en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
#በዋጋ_ተገዝተናል_ለእግዚአብሔር_የተለየን_ነን “ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 👉 እግዚአብሔር ለሰውነታችን እንኳን እንደሚጠነቀቅ ያሳየው ሰውነታችንንም በመግዛት ነው። (1ቆሮ 7:22-23) #ነፃ_የወጣን_የክርስቶስ_ባሪያዎች_ነን። ክርስቶስ አንዴ ከገዛን በኋላ የእርሱ ባሪያዎች ሆነናል። እግዚአብሔር ለሰውነታችንም የከፈለው ዋጋ ደም ነው። #የተገዛነው_በክርስቶስ_ኢየሱስ_ንፁህ_እና_ክቡር_ደም_ነው። ጌታ ኢየሱስ በዉድ ዋጋ ገዝቶ የራሱ አድርጎ ከገበያ አውጥቶ ለራሱ አድርጎናል። ይህ ምን ያህል መታደል ነው። 👉 ዋጋችንን ማወቃችን የምናደርገውን ብቻ ሳይሆን የማን መሆናችንን እና ለማን መኖር እንዳለብን ጭምር ይገልጣል። #ስለዚህ_አጥብቀን_ከቃሉ_እና_ከመንፈሱ_ጋር ልንጣበቅ ያስፈልገናል። የሰው ትልቅ እረፍት ማንነትን በመረዳት ውስጥ ያለ ሕይወት ነው። #የተባረከ_መልካም_ቀን @eccrm@eccrm @eccrm@eccrm

#በክርስቶስ_ያለን_ማንነት #የማንነት ትርጉም በእግዚአብሔር ቃል እይታ ምን ይመስላል። 👉 በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ያለን የሕይወት እና የማንነት ትርጉም መረዳት ማግኘት በአለም አመለካከት እየተደናበረች ላለች ነፍሳችን እፎይታን የሚያስገኝ የሕይወት ትርጉም የሚሰጥ ልዩ ሀይል ነው። 👉 #በክርስቶስ_ያገኘነው_ማንነታችን ባለንና በሌለን በተቀበልነው እና ባጣነው በተመለሰ እና ባልተመለሰ የፀሎት ጥያቄ በመጣ እና በሄደ ነገር ላይ የተመሰረተ ሳይሆን #በክርስቶስ_የመስቀል_ዋጋ ማን መሆናችን የተወሰነ ነው። 👉 በዚህም ምክንያት በእግዚአብሔር መንግስት የሚታወቀው ማንነታችን ሙሉ መሆናችን ነው። #እኛ_የእግዚአብሔር_ልጆች_ነን ። እኛ በክርስቶስ በኩል ሙሉ ነን። እንግዲህ የፍፃሜ መጀመሪያ ያለው እዚህ ጋር ነው። #ሙሉነት_በትግል_ብዛት_የምናገኘው_አይደለም። መገለጥ ይፈልጋል ክርስቶስ ተፈፀመ ባለው ላይ የተገኘውን ጅማሬ ማግኘት መረዳት ወሳኝ ነገር ነው። ምክንያቱም ጅማሬያችን ፍፃሜያችንን መናገር ይችላልና ነው። ትክክለኛ ጅማሬ በትክክለኛ ጉዞ ትክክለኛ መደምደሚያ ጋር ያደርሰናል ። በክርስቶስ አማካኝነት ከእግዚአብሔር መንፈስ ተወልደናል ። “የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።” — ሮሜ 8፥16 👉ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው እንደማንነታችን እንኖር ዘንድ አስቀድመን ማን መሆናችንን እንድናውቅለት እግዚአብሔር ይፈልጋል። ምክንያቱም በክርስቶስ ህያውና ነፃ የወጣን የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን የተደመደመ ሐቅ ነው እንጂ የምንጠብቀው ተስፋ አይደለም። ስለዚህ ማን መሆናችንን ተረድተን እንደ ተሰጠን የልጅነት ስልጣን እንመላለስ። #የተባረከ_ቀን

#ሕይወት_በጣም_ቀላል_ነው!!! እንዴት የሚል ብዙ ነው። ሕይወት ቀላል የሚያደርገው ነገር 1 #የሕይወትን_ትክክለኛ_አቅጣጫ_እና_መንገድ_ማግኘት_መቻል ኢሳይያስ 48 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ። ¹⁸ ትእዛዜን ብትሰማ ኖሮ፥ ሰላምህ እንደ ወንዝ ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር፤ የአብዛኛው ሰው ሕይወት ከባድ ነው እንዲልና ሰላሙን አጥቶ የሚኖርበት ምክንያት በዚህ ቃል ውስጥ ያለውን እውነት አለመከተሉ ነው። ስንቶቻችን ነን እግዚአብሔር በመታዘዝ በመረጠልን መንገድ የምንሄድ? ራሳችንን እንጠይቅ ስለዚህ በእግዚአብሔር መንገድ ሄደን ራሳችንን እንየው ሕይወት በእግዚአብሔር መንገድ አስደሳች እና ሰላማዊ እንደሆነ። 2 #ስሜታችንን_ሳይሆን_እግዚአብሔርን_መስማት “የሚሰማኝ ሰው ምስጉን ነው ዕለት ዕለት በቤቴ መግቢያ የሚተጋ፥ የደጄንም መድረክ የሚጠብቅ።”— ምሳሌ 8፥34 ሌላው ሕይወትን ቀላል ማድረጊያ መንገድ #እግዚአብሔርን_መስማት_ነው። እስኪ ዛሬ ወይም በዚህ ሳምንት ብዙ የሰማነው ነገር ምንድን ነው? የሰማነውን ነው የምናሰላስለው ያሰላሰልነውን ነው በልባችን ያለው በልባችን ያለውን ነው የምንኖረው። ስለዚህ #የእግዚአብሔርን_ቃል_ብንሰማ_ሕይወትን_ቀላል_ያደርግልናል። “የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤” — ዕብራውያን 4፥12 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የአሸናፊነት_ሕይወት 👉 ሕይወታችን እንዲቀየር እና የአሸናፊነት ሕይወት እንድንኖር ካስፈለገ በወንጌል ልንሸነፍ ይገባናል። በወንጌል ከተማረክን እና ከተሸነፍን ሕይወት በጣም ቀላል ነው። ምክንያቱም በወንጌል የተማረከ የሚመራው እግዚአብሔር ስለሆነ በእግዚአብሔር ዘንድ ደግሞ ምንም ከባድ ነገር የለም። ስለዚህ እኛም ሕይወትን በቀላሉ አሸንፎ መኖር እንችላለን። “የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።”— መዝሙር 16:11 👉 ሰው ሁሉ ስኬታማ እና ደስተኛ ሰላማዊ ሕይወት መኖር ይፈልጋል። ነገር ግን የሰው ችግር እግዚአብሔርን አለመፈለግ ነው። “እግዚአብሔርም ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላልና፦ እኔን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤” — አሞጽ 5፥4 ሰለዚህ መልካም ሕይወት መኖር ከፈለግን 👉 እግዚአብሔርን እንጂ ራሳችንን መስማት የለብንም የእግዚአብሔርን እንጂ የራሳችንን ሃሳብ ማድረግ የለብንም። ሳኦል ንጉስ ሆኖ ሳለ ዘመኑን በውድቀት ያጠናቀቀው የራሱን መልካም የሚመስል ሀሳብ ሰምቶ ነው። በፍፁም የራሳችን ሀሳብ እና ስሜት መከተል የለብንም። “ሳሙኤልም፦ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።” — 1ኛ ሳሙኤል 15፥22 👉 ራሳችንን እንጠይቅ ኑሮዬ እግዚአብሔርን በመስማት ምኖረው ነው ወይስ ስሜቴን በመስማት? የአሸናፊዎች ሕይወት እዚህ ውስጥ አለ። #የተባረከ_ቀን_ይሁንላችሁ!!

#የክርስቶስ_ምስክሮች “ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ #ምስክሮቼ_ትሆናላችሁ አለ።” — ሐ
#የክርስቶስ_ምስክሮች “ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ #ምስክሮቼ_ትሆናላችሁ አለ።” — ሐዋርያት 1፥8 እስኪ እንጠያየቅ ለሰዎች ፍቅራችንን የምንገልጥበት መንገድ ምን አይነት መንገድ ይሆን? እግዚአብሔር ፍቅሩን ለእኛ የገለጠው አንድያ ልጁን ለእኛ በመስጠት ነው። እኛም ለሰዎች ፍቅራችንን እንድንገልጥ የተጠየቀው #ስለ_ኢየሱስ_በመናገር_በመመስከር_ነው። “የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና።”— ሮሜ 8፥19 ብዙ ሰዎች የእኛን መገለጥ በጉጉት ይጠባበቃሉ ስለ ክርስቶስ እንድንመሰክርላቸው ይፈልጋሉ። ስለዚህ በንቃት ምስክርነታችንን ልንሰጥ ይገባናል። #እውነተኛ_ፍቅር_በድርጊት_ይገለጣል። #ኢየሱስ_ሰላማችን_ነው #ኢየሱስ_ደስታችን_ነው #ኢየሱስ_እረፍታችን_ነው ባለፉት ቀናት ስለኢየሱስ ለስንት ሰው ምን ያህል ተናግረሀል መስክረሀል? ካልተናገረክ ግን ዛሬ ጀምር ፍቅርህን ለሰዎች አሳያቸው። ኢየሱስ እንደሚወዳቸው ንገራቸው። #የተሰጠንን_መክሊት_እናትርፍበት። “አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፦ ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ።” — ማቴዎስ 25፥20 #ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ ሰሚናር እየመዘገብን ነው። #የተባረከ_ቀን_ይሁንልን!!!

#በብርሀን_መኖር “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”— ማቴዎስ 5፥16 የብርሃን ሕይወት የእግዚአብሔር ሕይወት ነው ቃሉ እንዲህ ይላልና ...  " እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት።"(1ዮሐ 1:5) ይህንን የእግዚአብሔር ሐይወት እንድንካፈል እና #የኛ_ማንነት እንዲሆን ጌታ በፈቃዱ ወዶ ጠርቶናል። " የብርሃን ልጆች እንድትሆኑ ብርሃን ሳለላችሁ በብርሃኑ እመኑ አላቸው። " (ዮሐን 12:36)  ስለዚህ ከዚህ ብርሃን በእምነት የተወለዱ ሁሉ እነሱ የብርሃን ልጆችና ደግሞም ብርሃን ናቸው ። " እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። "(ማቴ 5:14)  ነገር ግን ይህ የብርሃን ሕይወት ከእኛ የሚጠይቀው ሀላፊነት አለ እሱም #ብርሀናችን_በመልካም_ሥራ_ተገልጦ_ለዓለም_ሁሉ_እንዲያበራ_ነው ።  " መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።" (ማቴ 5:16) የብርሃን ልጆች  የሕይወት አኗኗር ዘይቤያቸው #ሰማያዊ_ነው 👉 ጌታ ደግሞ እንደ ብርሃን ልጆች በጥበብ ተመላለሱ ብሎናል። በዚህ አለም በምንኖርበት ጊዜ በኑሯችን ሁሉ ብርሃን መሆን አለብን። መልካም የተባረከ ሰንበት ይሁንልን

#ሕይወት_በመንፈሰ_ቅዱስ ውጤታማ ከሚያደርጉንና #በአእምሮ_የበሰሉ ሰዎች መገለጫ መካከል #ራስን_መፈተሽ ብቃት ማዳበር ነው፡፡ በአእምሮ የበሰሉ ሰዎች #ራሳቸውን_ይፈትሻሉ፡፡ እራሳቸውን ይገመግማሉ፣ ከራሳቸው ጋር ይወያያሉ፣ ይመካከራሉ በመጨረሻም እየሄዱ ያሉበት መንገድ ልክ ካልሆነ #መንገዱን_በማስተካከል የተሻለ ነገ ለመኖር እራሳቸውን ያዘጋጃሉ መሳሳታችን አይደለም ችግሩ ራሳችንን ለመለወጥ ካልተዘጋጀን ሁሌም ችግሩ ከእኛ ጋር ይኖራል ፡፡ አንድ ነገር ራሳችንን መጠየቅ አለብን መቼም ቢሆን ለሰዎች በአንደበታችን ልንዋሻቸው እንችል ይሆናል እንጂ ለልባችን አንዋሸውም ልባችን ይፈርድብናል። ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ ይጠበቅብናል። #ምንድን_ነው_ሕይወቴ_ውስጥ_መቀየር_ያለብኝ ብለን ራሳችንን እንጠይቅ? ብርቱውንና ደካማውን ቦታችንን መለየት እንችላለን። ምን እንደሚያስፈልገን ካወቅን ለሚያስፈልገን ነገር የሚገባውን ቦታ እንስጠው። “የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።” — ሉቃስ 10፥42 ኢየሱስ #መንፈስ_ቅዱስን የሰጠን ሁሉ ነገራችንን እንድንቀይርበት ነው። አንድ ሰው #በመንፈስ_ቅዱስ የሆነ ሕይወት ሲያገኘው ከሀዘን ወደ ደስታ፣ ከድካም ወደ ብርታት ፣ ከጭንቀት ወደ ዕረፍት ይሻገራል። ሕይወት ክርስቶስ እንደሰጠው #አዲስ_ሕይወት ይሆንለታል። #በሕይወታችን_ያለብን_ጥያቄ_ምንድን_ነው? #መንፈሳዊ_ድካም? ጳውሎስም መንፈሳዊ ድካም የነበረበት ሰው ነው። ነገር ግን #በመንፈስ_ቅዱስ ኃይል ድካሙን አስወግዶ በዘመኑ ሁሉ ለጌታ የተሰጠ የከበረ ሕይወት ኖሮ አለፈ። እኛም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በርትተን ከጌታ ጋር የከበረ ሕይወት እንድንኖር #መንፈስ_ቅዱስ ተሰጠን። “ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።” — ፊልጵስዩስ 4፥13 #ኃጢአት_ነው_ያስቸገረን? ንጉስ ዳዊት ኃጢአት ያስቸገረው ሰው ነበር። ነገር ግን በንስሐ ተመልሶ እግዚአብሔርን አስከብሮ ዘመኑን ጨረስ። እግዚአብሔር እንደልቤ ብሎ እስኪመሰክርለት ድረስ ሆነ። እኛም #በመንፈስ_ቅዱስ ኃይል መቀየር እንችላለን። “በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።”— መዝሙር 51፥7 #መንፈስ_ቅዱስ ሁሉ ነገራችንን ሊቀይር የሚችል ኢየሱስ የመሰከረለት ታላቅ የእግዚአብሔር ኃይል ነው። እኛም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሁሉ ነገራችን ይቀየራል። ለዚህ ነው በመንፈስ ቅዱስ የሆነ ሕይወት የሚያስፈልገን። “ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ #እውነት_ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።” — ዮሐንስ 16፥13

#ሕይወት_የምርጫችን_ውጤት_ነው “ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ።” — ኢሳይያስ 48፥17 ከወላጆቹ ጋር የሚኖርን አንድ ወጣት እንደ ምሳሌ እንመልከት። አባቱ ልጁን በጣም ይወደዋል፤ ጥሩ ውሳኔ ማድረግ እንዲችልም አሠልጥኖታል። ሆኖም ልጁ በአባቱ ላይ ያምፅና ቤቱን ጥሎ ይወጣል። ከዚያም መጥፎ ነገር ይፈጽምና ችግር ላይ ይወድቃል። አባትየው ልጁ ከቤት ሲወጣ ስላልከለከለው፣ ልጁ ለደረሰበት ችግር አባትየው ተጠያቂ ሊሆን ይችላል? በፍጹም! (ሉቃስ 15:11-13) ልክ እንደዚህ አባት፣ እግዚአብሔር የሰው ልጆች በእሱ ላይ ሲያምፁና መጥፎ ነገር ሲያደርጉ አልከለከላቸውም። ለሰው ሁሉ ነጻ ፈቃድ ስለሰጠ። ስለዚህ አንድ መጥፎ ነገር ሲደርስ ይህን ያመጣው እግዚአብሔር እንዳልሆነ መገንዘብ አለብን። #የመጥፋትም_ሆነ_አብሮ_የመኖርም_ምርጫው_በእኛ_እጅ_ነው። ዛሬ ምርጫችን ምንድን ነው? እግዚአብሔር ሁልግዜ ይፈልገናል። ስንመለስ በፍቅሩ ይቀበለናል።

#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሰሚናር 👉 ይህ ሰሚናር በአለም አቀፍ ደረጃ በካቶሊክ ካርዝማቲክ እንቅስቃሴ #LIFE_IN_THE_SPRITE #ሕይወት_በመንፈሰ_ቅዱስ በሚል ርዕስ ለ ሶስት ወር የሚሰጥ ሲሆን ብዙ ምዕመና መንፈሳዊነታቸውን የለወጡበት እና ያሳደጉበት ነው። #ሰሚናሩን_ከወሰዱ_ሰዎች ምስክርነት ማግኘት ይችላሉ። #የሴሚናሩ_ጥቅም_በአጭሩ የቃሉን መረዳት ይሰጠናል 👉 መጽሐፍ ቅዱስ ለምናነሳቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል አንዳንድ ሰዎች መልስ እንደሚሰጥ ያምናሉ፤ ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስን መረዳት ከባድ እንደሆነ ስለሚሰማቸው መጽሐፍ ቅዱስ አያጠኑም። በርግጥም ቃሉን እንድንረዳ የሚያስችለን #መንፈስ_ቅዱስ_ነው። “በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤” — ሉቃስ 24፥45 የጸሎት ሕይወታችን ያሳድጋል 👉 በጸሎት ሕይወታችን ጠንካራ እንድንሆን #ፍሬያማ_የጸሎት_ሕይወት_እንዲኖረን የሚያደርገን የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ነው። ይህን ኃይል እናገኝበታለን። “እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤” — ሮሜ 8፥26 አዘጋጅ #የኢትዮጵያ_ካቶሊክ_ካርዝማቲክ_እንቅስቃሴ ቦታ ጎተራ ደንቦስኮ ቤተክርስቲያን ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ጥር 23 ዘወትር እሁድ ከ7:30-9:00 መረጃ ለማግኘት 0923461848 0910056879 0934441751 ምዝገባ ጀምረናል ይህን መልዕክት ለ3 ሰው share ያድርጉት። @eccrm @eccrm

#የመንፈሰ_ቅዱስ_ስራ_በሕይወታችን_ይገለጥ ሐዋርያት 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ² ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። ³ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። ⁴ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር። #መንፈሰ_ቅዱስ_ሲሞላን 👉አዲስ የፀሎት ሕይወት ይሆንልናል ኃይል ያገኘናል 👉እግዚአብሔር የመፈለግ ጉጉት ይመጣብናል 👉አዲስ የደስታ ሕይወት እረፍት ይሆንልና 👉የመመስከር ድፍረት ይሰጠናል “የሕይወትን መንገድ አስታወቅኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን ትሞላብኛለህ።”— ሐዋርያት 2፥28 ✅ አዲስ የሕይወት መንገድ ደስታ ያለው ሕይወት ነገ በሚኖረን ፕሮግራም መንፈሰ ቅዱስ በኃይል ይሰራል። ሁላችንም የማንቀርበት ልዩ ፕሮግራም። እግዚአብሔር በመንፈሱ ይጎበኘናል።