en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች ✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን 📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው 📖 መዝሙረ ዳዊት 22 24፤ የችግረኛን ችግር አልናቀምና፥ ቸልም አላለምና፤ ፊቱንም ከእኔ አልሰወረምና፥ ነገር ግን ወደ እርሱ በጮኽሁ ጊዜ ሰማኝ።

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ቅዳሜን ስለፈወስ ✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች ✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል መዝሙረ ዳዊት 103 2፤ ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ፤ 3፤ ኃጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፥ ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፥ 4፤ ሕይወትሽን ከጥፋት የሚያድናት፥ በምሕረቱና በቸርነቱ የሚከልልሽ፥ 5፤ ምኞትሽን ከበረከቱ የሚያጠግባት፥ ጕልማስነትሽን እንደ ንስር ያድሳል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ምስጋና ✅ አዲስ ዘመን ስላየን ✅በቸርነት እና ምህረቱ አመታትን ስለተቀዳጀን ✅ በብዙ ባርኮት እና ጥበቃ ስላሻገረን በበዛ ምስጋና በህብረት ሆነን በፊቱ እንቀርባለን 🙏 📖 መዝሙረ ዳዊት 65 11፤ በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። 12፤ የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ።

አሜን አሜን አሜን !!! ሀሌሉያ እናውጃለን ለኢትዮጲያችን በምስራቅ በምእራብ በስሜን በደቡብ ለሕዝቦችዋ ለመሪዋቻችን ለሀይማኖት መሪዎች ለወታደሩ ለገበሬው ለቤተክርስቲያንአችን ለአዛውንቶች ለአባት እናቶች ለእህት ለወንድሞች በቤታችን ለወጣቶች ለህጻናት ለተወለዱ ገናም ዛሬም ለሚወለዱ በሆስፒታል ላሉ በጎዳን ላሉ በስደት ላሉ በባህር በየብስ ለሚሄዱ ለአገልግሎታችን ለቤተሰባችን ለልጆቻችን ሁሉ የእግዚአብሔርን ታላቅነት እናውጃለን!!! አሜን!!! ሀሌሉያ አዲሱን አመት በተዋጀ ህይወት በደስታ ምህረቱ ለዘለአለም ነውና የተስጠንን አዲስ አመት በምስጋና አስቀድመን እንወጣለን:: አሜን!!! 2013 ልባችንን በምስጋና ሞልተን ጌጠኛ ልብስ ለብሰን በምስጋና ቸር ነውና ምህረቱ ለዘለአለም ነውና እግዚአብሔር አመስግኑ የሚለውን በመዘመር እንገባለን አሜን በእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት ታምነን በምስጋና አዲሱን አመት እንገባለን በምስጋና እንነሳ የምስጋና መስዋት እናቀርብለታለን እንዘረዝርለታለን እናወራዋለን ምስጋናችንን እንቆጥራለን :: ቃሉን በእምነት እናውጃለን እናገራለን እንገልጣለን:: መልካም የፍቅር የበረከት የሰላም የደስታ የመከባበር የመረዳዳት እግዚአብሔር የማክበት የማንገስ ዘመን ይሁንልን!!! አሜን !!!! የእግዚአብሔርን በጎነት ምህረት ቸርነት የተሞላ አመት ይሁንልን !!! አሜን!!!

🗣የአዲሱ ዓመት አዋጅ ✅ በጌታ ሀሴት የምናደርግበት ✅ በብርሃን የምንመላለስበት ✅ በከፍታ የምንገለጥበት ✅ በልህቀት የምንወጣበት ✅ በጥበብ የምንመላለስበት ✅ በእግዚአብሔር ቃል የምንመራበት ✅ የመንፈስ ቅዱስ ድምጽ በግልጽ የምንሰማበት ✅ ብርሃናችን በሰው ፊት የሚበራበት ✅ ከዓለም አስተሳሰብ የምንለይበት ✅ በጽድቅ በቅድስና የምንመላለስበት ✅ ለስጋ የማንገዛበት ✅ በእውነት ነፃ የምንወጣበት ✅ እግዚአብሔርን በመግለጥ የምንደምቅበት ✅ የጽድቅ ኑሮ በመኖር የምንፈካበት ✅ የክርስቶስ መዓዛ የሕይወት ሽታ የምንሆንበት ✅ ቃላችን ለሰዎች ፈውስ የሚሆንበት ✅ ስለሁኔታዎች ነገሮች በጎውን የምናወራበት ✅ ትዳራችንን ልጆቻችንን የምንባርክበት ✅ ጤናችን የበለጠ በቅጥር የሚጠበቅበት ✅ ስለ ቤተከርስቲያን በፀሎት የምንተጋበት ✅ በክፋት ላይ የምንነግስበት ✅ ከዓመጽ በመራቅ ከጽድቅ ጋር የምንተባበርበት ✅ የጨለማን ክፉ ስራ በስልጣናችን የምናፈርስበት ✅ ያለ ፍርሀት በድፍረት መንፈስ ቅዱስን የምገልጥበት ✅ በፍቅር በልግስና በመስጠት የምንባረክበት ✅ ለእግዚአብሔር ቤት ስራ ቀድመን በኃላፊነት ከፊት የምንቆምበት 🗣እናውጃል እነዚህን በእኛ በቤታችን በሀገራችን ላይ “እግዚአብሔር አምላክ ምሕረትንና እውነትን ስለ ወደደ፥ ሞገስንና ክብርን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም።” — መዝሙር 84፥11 “ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም።” — መዝሙር 34፥10 እግዚአብሔርን የሚያምን ከመልካም ነገር አይጎድልም

👇አዲሱ ዓመት ✅ በጌታ ሀሴት የምናደርግበት ✅ በብርሃን የምንመላለስበት ✅ በከፍታ የምንገለጥበት ✅ በልህቀት የምንወጣበት ✅ በጥበብ የምንመላለስበት ✅ በእግዚአብሔር ቃል የምንመራበት ✅ የመንፈስ ቅዱስ ድምጽ በግልጽ የምንሰማበት ✅ ብርሃናችን በሰው ፊት የሚበራበት ✅ ከዓለም አስተሳሰብ የምንለይበት ✅ በጽድቅ በቅድስና የምንመላለስበት ✅ ለስጋ የማንገዛበት ✅ በእውነት ነፃ የምንወጣበት ✅ እግዚአብሔርን በመግለጥ የምንደምቅበት ✅ የጽድቅ ኑሮ በመኖር የምንፈካበት ✅ የክርስቶስ መዓዛ የሕይወት ሽታ የምንሆንበት ✅ ቃላችን ለሰዎች ፈውስ የሚሆንበት ✅ ስለሁኔታዎች ነገሮች በጎውን የምናወራበት ✅ ትዳራችንን ልጆቻችንን የምንባርክበት ✅ ጤናችን የበለጠ በቅጥር የሚጠበቅበት ✅ ስለ ቤተከርስቲያን በፀሎት የምንተጋበት ✅ በክፋት ላይ የምንነግስበት ✅ ከዓመጽ በመራቅ ከጽድቅ ጋር የምንተባበርበት ✅ የጨለማን ክፉ ስራ በስልጣናችን የምናፈርስበት ✅ ያለ ፍርሀት በድፍረት መንፈስ ቅዱስን የምገልጥበት ✅ በፍቅር በልግስና በመስጠት የምንባረክበት ✅ ለእግዚአብሔር ቤት ስራ ቀድመን በኃላፊነት ከፊት የምንቆምበት ❤ ዘመን ይሁንልን በኢየሱስ ስም አሜን!!! በአዲሰ ዘመን አዲስ ነገር የእግዚአብሔር ስም እንዲከበር እንጠብቃለን በናፍቆት ያደርገዋል ምን ተስኖት

የዮሐንስ ወንጌል 3 30፤ እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል። አሜን መጥምቁ ዩሐንስ ቦታውን ያውቃል የተላከው ኢየሱስን ከፍ ለማድረግ ነው:: እኛም በክርስቶስ ደም የተዋጀነው የክርስቶስ ተከታይዬች የእግዚአብሔር ልጆች ይሆንን የተጠራነው የክርስቶስን ብርሀን ለማብራት ኢየሱስ ከፍ ብሎ እኛ ለክብሩ ዝቅ እንድንል ነውና እኛ ልናንስ አንተ ግን በህይወታችን ልትልቅ ይገባሀል አሜን!!! ጌታ ሆይ አንተን በማክበር ለቃልህ በመታዘዝ እርስ በርሳችን በመከባበር በመዋደድ አንተን በማስቀደም አንተን በልባችን በማንገስ በተዋጀንበት ህይወት በመኖር ትልቅነትህን በልባችን በሀሳባችን በእቅዳችን በአገልግሎታችን በአመለካከታችን በአኖአኖራችን በአካሄዳችን በአነጋገራችን በስራችን በባህሪያችን በሁለንተናችን የአንተን ታላቅነት ክብር በበጎነት ሁሉ እንድንመሰክር በስራችን እንድናስከብርህ ከሁሉ በላይ መሆንህን እኛ ልናንስ አንተ ግን ልቀህ በህይወታችን የምኖርበት ጸጋህን አብዛልን አሜን!!! እኔ ላንስ አንተ ልትልቅ ይገባልና ትእቢቴን ሻረው ልቤንም ስበረው ጌታሆይ!!! በተሰበር ልብ ዝቅ ባለ ልብ በሚታዘዝ ልብ እናገልግልህ እኛ ልናንስ አንተ ግን ልትልቅ ይገባልና እጅግ በህይወታችን ልቀህ ደግሞ ልቀህ በሀሳባችን አሜን አሜን አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 አዋጅ ✅ በሀይላችን ሳይሆን በመንፈሱ ውስጥ ሆነን ✅በመጪው አመት እኛነታችን የስጋ ምልልሳችንን ዝቅ እያረግን እየሱስ ከፍ እንዲል በህይወትችንን እናውጃለን 🙏 📖 የዮሐንስ ወንጌል 3:30 እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።

ትንቢተ ዘካርያስ 4 6፤ መልሶም፡— ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፡— በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። 7፤ ታላቅ ተራራ ሆይ፥ አንተ ምንድር ነህ? በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎችም፡— ሞገስ፥ ሞገስ ይሁንለት፥ ብለው እየጮኹ፥ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል፥ ብሎ ተናገረኝ። አሜን አሜን አሜን በእግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በራሳችን ምንም ማድረግ አንችልም!!! የወታደር ሀይል የፖለትካ ስልጣን ወይም የሰው ብርታት የእግዚአብሔር ስራ ሊፈጽም አይችልም የእግዚአብሔር ስራ ማከናወን የምንችለው በእግዚአብሔር አብ መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ሀይልና ብርታት ብቻ ነው:: ሰው በሀይሉ አይበረታምና በመንፈስ ቅዱስ ሀልና ብርታት ግን እንበረታለን አሜን!!! ዛሬም እንደተራራ የከበደ የማይገፋ የሚመስል ልዩ ልዩ ችግር በእኛ ውስጥ በሚሰራው በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ይወገዳል:: በሀገራችን በሕዝባችን ላይ ተራራ የሆነ ችግር ግራ መጋባት በሽታ ሁሉ በኢየሱስ ስም ደልዳላ ሜዳ ይሁን ይለወጥ ይጠረግ የከበደ የማይነቃነቅ የሚመስል ሁሉ ይነቀል ከእያንዳንዳችን ህይወት አልወጣ ያለ ነገር ሁሉ ሜዳ ይሁን በአገልግሎታችን በኑሮአችን በቤተሰባችን በቤተክርስቲያናችን ሁሉ ተራራው ሆኖ የማይወጣ የማይናድ የማያልፍ የሚመስለው ሁሉ በኢየሱስ ስም ደልዳላ የሚመች ሜዳ ይሁን በልባችን ላይ እንደተራራ የተቆለለ ነግር ሁሉ ይናድ ይደርመስ ይጠረግ ከምንሰማው ከምናየው ከሁኔታ ከሚሆነው ሁሉ ላይ የንኛ ከሆነው ሁሉ ላይ ተራራው ይናድ ይደልደል ምቹ መሬት ምቹ ልብ ይሁን 2012 ትን አይሻገር በጌታ በኢየሱስ ስም አሜን!!!

ሉቃስ 13: 11 -13 በሰንበትም በአንድ ምኰራብ ያስተምር ነበር። እነሆም ከአስራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች እርሳም ጎባጣ ነበረችቀንታም ልትቆም አልቻለችም። ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና አንቺ ሴት ከድካምሽ ተፈተሻል አላት እጁንም ጫነባት ያን ጊዜም ቀጥ አለች ።እግዚአብሄርንም አመሰገነች። አባት ሆይ ዛሬም ለምድራችን መፈታት ለእኛም ተራራ የሆነብንን ይዘን እንዳንሻገር መጣል ይሁንልን በኢየሱስ ስም አሜን🙏

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 አዋጅ ✅ በሀይላችን ሳይሆን በመንፈሱ ውስጥ ሆነን ✅ ተራራ የሆኑብንን ነግሮች ሁሉ ላይ ዛሬ ሜዳ ትሆናለህ እንላለን ወደመጪው ዘመን ይዘነው አንሄደም 🙏የእግዚአብሄር መንፈስ ከኛ ጋር ያለው ይረዳናል 📖 ትንቢተ ዘካርያስ 4 6፤ መልሶም፡— ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፡— በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። 7፤ ታላቅ ተራራ ሆይ፥ አንተ ምንድር ነህ? በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎችም፡— ሞገስ፥ ሞገስ ይሁንለት፥ ብለው እየጮኹ፥ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል፥ ብሎ ተናገረኝ።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 73 28፤ ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።

የማቴዎስ ወንጌል 6 14፤ ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ 15፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም። የምህረት አምላክ የምህረት ንጉስ እግዚአብሄር አባታችን እናመሰግንሀለን የሀያላን ሁሉ ሀያል የጌቶች ሁሉ ጌታ የነገስታት ሁሉ ንጉስ አምላካችን አባታችን እግዚአብሔር ስምህ ይመስገን ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን!!! ስለተቀደሰው እለተ ሰንበት እጅግ እናመሰግንሀለን:: ዛሬም ደግሞ ማለዳ ማለዳ አዲስ በሆነው ምህረትህ ቸርነትህ በዝቶልን እያሻገርከን እያሳለፍከን ለዚህ ይቅር ለመባባልና የንሰሀ እድሜና ጊዜ አድርሰኸናል እጅግ እናመሰግንሀለን ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን!!! እግዚአብሄር አባት ሆይ ወደ አንተ እንጸልያለን እንደቃልህ ከልብ የሆነ ይቅርታን ለማድረግና ለመቀበል የሚችልበትን መለኮታዊ ጸጋ የተሰበረ የይቅርታ ልብ የመታዘዝ የትህትና መንፈስ በደልን ቂምን በመተው ያለፈውን ሁሉ በመተው በእውነተኛ ይቅርታ በኢዲስ ልብ በንጽህ ህሊና ወደ አዲስ ምእራፍ እንድንሻገር ከአንተ የሆነ መለኮታዊ ጸጋ ለኢትዮጵያ ሀገራችን ለሕዝባችን ለመሪዎች ለሀይማኖት መሪዎች ለቤተሰብ ሁሉ ለልጆች ለድንበር ጠባቂው ለገበሬው ለወጣቱ ለሁሉም ከትልቅ እስከትንሽ የምረትህን ሀይል የምህረትህ ዝናብ ከጫፍ እስከጫፍ እንድታፈስልን እንድታጥበን እንድታነጻን እንድታንጸን በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሀለን:: እግዚአብሔር አባታችን ሆይ ምህረትህ አያልቅምና ለዘለአለምም ቸር ነህና በሀገራችን የማዳንህን የምህረትህን ሀይል አሳየን ምህረትህ ይግነን ኢትዬጵያ እጆችዋን ከልብዋ ጋር ወደ አንተ ዘርግታለችና በሆነው ሁሉ ይቅር በለን በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን!!! ስለሰማኸን እናመሰግንሀለን!!! 2013 የምህረትህ ብርሀን በሀገራችን በህዝባችን ላይ ይብራ ይፈንድቅ ኢትዬጵያን ምህረትህ ይሸፍናት ምህረትህ ከሁሉም በላይ ከፍ ብሎ በከፍታ ደምቆ ይታይ በኢየሱስ ስም አሜን!!!! ክብር ምስጋና አምልኮ ስግደት ውዳሴ ቅዳሴ ሁሉ ለአንተ ለአምላካችን ይሁን አሜን!!!🙏🙏🙏

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ይቅርታ ✅ይቅርታን ለመስጠት እና ለመቀበል የተሰበረ ልብ ለመላው ህዝባቻን እንዲሆን ✅እውነተኛ ይቅርታ እውነተኛ መሻገር እንዲሆንልን አባታችን ፊት ቆመንን ለኛ እና ለሀገራችን ሁሉ ፀጋውን እንጠይቃልን ብርሃሁንንም በልባቻንን እንዲያበራ እንለምናለን 🙏 📖 የማቴዎስ ወንጌል 6 14፤ ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ 15፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።

ወደ ፊልጵስዩስ 2 9፤ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ 10፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ 11፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ለስሙ ጉልበት ሁሉ ይንበረከካል የከበረ ስም አባቱ ያከበረው ስም ነው ለእግዚአብሔር አብ ክብር ሁሉ ይንበረከካል አሜን አሜን አሜን!!! ሀሌሉያ ኢየሱስ ሆይ ስምህ እንደሚፈስ ዘይት ነው:: ኢየሱስ ማለት እግዚአብሔር አዳኜ ነው :: አሜን!!! ኢየሱስ አዳኝ ነው ህያው የሆነ ስም ነው ኢየሱስ አባቱ ያከበረው በሰማይም በምድርም ስልጣን የተሰጠው ስም ኢየሱስ በሚለው ስም በአብ ፊት እንቀርባለን:: ኢየሱስ ብለን በመንፈስ ቅዱስ ሀይልና ስልጣን ስንጠራው በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ የሚገኝ ሁሉን ማድረግ የሚችል አቅም ጉልበት ስልጣን ያለው ሁሉን ማድረግ የሚችል ኢየሱስ አብ ያልተከለውን ሁሉ ከህይወታችን ያስወግዳል ህይወታችንን ይለውጣል የታመመን ይፈውሳል ጥያቄን ይመልሳል አዲስ ነገርም ይሆናል ያረጀውን ያድሳል ለሙታን አዲስ ህይወት ይሰጣል ነገርን ይለውጣል እስራትን ሁሉ ይፈታል በድንቅ ያራምዳል በሰማይና በምድር ስልጣን ሁሉ የኢየሱስ ነው:: አሜን!!! በCOVID የታመሙትን ሁሉ በቤታቸው በሆስፒታል ያሉትን ሁሉ ወደ አንተ ሁሉን የምታድን አምላካችን አባታችን ፊት አቀረብን ኢየሱስ በማዳንህ በፈውስህ ተገለጥ የሚያድነውን ከስሞች ሁሉ በላይ የሆነውን እንድንድንበት የተሰጠን ከሰማይ በታች ሁሉም የሚታዘዙለትን ኢየሱስ የሚለውን ስም በእምነት ጠራን ኢየሱስ አዳኝ ፈዋሽ ኢየሱስ መድሀኒት ስምህን እንጠራለን ከስምህ ሀይል ክብር የተነሳ መፈወስ መዳን ይሁን መተንፈስ የማይችሉትን ሁሉ የአንተን ህይወት ሰጪ እስትንፋስ ይሙላባቸው ኢየሱስ ሆይ እንጠራሀለን እለፍ ሰላምህ ያግኛቸው ሁሉ ይፈወሱ ነጻ ይውጡ በአዲስ ህይወት መኖር ይሁላቸው ከጭንቅ አውጣቸው:: ደጉ ኢየሱስ ሆይ ፍቅርህ ወሰን የለውም ጸሎታችንን ስለስማኸን እናመሰግንሀለን!!! ክብርም ምስጋናም አምልኮም ስግደትም ከዘለአለም እስከዘላለም ለአንተ ይሁን አሜን!!!

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ቅዳሜን ስለፈወስ ✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች ✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል መዝሙረ ዳዊት 103 2፤ ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ፤ 3፤ ኃጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፥ ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፥ 4፤ ሕይወትሽን ከጥፋት የሚያድናት፥ በምሕረቱና በቸርነቱ የሚከልልሽ፥ 5፤ ምኞትሽን ከበረከቱ የሚያጠግባት፥ ጕልማስነትሽን እንደ ንስር ያድሳል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 አምስጋኞች እንድንሆን ✅ የብዙ ተስፋ ባለቤቶች ስለሆንን ✅ በምስጋና ብዙ ተራራዎችን ስለምናልፍ ✅ጠላትንም ለማሳፈር ! አፋችንን እና ልባችን ሁል ጊዜ በምስጋና እንዲሞላን እግዚአብሔር ፀጋውን እንዲበዛልን እንፀልያለን 🙏 📖 ወደ ቆላስይስ 4: 2 ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 አምስጋኞች እንድንሆን ✅ የብዙ ተስፋ ባለቤቶች ስለሆንን ✅ በምስጋና ብዙ ተራራዎችን ስለምናልፍ ✅ጠላትንም ለማሳፈር ! አፋችንን እና ልባችን ሁል ጊዜ በምስጋና እንዲሞላን እግዚአብሔር ፀጋውን እንዲበዛልን እንፀልያለን 🙏 📖 ወደ ቆላስይስ 4: 2 ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።

🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏 ✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏 📖 ትንቢተ ኤርምያስ 29 12፤ እናንተም ትጠሩኛላችሁ፥ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፥ እኔም እሰማችኋለሁ። 13፤ እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። 14፤ ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ ምርኮአችሁንም እመልሳለሁ፥ ከአሕዛብም ሁሉ ዘንድ እናንተንም ካሳደድሁበት ስፍራ ሁሉ እሰበስባችኋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እናንተንም ለምርኮ ወዳፈለስሁበት ስፍራ እመልሳችኋለሁ።

2ኛ ሳሙኤል 22:3-4 እግዚአብሔር ጠባቂዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ፤ ጋሻዬና የረድኤቴ ቀንድ፥ መጠጊያዬና መሸሸጊያዬ፥ መድኃኒቴ ሆይ፥ ከግፍ ሥራ ታድነኛለህ። ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፤ ከጠላቶቼም እድናለሁ። አሜን አሜን አሜን አባት ሆይ ስለውሎአችን ተመስገን ተባረክ ስለምሽታችንም በምስጋና በፊትህ ቀረብን ጠባቂያችን አንተ መታመኛችን አንተ ረዳታችን አንተ ጋሻችን አንተ መጠጊያ መሸሸጊያችን አንተ መድሃኒታችን አንተ ከግፍ ሥራ ጠባቂያችን አንተ አዳኛችን አንተ ስለሆንክ እናመሰግንሃለን አባ ስለሀገራችን በሆነልን ባሳለፍክልን ሁሉ ተመስገን ጥበቃህ ስለበዛልን እናመሰግንሃለን ዛሬ ደግሞ በአገራችን ድንበር ላይ ላይም ሆነ በአገራችን ጠቅላላ የደህነት አገልግሎት ሥራ ላይ የተሰማሩትን እና ቤተሰቦቻቸውን ሁሉ ይዘን በፊትህ ቀረብን ደግመን ደግመን እንጠራሀለን ትሰማናለህ ተመስገን አባት ሆይ ቤተሰባቸውንና ኑሮአቸውን ሁሉ ትተው ግዳጃቸውን በዱር በበረሀ በብዙ ውጣ ውረድ ብዙ ስቃይና መከራ እያሳለፉ አገራችንንየሚጠብቁትን ሁሉ በደምህ ሸፈናቸው ጌታ ሆይ ጥበቃህ ይብዛላቸው መዳን ይሁንላቸው በሚያስፈልጋቸው ሁሉ አንተን እየሱስ እየሱስ እየሱስ ብለን ሃያሉን ስምህን ጠራንባቸው ሁሉን ለታማኝ እጆችህ አስረከብን በጌታ እየሱስ ክርስቶስ ስም 🙏🏽🙏🏽🙏🏽