en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
✔️የእግዚአብሔርን ደስታ ሀይላችን ነው:: ✔️የደስታችን ምንጭ እግዚአብሔር ነው:: ✔️መዝሙር 34(35) 9 ነፍሴ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይላታል፥ በማዳኑም ሐሴት ታደርጋለች። ✔️ትንቢተ እንባቆም 3: 17 ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥ 18 እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። 19 ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል። አሜን ሀሌሉያ ✔️መንፈሳዊ ደስታ በስራችን ወይም በአቅማችን ወይም በራሳችን ችሎታ ወይም በእውቀታችን ወይም በሀብታችን ወይም በስኬት ባገኘናቸው ወይም በሆነልን ነገር ወይም አለኝ በምንለው ቁሳዊ ነገሮች የምናገኘው ሳይሆን ከእግዚአብሔር አባታችን ከእግዚአብሔር ወልድ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር ካለን ህብረት የተነሳ ወደልባችን ወደ ልባችን ብሚፈሰው መንፈስ ምክንያት የምናፈራው ደስታ ሀሴት ነው:: ሀሌሉያ ስሙ ይመስገን!!! ✔️የእግአብሔር ደስታ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት አምነን በተሰጠን መንፈስ ቅዱስ በህይወት በመኖር የምናገኘው የማይለዋወጥ የማይቀይር ሁል ጊዜ አምላካችንን በማሰብና ከእሱ ጋር ህብረት በማድረግ የምናገኘው ከውስጥ የሚፈልቅ ደስታ ነው:: አሜን!!! ✔️ሁል ጊዜ ደስተኛ መሆን የምንችለው የደስታ ምንጭ ከሆነው ጌታችን ጋር ከምንጬ የሚፈልቀውን ስንጠጣ እርካታ እናገኛለን ደስታችን ሙሉ ነው:: ✔️ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 04 4 ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ✔️ 1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 05 16 ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ✔️ህይወቱ በእግዚአብሔር ፍቅር የተሞላ ሰው በጌታ ሁሌም ደስ ይለዋል:: ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት በማድረጉ ቅርብ በመሆኑ ይደሰታል:: ✔️ሁል ጌዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ ትእዛዝ ተሰጥቶናል :: በትዛዙ መሰረት ሁሌም የህይወት የመንፈስ ደስታ የሚገኘው ከደስታ ባለቤት ከሆነው ከኢየሱስ ጋር ከመንፈስ ቅድስ ጋር የጠበቀ ህብረት የጠበቀ ግንኙነት ማድረግ ነውና እግዚአብሄር ይህንን የምናደርግበት ጸጋ ሁሌም በጌታ ደስ የምንሰኝበት ጸጋ ብዙ ደስታ ልባችን ሞልቶ በችግር በመከራ በሀዝን ላሉት ደስታ የምንዘራበትን ጸጋ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያብዛልን:: አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው ደስታ 👉በኛ , በምናውቃቸው , በቤተክርቲያን በህዝባችን ላይ ✅የማያቆርጥ ✅ከጌታ ብቻ የሆነ ✅በነገሮች / በሁኔታ ያልተገደበ ደስታ እንዲሆን በህብረት አባታችንን እንጠይቃለን 🙏 📖 ወደ ፊልጵስዩስ 4 4፤ ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው ሰላም ✅በኛ , በምናውቃቸው , በቤተክርቲያን በህዝባችን ላይ ✅ይህ እውነተኛ የሆነው ከአእምሮ እና ከሁኔታዎች የሚያልፈውን ሰላም እንዲሰፍን እንዲፀና በህብረት አባታችንን እንጠይቃለን 🙏 📖 ወደ ፊልጵስዩስ 4 7፤ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።

ሀሌሉያ መንፈስ ቅድስ የሚታገሰው ፍቅር ቸርነትን የሚያደርገው ፍቅር የማይቀና ፍቅር የማይመካ ፍቅር የማይታበይ ፍቅር የማይገባውን የማያደርግ ፍቅር የራሱን የማይወድ ፍቅር የማይበሳጨው ፍቅር በደልን የማይቆጥረው ፍቅር ከእውነት ጋር ደስ የሚለው ፍቅር ሁሉን የሚታገስ ፍቅር ሁሉን የሚያምን ፍቅር ሁሉን ተስፋ የሚያደርን የእግዚአብሔር ፍቅር እንድናፈራ መንፈስ ቅድስ ሆይ እንፈልጋለን ሀይልህ ጸጋ ብርታት አቅም ችሎታ ከአንተ ዘንድ ነውና ዛሬም ለእያንዳንዳችን እውነት የሆነውን ፍቅር በብዙ እንድናፈራ በኢየሱስም ጠየቅንህ እንፈልጋለን እውነተኛ ፍሬ ማፍራት ይሁን መንፈስ ቅድስ እርዳን አግዘን ደግፈን አሜን!!!

✅ አብዛኛው የመንፈስ ፍሬ ከእኛ ተጠቅመን ሌሎችን የምንጠቅምበት ናቸው። ከሰዎች ጋር ባለን ሕብረት በከፋተኛ ሁኔታ የሚረዱን በመልካም ባህሪ የሚያኖሩን ፍሬዎች ናቸው። በጣም አስፈላጊው ፍሬ በመጀመሪያ የተጠቀሰው #ፍቅር ነው። #ፍቅር የሁሉም ስጦታዎች መሰረት ነው። ክርስቲያን ያለ #ፍቅር ዋጋ የለውም። “ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ #ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 13፥2 በሐዋርያት ስራ እንደምናገኘው የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች መለያ እርስ በእርስ ያላቸው ፍቅር ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር መኖሩ በፍቅር እንድንኖር ይረዳናል ነገር ግን እኛም ልንታዘዝለት እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት ልናደርግ ይገባል በፍቅር ለመመላለስ መንፈስ ቅዱስን እንጋብዘው። “በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም።” — ሮሜ 5፥5

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው ፍቅር ✅በኛ , በምናውቃቸው , በቤተክርቲያን በህዝባችን ላይ ✅ይህ እውነተኛ የሆነው የማያልቀው ፍቅር እንዲሰፍን እንዲሰለጥን ሳያቆርጥ እንዲፈስ በህብረት አባታችንን እንጠይቃለን 🙏 📖 ወደ ገላትያ 5 22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 2ኛ ቆሮንቶስ 9 15፤ ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በጸራቅሊጦስ ምሽት መንፈስ ቅዱስ እንደ አዲስ እንዲነካን ሀይላችን እንዲያድስ ✅እንደ ሀዋሪያቱ በአንድ ልብ እና በአንድ ሀሳብ ሆነን ✅ በሙሉ እምነት ይሄ የመንፈስ እሳት በቤታችን በምናውቃቸው በሀገራችን እናበአለም ሁሉ ላይ እንጠራለን 📖 የሐዋርያት ሥራ 2 1፤ በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ 2፤ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። 3፤ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። 4፤ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በጸራቅሊጦስ ምሽት መንፈስ ቅዱስ እንደ አዲስ እንዲነካን ሀይላችን እንዲያድስ ✅እንደ ሀዋሪያቱ በአንድ ልብ እና በአንድ ሀሳብ ሆነን ✅ በሙሉ እምነት ይሄ የመንፈስ እሳት በቤታችን በምናውቃቸው በሀገራችን እናበአለም ሁሉ ላይ እንጠራለን 📖 የሐዋርያት ሥራ 2 1፤ በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ 2፤ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። 3፤ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። 4፤ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌የመንፈድ ቅዱስ ተልእኮ በክርስቲያን ህይወት part 9 ስለ እውነተኛ ንስሐ መግባት እና መመለስ ✅በሕይወታችን ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ✅ በንስሐ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታዎች ለመቀበል በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር እንቀርባለን 📖 ትንቢተ ኢዮኤል 2 13፤ ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ።

#ተሀድሶ ለማግኘት ምን እናድርግ 🙏የንስሐ ሕይወት ✅ እውነተኛ ንስሐ መግባት መመለስ ልምምድ ብቻ ሳይሆን ለወደደን በፍቅሩ ለሳበን አባት እግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ የመስጠት የሚፀፀት ልብ ጩኸት ነው። ጌታውን ሦስት ግዜ ከካደ በኋላ የጴጥሮስ በንስሐ መመለስ ምስክር ነው። የኢየሱስ ማለቂያ የሌለው ምህረት እና የጴጥሮስ የጸጸት የንሰሐ እንባ ታሪክን ለውጧል። የጴጥሮስ ፀፀት ለጌታ ስላለው ፍቅር የሦስት ግዜ እጥፍ ማረጋገጫ አሰገኝቶለታል። (ዮሐ 21:15-17) ✅ ውስጣዊ ንሰሐ የመላ ሕይወታችን ስር ነቀል ለውጥ ፣ ፀፀት ፣ በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር መመለስ የኀጢአት ማክተሚያ የፈፀምናቸውን መጥፎ ተግባራት በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው። ይህ ሁኔታ በእግዚአብሔር ምህረት ተስፋ በማድረግና በፀጋው ድጋፋ በመተማመን ሕይወትን የመለወጥ ምኞትና ውሳኔም ያስከትላል። ይህ ከልብ የሆነ መለወጥ የመንፈስ ስብራት እና ልባዊ ፀፀት ውጤታማ ሕመም እና ሐዘን ታጅቦ ቁርጥ ፈቃድ ስናደርግ መንፈስ ቅዱስ በኃይል እንድንሞላ ይረዳናል። “ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥” — ኢሳይያስ 1፥16 ✅ የጸጸት እና የንስሐ ሂደት ኢየሱስ መሀሪውን አባት ማዕከል ባደረገው የአባካኙ ልጅ ታሪክ ገልፆታል። በውሸት ዓለም ነፃነት መማረኩ የአባቱን ቤት ጥሎ መሄዱ ገንዘቡን ካባከነ በኋላ አስከፊ መከራ ውስጥ መውደቁ አሳማ ጠባቂ እስከመሆን መገደዱ አሳማዎች የሚመገቡትን ለመብላት እስከመፈለግ ክፋኛ መዋረዱ ነው።ይህ በውጭው አለም መታለሉ ዋጋ አስከፈለው። የአብዛኞቻችን ታሪክ ይህ ነው። ነገር ግን መጸጸቱ እና ጥፋተኝነቱን አምኖ እርምጃ መውሰዱ ወደ አባቱ ቤት ያደረገው ጉዞ ውጤታማ ሆነለት። የአባቱ ቸር አቀባበል ፣ የአባቱ ደስታ ፣ አዲስ ልብስ ፣ ቀለበቱና ድግሱ የአባቱን ጥልቅ ፍቅርና የምህረቱን ስፋት እንዲረዳ ሆነ። እኛም እንደዚሁ በንስሐ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታዎች ለመቀበል ራሳችንን በንስሐ እናዘጋጅ። መልካም የተባረከ የመንፈስ ቅዱስ (የጵራቅሊጦስ) በዓል ያድርግልን እንኳን አደረሳችሁ !!!

#ተሀድሶ ለማግኘት ምን እናድርግ 🙏የንስሐ ሕይወት ✅ እውነተኛ ንስሐ መግባት መመለስ ልምምድ ብቻ ሳይሆን ለወደደን በፍቅሩ ለሳበን አባት እግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ የመስጠት የሚፀፀት ልብ ጩኸት ነው። ጌታውን ሦስት ግዜ ከካደ በኋላ የጴጥሮስ በንስሐ መመለስ ምስክር ነው። የኢየሱስ ማለቂያ የሌለው ምህረት እና የጴጥሮስ የጸጸት የንሰሐ እንባ ታሪክን ለውጧል። የጴጥሮስ ፀፀት ለጌታ ስላለው ፍቅር የሦስት ግዜ እጥፍ ማረጋገጫ አሰገኝቶለታል። (ዮሐ 21:15-17) ✅ ውስጣዊ ንሰሐ የመላ ሕይወታችን ስር ነቀል ለውጥ ፣ ፀፀት ፣ በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር መመለስ የኀጢአት ማክተሚያ የፈፀምናቸውን መጥፎ ተግባራት በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው። ይህ ሁኔታ በእግዚአብሔር ምህረት ተስፋ በማድረግና በፀጋው ድጋፋ በመተማመን ሕይወትን የመለወጥ ምኞትና ውሳኔም ያስከትላል። ይህ ከልብ የሆነ መለወጥ የመንፈስ ስብራት እና ልባዊ ፀፀት ውጤታማ ሕመም እና ሐዘን ታጅቦ ቁርጥ ፈቃድ ስናደርግ መንፈስ ቅዱስ በኃይል እንድንሞላ ይረዳናል። “ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥” — ኢሳይያስ 1፥16 ✅ የጸጸት እና የንስሐ ሂደት ኢየሱስ መሀሪውን አባት ማዕከል ባደረገው የአባካኙ ልጅ ታሪክ ገልፆታል። በውሸት ዓለም ነፃነት መማረኩ የአባቱን ቤት ጥሎ መሄዱ ገንዘቡን ካባከነ በኋላ አስከፊ መከራ ውስጥ መውደቁ አሳማ ጠባቂ እስከመሆን መገደዱ አሳማዎች የሚመገቡትን ለመብላት እስከመፈለግ ክፋኛ መዋረዱ ነው።ይህ በውጭው አለም መታለሉ ዋጋ አስከፈለው። የአብዛኞቻችን ታሪክ ይህ ነው። ነገር ግን መጸጸቱ እና ጥፋተኝነቱን አምኖ እርምጃ መውሰዱ ወደ አባቱ ቤት ያደረገው ጉዞ ውጤታማ ሆነለት። የአባቱ ቸር አቀባበል ፣ የአባቱ ደስታ ፣ አዲስ ልብስ ፣ ቀለበቱና ድግሱ የአባቱን ጥልቅ ፍቅርና የምህረቱን ስፋት እንዲረዳ ሆነ። እኛም እንደዚሁ በንስሐ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታዎች ለመቀበል ራሳችንን በንስሐ እናዘጋጅ። መልካም የተባረከ የመንፈስ ቅዱስ (የጵራቅሊጦስ) በዓል ያድርግልን እንኳን አደረሳችሁ !!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌የመንፈስ ቅዱስ ተልእኮ በክርስቲያን ህይወት part 8 ✅እውነተኛ የመንፈስ ቅዱስ ተሀድሶ እና አሰራር በምእናን እና በቤተክርቲያን እንዲሰፍን 📖 ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20

🙏እውነተኛ ተሃድሶ እና የመንፈስ ቅዱስ አሰራር “እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።” — ኢሳይያስ 40፥31 ✅ #ተሃድሶ ማለት አዲስ የሆነ ለኃጢአት ወቀሳና ነስሀ መግባት ሲሆን ይህን ተከትሎ የሚመጣ ጥልቅ የሆነ እግዚአብሔርን ለመታዘዝ የሚመጣ ፋላጎትና መሻት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አቅም ማግኘት ነው። ✅ #ተሃድሶ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በመንፈሳዊ ነገራቸው ሙት የሆኑትን በክርስቶስ ህያው ወደ ሆነው ሕይወት የሚያመጣበት እና መንፈሳዊ ሕይወታቸው ቀዝቃዛ የሆነባቸውን የደከሙትን ውስጣዊ የክርስትና ሕይወት የሚያድስበት አሰራር ነው። ተሃድሶ አንገተ ደንዳኖችና በመንፈሳዊ ሕይወት ዝለት ውስጥ ያሉትን ኃይል በመስጠት ሁሉን ነገር አዲስ የሚያደርግ የመንፈሰ ቅዱስ ኃይል ነው። ✅ #ተሀድሶ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ በመንቀሳቀስ ለጌታ ያላቸውን ትጋትና ቅናት እንደገና የሚያድስበት የሚያነቃቃበት ለአዲስ አገልግሎት የሚያዘጋጅበት ልዪ የሆነ ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ መንፈሳዊ መነቃቃት ነው። “እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።” — ሐዋርያት 2፥3 ✅ #ተሀድሶ በመንፈስ ቅዱስ እሳት መነካት እና መዳሰስ ሲሆን በተነኩት አማኞች ሙሉ ለሙሉ ለውጥ የሚያመጣ ሲሆን ከነዚህ ሰዎች በመነሳት የብዙ ሰዎች ሕይወት ሲለወጥ እና ሲስፋፋ ማለት ነው። “ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ፤” — ሐዋርያት 2፥41 እውነተኛውን ተሀድሶ ለማግኘት ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? “እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።” — ሮሜ 12፥1 ✅ እሳት በሚገባ ተቀጣጥሎ መንደድ ከጀመረ ማንኛውም ነገር ከማቃጠል ወደ ኋላ አይመለስም ሆኖም እስኪቀጣጠል ተስማሚ የሆነ ቦታ ወይም ቁስ ይፈልጋል። ሁላችንም እንደምናውቀው እሳትን ለማቀጣጠል ደረቅ ተቀጣጣይ ቀላል እና ተፈልጦ የተዘጋጀ እንጨት መጠቀም እርጥበት ያለውን ማስወገድ በጣም የተሻለ አማራጭ መሆኑ ግልፅ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የመንፈስ ቅዱስ እሳት በሕይወታችን እንዲቀጣጠል ካስፈለገ ለጌታ የሚመች ንፁህ ልብ ይዘን በመቅረብ በሕይወተችን ያሉ ከጌታ መንፈስ ጋር የማይስማሙ ድርጊቶች ማስወገድ የግድ ይለናል ምክንያቱም ጌታ የሚያየው ልባችንን ስለሆነ። ጌታ የሚመች ልብ ያለውን ሰው ካገኘ እሳቱን ማቀጣጠል ይጀምራል። ✅ “ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 ቤተመቅደስ ናችሁ እስከተባልን ድረስ ራሳችንን በሚገባ ልንጠብቅ ይገባል ከክፉ ስራ እና እግዚአብሔርን ከማያስከብር ሕይወት በማራቅ መዘጋጀት አለብን ለውጥ የምንፈልግ ከሆነ ጌታ በምድር ላይ በነበረው የሦስት ዓመት ቆይታ ደቀመዛሙርቱን በጰንጠቆስጤ ቀን ሊወርድ ለነበረው የመንፈስ ቅዱስ እሳት ያዘጋጃቸው ነበር። ስለዚህ እኛም ልንዘጋጅ ይገባል ራሱን ያልሰጠ ሰው #በመታደስ ሕይወት ሊኖር አይችልም። ይቀጥላል

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 መንፈስ ቅዱስ አዲስ መገለጥን ጥበብን እና ሀይልን እንዲሰጠን ✅አባታችንን ካወቅነው እና ከተረዳነው በላይ እንድናውቀው ✅ የልቦና አይኖችን እንዲከፍትልን እና የመጠራታችን ተስፋ ምን እንደሆነ እንድንረዳ ዛሬም መንፈስ ቅዱሱን እንጋብዛለን 📖1ኛ ቆሮንቶስ 2 10፤ መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው። 11፤ በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው? እንዲሁም ደግሞ ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም።

በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ እኖራለሁ::" በክርስቶስ መኖር ማለት እግዚአብሔር ማወቅ መውደድ መታዘዝ ህብረት ማድረግ እግዚአብሔር ማምለክ ማለት ነው:: በክርስቶስ መኖር ማለት ቅርንጫፍ ከወይን ግንድ ጋር እንደተጣበቀ ከክርስቶስ ጋር በመንፈስ መጣበቅ : ከክስቶስ ጋር ስንጣበቅ ህያው ቅርንጫፍ እንሆናለን በወይኑ ግንድ ውስጥ ያለውን ምግብ ወደ ቅርንጫፎቹ እየፈሰሰ ህይወት ይሰጠናል የክርስቶስ መንፈስ በእኛ ውስጥ እየፈሰሰልን ከግንድ የተመገብን እየጠጣን የራሱን የእየሱስን ህይወት ይሰጠናል እንኖራለን እናብባለን ፍሬ እናፈራለን ሀሌሉያ!!! ፍሬአችንም ከግንድ ከዘራችን ከእየሱስ ጋር በእርሱ ስኖር የመንፈስ ፍሬአችን ብዙ ነው ✔️ፍቅር ...ይህ ፍቅር የራሱ የእግዚአብሔር የሆነ እንዲሁ የሚወደው ፍቅር ነው ስውን መውደድ የምንችልበት ፍቅር በልባችን ፈሶአል አሜን:: ✔️ደስታ ... ይህ ደስታ በመከራ በችግር ጊዜ የማይጠፋ በእግዚአብሔር ጸጋ የተሰጠን የመዳናችን ደስታ በሁኔታ ሳይሆን በተሰጠን ጸጋ አሜን:: ሀሌሉያ!!!/ ፊሊ 4:4/ ዩሐ 15:11/ ✔️ሰላም ....በኢየሱስ በማመናችን የመንፈስ ፍሬአችን አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል። አሜን ::ሀሌሉያ ፊሊ 4:7 ✔️ትግስት.....በመከራና በፈተና መጽናት.. በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤ኤፌ 4:2 ✔️ደግነት: በጎነትና : ታማኝነት ... ደግነት ... ምህረት ማድረግና ይቅር ባይነት አሜን :: ✔️በጎነት ... ለሰው ሁሉ መልካም ነገርን ማድረግ መፈለግ መመኘት አሜን :: ✔️ታማኝነት..ታማኝ ሰው መሆን ለእግዚአብሔር ታማኝ መሆን አሜን:: ✔️እምነት.. የመንፈሳችን ፍሬ እምነት ከሰማነው ከእግዚአብሄር ቃል ነው ቃሉ የሚለንን መቀበል በህይወታችን ላይ መግለጽ ቃሉን በማመን እንጂ በማየት አለመላለ አሜን:: ✔️እራስን መግዛት....እራሳችንን በመንፈስ ቅድስ ስር ማስገዛት ለቃሉ መገዛት መታዘዝ የስጋን ምኞት ፍላጎትን አለማድረግ ስጋችንን ጎሽመን ለመንፈስ ቅዱስ መገዛት አሜን:: እናመሰግንሀለን ይህንን የመንፈስ ፍሬ በእኛ ውስጥ ስላለ ስለሚበዛ ስለሚትረፈረፍ እናመሰግንሀለን መንፈስ ቅዱስ የፍሬአችን ምንጭ አንት ነህና ተባረክ አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የመንፈስ ቅዱስ ተልዕኮ በክርስቲያን ሕይወት part 6 የመንፈስ ፍሬ እንድናፈራ ✅ የመንፈስ ፍሬ የሆነውን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛትን በሰዎች ላይ እንዲገለጥ ✅እነዚህን ፍሬ እንድናፈራ ከሚያረገን ከክርስቶስ ጋራ እንድንጣበቅ ✅ፍሬ እንዳናፈራ ከሚያግተን ምንም አይነት መሰናከል እንድንላቀቅ በህብረት በአባታችን ፊት እንቆማለን 📖የዮሐንስ ወንጌል 15 4፤ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም።

🙏የመንፈስ ፍሬ ✅ መንፈስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ወደሚያፈራው ፍሬ የሚመራ ኃይል ነው። ፍሬ የሚያድግ እንጂ ሰው የሚሰራው አይደለም። ስለዚህ የመንፈስ ስራ ውጤት የመንፈሰ ፍሬ ተብሎ ይጠራል። የመንፈስ ፍሬ ውጤት ሰው በራሱ ጥረት የሚያመጣው ሳይሆን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በሚኖረው ሕብረት የሚገለጥ የእድገት ውጤት ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ዛሬ ፍቅር መሆን ደስተኛ መሆን፣ ሰለም መሆን እፈልጋለው ብሎ በራሱ ተለማምዶ ማምጣት አይችልም። ነገር ግን ከዛሬ ጀምሮ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት ማድረግ እጀምራለው ብሎ ቢነሳ እነዚህ የመንፈስ ፍሬዎች በሕይወቱ መገለጥ ይጀምራሉ። ስለዚህ የፍቅር ሰው ለመሆን ደስተኛ ሰው ለመሆን የሰላም ሰው ለመሆን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት ማድረግ እንጀምር። “በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም።” — ዮሐንስ 15፥4 ✅ አብዛኛው የመንፈስ ፍሬ ከእኛ ተጠቅመን ሌሎችን የምንጠቅምበት ናቸው። ከሰዎች ጋር ባለን ሕብረት በከፋተኛ ሁኔታ የሚረዱን በመልካም ባህሪ የሚያኖሩን ፍሬዎች ናቸው። በጣም አስፈላጊው ፍሬ በመጀመሪያ የተጠቀሰው #ፍቅር ነው። #ፍቅር የሁሉም ስጦታዎች መሰረት ነው። ክርስቲያን ያለ #ፍቅር ዋጋ የለውም። “ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ #ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 13፥2 በሐዋርያት ስራ እንደምናገኘው የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች መለያ እርስ በእርስ ያላቸው ፍቅር ነበር። ✅ ጳውሎስ በገላትያ 5:22 የሚጠቅሰው ከፍቅር ቀጥሎ ያለው የመንፈስ ፋሬ ደስታ ነው። #ደስታ ሁልግዜ በመንፈስ የተሞላ ሰው ከሚያሳየው ምልክቶች አንዱ ነው። በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል ጥልቅ የሆነ እና ዘለቄታ ያለው #ደስታ ይሰማዋል። ደስታውን በሁኔታ እና በነገሮች ላይ አያስደግፋም። ሁልግዜ አመስጋኝ ነው በጌታ ሀሴት የሚያደርግ ነው። ዕንባቆም 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥ ¹⁸ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። ✅ ሦስተኛው የመንፈስ ፍሬ #ሰላም ነው። በአዲስ ኪዳን #ሰላም ብዙ ትርጉም ካላቸው ቃላት አንዱ ነው። #ሰላም ማለት ከደኅንነት የሚገኙ ነገሮች ይኸውም ጸጥታ በረከት እረፋት የመሳሰሉ ማለት ሲሆን ይህ #ሰላም ምንም ችግር በሌለበት ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ ሳይሆን ችግር እያለ ችግሩ ውስጣችን ቦታ እንዳያገኝ የሚከላከል የተለየ #ሰላም ነው። “ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና #ሰላም ነው።” — ሮሜ 8:6 ከመንፈስ የሚገኘው #ሰላም አእምሮን ሁሉ የሚያልፋ ነው እርሱን ማግኘት የሚቻለው ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት በማድረግ ብቻ ነው “አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር #ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።” — ፊልጵስዩስ 4፥7 ✅ ሰለዚህ ይህን መልዕክት የምናነብ ሁሉ መንፈስ ቅዱስን አሰራር ያላወቅነው ብናውቀው የምናውቀውም ብንሆን የበለጠ ወደ እርሱ እንድንቀርብ ጌታ ይርዳን።

በእውነት መመራት.m4a22.81 MB