለእኛ “እናንተ እኔን ማን ትሉኛላችሁ?” የሚለውን ጥያቄ ለእያንዳንዳችን ይቀርብልናል። ለእያንዳንዳችን። እናም እያንዳንዳችን ነገረ መለኮታዊ የሆነ መልስ መስጠት የለብንም ፣ መልሳችን ሊሆን የሚገባ እምነትን ባካተተ ሕይወት ነው። “ለእኔ አንተ …” እናም ከዚያ በኋላ ኢየሱስን መመስከር። እኛ እንደ መጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት በውስጣችን የአብን ድምፅ እና በጴጥሮስ ዙሪያ ከተሰበሰበችው ቤተክርስቲያን ጋር መስማማት የሚጠይቅ መልስ መስጠት ይኖርብናል። ክርስቶስ ለእኛ ማን እንደ ሆነ የመረዳት ጉዳይ ነው፤ እርሱ የሕይወታችን ማዕከል ከሆነ ፣ በቤተክርስቲያን ውስጥ የገባንበት ዋነኛው ግብ እርሱ ከሆነ፣ በህብረተሰቡ ውስጥ ያለን ቁርጠኝነት ምን እንደ ሆነ የመረዳት ጉዳይ ነው። ለእኔ ኢየሱስ ክርስቶስ ማነው? ኢየሱስ ክርስቶስ ለአንተ ማን ነው ፣ ለእርስዎስ ማነው…? በየቀኑ መስጠት ያለብን መልስ ነው።
ነገር ግን ማሰታውል አለብን፣ ለሕብረተሰባችን የምናደርገው ሐዋርያዊ እንክብካቤ በየቦታው ላሉት ብዙ የድህነት እና ቀውስ ዓይነቶች ክፍት መሆናቸው አስፈላጊ እና የሚያስመሰግን መሆኑን መረዳት ይኖርብናል። ልግስና ሁል ጊዜም የእምነት ጎዳና ፣ የእምነት ፍፁም ጎዳና ነው። ነገር ግን የምናከናውናቸው የበጎ ሥራ አገልግሎቶች አስፈላጊ እና ሊከናወኑ የሚገባቸው ቢሆንም ከጌታ ኢየሱስ ጋር እንዳንገናኝ እኛን ሊያግዱን ግን አይገባም። የክርስቲያን በጎ አድራጎት ድርጅት ቀላል የሆነ የበጎ አድራጎት ተግባር አይደለም ነገር ግን በአንድ ወገን ሌሎችን በክርስቶስ ዓይን ይመለከታል፣ በድሆች ፊት ላይ ኢየሱስን ይመለከታል። ይህ እውነተኛው የክርስቲያን በጎ አድራጎት መንገድ ነው ፣ በማዕከሉ ውስጥ ሁልጊዜም ቢሆን ኢየሱስ አለ። በማመኗ የተነሳ ብጽዕት የሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በክርስቶስ የእምነት ጎዳና ላይ መራመድ እንችል ዘንድ መሪያችን እና አርአያችን ትሁን ፣ እናም በእርሱ ላይ ያለን መታመን ለበጎ አድራጎት ተግባር እና ለህይወታችን ሙሉ ትርጉም እንደሚሰጥ እንድንገነዘብ እርሷ በአማልጅነቷ ትርዳን።
ምንጭ:- ቫቲካን ዜና
ሀሌሉያ እግዚአብሔር ሆይ በሙሉ ሀይላችን እናመሰግንሀለን!!!
መዝሙረ ዳዊት 50
23፤ ምስጋና የሚሠዋ ያከብረኛል፤ የእግዚአብሔርን ማዳን ለእርሱ የማሳይበት መንገድ ከዚያ አለ።
ሰማይን ምድርና ሞላዋን የፈጠርክ ሁሉ በአንተ የሆነ ያለህና የምትኖር ሁሉን ቻይ ኤርሻዳይ አልፋ ኦሜጋ ቸር መሀሪ ይቅር ባይ አምላክ ሆይ ምስጋና ይገባሀል ::
እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ጻድቅ ነህ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ትክክል ነህ አትሳሳትም እንከን የሌለብህ ቅዱስ አምላክ ነህ ምስጋና ውዳሴ ስግደትም ይገባሀል::
እግዚአብሔር ሆይ አንተ ታላቅ ነህ ክብርህ ሰማያትን ሸፍኖአል ምድርም ጥበብህን ባህርም ኃይልህን የሚናገሩልህ ፍጥረታት ሁሉ ታላቅነትህን የሚያውጁልህ ሀያል እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ ክብር ምስጋና ሀይል ታላቅነት ከዘላለም እስከዘላለም ለአንተ ይሁን!!! አሜን!!!
ቸርነት በጎነት ምህረት ፍቅር ባህሪህ ነው መገለጫህ ፍቅር ነው እናመሰግንሀለን::
ነገር ቢምላም ባይሞላም ዝም ብለን ሁሌም በሁሉም ተመስገን እንልሀለን:: እንሶብህ አይደለም ምስጋና ስለሚገባህ ጌታ ስለሆንክ
እናመሰግንሀለን ጌታ ሆይ ክብር ምስጋና ለአንተ ይገባሀል::
እግዚአብሔር ሆይ ስላሳለፍነው ሳምንት እናመሰግንሀለን ምስጋና ይገባሀል ምስጋና ልናቀርብ በጎነትን እንድንናገር የተጠራን ልጆቹህ ነንና እናመሰግንሀለን::
ሁሌም አዲስ ምስጋና እንሰጥሀለን
ስላሳለፍነው ቀን እናመሰግንሀለን ይህንንም ሳምንታችንን ለአንተ እናስረክባለን እንተ ክበርበት የምስጋና የሰላም የፍቅር የበረከት የስራ ሳምንት መልካም ነገር የምንሰማበት ስለምታደርግልን እናመሰግንሀለን ሀገራችንን በአንተ ከለላ ጥበቃ ስር አስገዛን የእኛ እና የእኛ የሆኑትን ሁሉ በአንተ መንግስት አስተዳደር ስር አስገዛን ስለሰማኸን ተመስገን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን!!!
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 ወደ ዕብራውያን 13
15፤ እንግዲህ ዘወትር ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት፥ ማለት ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ በእርሱ እናቅርብለት። 16፤ ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች
✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ
በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን
📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው
📖 መዝሙረ ዳዊት 66
19፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ሰማኝ፤ የልመናዬን ድምፅ አደመጠ። 20፤ ጸሎቴን ያልከለከለኝ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይመስገን።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ሰለ እናታችን ማርያም
የዮሐንስ ወንጌል 19
26፤ ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን፡— አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ፡ አላት። 27፤ ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን፡— እናትህ እነኋት፡ አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
