en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው በወጣት ዲቦራ ጌቱ ክፍል አንድ ሮሜ 13:8 እርስ በእርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ ሌላውን የሚወድ ህግን ፈጽሞታልና። *እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ የሚለውን ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለያየ ክፍል ተደጋግሞ እናገኘዋለን።በዚህም ክፍል እግዚአብሔር እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ይነግረናል። *በመጀመሪያ እርስ በእርስ ለመዋደድ ምን ያስፈልጋል? ፍቅር ያስፈልጋል። ⨳ፍቅር ምንድነው ? *ፍቅር ማለት ያለምንም ምላሽ ሰውን መውደድ ማለት ነው።እንዲሁም ፍቅር መስዋዕትነት እስከ መክፈል ያደርሳል። ለዚህም ክርስቶስ በፍቅር ሃጥያት ሳይኖርበት ስለኛ ሃጥያት ሲል ያለምንም ልዩነት (ሃጥያተኛ , ፃድቅ , ሴት , ወንድ , ትንሽ , ትልቅ) ብሎ ሳይከፋፍል ስለ ለሁላችን ያን ሁሉ መከራ ስለ ፍቅር ተቀብሎ መክፈል ማንችለውን እዳ ከፍሎ አዳነን , ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን , ልጆች አደረገን። ⨳ "እርስ በእርስ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ።" *በምድር እስካለን ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ዕዳ ቢኖር እርስ በእርሳችን መዋደድ ነው። ⨳ዕዳ ማለት ከአንድ ሰው በብድር ለመመለስ የተቀበልነው ሲሆን የተቀበልነውን ሙሉ በሙሉ እስከምንመልስ ባለ እዳ ነን። ⨳እግዚአብሔር እኛን በንፁህ ፍቅር ወዶናል።አንድያ ልጁን ለኛ ካለው ፍቅር የተነሳ እስከ ሞት አድርሶታል እና እሱ ለኛ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሰጠንን ንፁህ ፍቅር እኛም ከጎናችን ላሉት ሰዎች በነፃ መስጠት እንዳለብን ይነግረናል።ይህን ማድረግ እስካልቻልን ድረስ ባለ ዕዳዎች ነን። ⨳አጠገባችን ያሉትን ሰዎች መውደድ ያለብን ክርስቶስ እንዳስተማረን ያለ አንዳች ልዩነት (በሃይማኖት , የሃብት ደረጃ , የእውቀት ደረጃ , በብሔር ,...) ሳንመርጥ በእግዚአብሔር አምሳል በመፈጠራቸው ብቻ ንፁህ ፍቅር መስጠት እንዲሁም በምናስፈልጋቸው ሰዐት መስዋዕትነትን እስከመክፈል መውደድ እንዳለብን አስተምሮናል። ⨳እግዚአብሔር ህግን ሁሉ አቅልሎ እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ በሚል አንድ ቃል ጠቅልሎ ሰቶናል።ይህን ፈጸምን ማለት ሌሎች ህጎችን ሁሉ በተዘዋዋሪ ፈጽመናል ማለት ነው። ምክንያቱም በፍቅር ውስጥ ጥላቻ, ውሽት, ራስ ወዳድነት, አለመከባበር, መገዳደል... አይኖርም። ⨳በፍቅርም ከሃጥያት ሁሉ እንርቃለን። ⨳እግዚአብሔር ወደ ምድር የጠራን በፍቅር ተሳስረን በአንድነት እንድኖር ነው። #ስንቶቻችን የተጠራንበትን ምክንያት ተረድተን እየኖርነው ነው? ሮሜ13:11 "ከእንቅልፍ የምትነሱበት ሰዐት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ ካመንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።" እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm @eccrm @eccrm

#የንስሐ_ሕይወት_ማጠቃለያ #የመጨረሻ_ክፍል 1 #ንስሐ ማለት ለሰሩት ኃጢአት በመናዘዝ ለአዲስእና #ንፁሕ ሕይወት ራስን ማዘጋጀት ማለት ነው። “አቤቱ፥ #ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።” — መዝሙር 51፥10 2 #ንስሐ ለተረዳነው ለእግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ ለመስጠት በፍቅሩ የተማረከ እና የተሸነፈ የተፀፀተ ልብ ጩኸት ሊሆን ይገባል። “የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን #ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።”— መዝሙር 51፥17 3 #ንስሐ በኃጢአት ምክንያት ከአብ የራቀውን ማንነት እንደገና በኢየሱስ በኩል የምናድስበትና የምንለውጥበት ታላቅ #ምስጢር ነው። “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም #አሳርፋችኋለሁ። — ማቴዎስ 11፥28 4 እንድንለወጥ እና #ንስሐ እንድንገባ የቀረበው የኢየሱስ ጥሪ ከእርሱ በፊት እንደነበሩት ነቢያት ጥሪ በመጀመሪያ ደረጃ ማቅ በመልበስ አመድ በመነስነስ እንዲሁም በፆም እና ተጋድሎ ላይ የሚያተኩር ውጫዊ ሳይሆን ልባዊ ወይም #ውስጣዊ መለወጥን የሚጠይቅ ነው። ያለዚህ ንስሐ ፍሬ ቢስ ከንቱ ይሆናል። “ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ።” — ኢዮኤል 2፥13 5 ውስጣዊ #ንስሐ የመላ ሕይወታችን ስርነቀል ለውጥ ፀፀት በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር መመለስ የኀጢአት ማክተሚያ እና የፈፀምናቸው መጥፎ ተግባራትን በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው። “አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።”— ሰቆ. 5፥21 6 እግዚአብሔርን የሚያስደስተው እውነተኛ የተሰበረ የተፀፀተ ለመለወጥ የቆረጠ ልብ ነው። #የኀጢአታችን_ትልቅ_መሆንና_ትንሽ_መሆን_አይደለም የእግዚአብሔር ምህረት እንዲያገኘን የሚያደርገው። 7 የንስሐችን ፍሬ የሰማይ ብርሃን በልባችን ቷ ብሎ እንዲበራ፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር ተቆጣጥሮን በታደሰ ማንነት ለጌታ ክብር የምንኖረው #አዲስ_ሕይወት ሊሆን ይገባዋል። “ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።” — ኢሳይያስ 1፥18 8 ወደ ፀጋው ዙፍን በመቅረብ እንጂ ከአሁን በኋላ እተዋለው በሚል ፉከራ እና ሽለላ ኃጢአትን ለማቆም #ውጤታማ አያደርገንም። “እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።” — ዕብራውያን 4፥16 9 የእግዚአብሔር ቃል ዋናው የእግዚአብሔር ፀጋ ነው ቃሉ በሙላት እኛን ከተቆጣጠረን የማናሸንፈው ኃጢአት አይኖርም። “የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤” — ዕብራውያን 4፥12 10 የእግዚአብሔር ፍጹም ጻድቅነት ባይኖር ኖሮ መናዘዣ ቦታም፣ ይቅርታ የሚለመንም አይኖርም ነበር። የእኛ ኀጢአት ከእርሱ ጽድቅ ጋር ሲፋጠጥ የእርሱ #የፍቅር_ሚዛን_ከፍ_ያደርገናል። “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥”— ኤፌሶን 2፥5 11 ዛሬስ እኛ #ለንስሐ በመዘግየታችን ስንት ነገር በሕይወታችን እየተከናወነ ይሆን ? በማይመች እና በማይጠቅም ሕይወት ልንኖር አልተጠራንም። ዛሬም ፍቅር የሆነው እግዚአብሔር እጁን ዘርግቶ ሊቀበለን እየጠበቀን ነው። “አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።” — ሐዋርያት 22፥16 12 መጥመቁ ዮሐንስ ሰዎች እንዲናዘዙና ለምልክትም በውሃው ውስጥ እንዲጠመቁ ብቻ እየነገረ አልኖረም። ይልቁን በጣም #ተግባራዊ ዝርዝር ይሰጣቸው ነበር። “ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ …ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ፣ በማንም ግፍ አትሥሩ… ደመወዛችሁ ይብቃችሁ…” (ሉቃ 3፥10-14)። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#ንስሐ_በተግባራዊ_መንገድ_ፍሬ_ያፈራል #ክፍል_አምስት ✅ መጥመቁ ዮሐንስ ሰዎች እንዲናዘዙና ለምልክትም በውሃው ውስጥ እንዲጠመቁ ብቻ እየነገረ አልኖረም። ይልቁን በጣም ተግባራዊ ዝርዝር ይሰጣቸው ነበር። “ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ …ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ፣ በማንም ግፍ አትሥሩ… ደመወዛችሁ ይብቃችሁ…” (ሉቃ 3፥10-14)። ይህ ምክር ሐዋርያው ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ልጁ ለጢሞቴዎስ ከመከረው ምክር ጋር ይመሳሰላል። ራስህን ለመልካም ነገር አሰልጥን ብሎ ይመክረዋል ማንኛውም ሕይወት ስልጠና ነው። ስለዚህ እኛም መልካም ፍሬ ለማፍራት ራሳችንን ማሰልጠን እና ማስለመድ አለብን። እንደዚህ ከሆነ ንስሐችን ውጤታማ ይሆናል። #እውነተኛ_ንስሐ_በጌታ_ምሕረት_ይታመናል “ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።” — ዕብራውያን 4፥15 ✅ ያለንበትን ውድቀት፣ የሰመጥንበትን የኀጢአት ረግረግ ስናስተውል፣ ‘እንዴት ከዚህ እንወጣለን? አምላክስ በምን መንገድ ይታረቀናል?’ የሚል ፍርሀትና ተስፋ መቁረጥ ይመጣብን ይሆናል። ከእኛ ዘንድ እግዚአብሔርን ሊያባብል ወይም በቃል ይሁን በሥራው ሊያስገርም፣ ምሕረትም ከእጁ ፈልቅቆ ሊያመጣልን የሚችል ምንም ተግባር የለንም። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድካማችንን አይቶ ራራልን። “…ይህ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው” ያለው ከአባቱ ዘንድ በደሙ በኩል ለእኛ የሚሰጠውን ስርየት ዋስትና ሲያረጋጥልን ነው። ተስፋ ቢስ ኀጢአተኛ በዚህ የኪዳን ደም ተመክቶ “ስለ ልጅህ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስትል ማረኝ” ብሎ ሊማጠን ይችላል። የልዑል አምላክን ምሕረትም በነጻ ይቀበላል። ትምክህታችን ይኸው ብቻ ነው። በዚህ የደም አምባ ውስጥ ምህረት እናገኛለን፤ ከመዐትም እናመልጣለን ክብር ለስሙ ይሁን። ይቀጥላል @eccrm @eccrm @eccrm

ንስሐ ካደረክ ካደረክሽ ምን ያህል ግዜ ሆኖሀል? እውነት ግን ንስሐ የማናደርገው ንፁህ ስለሆንን ነው? ወይስ ስለ ንስሐ ያለን አመለካከት ችግር? የንስሐ እንቅፋቶች ምንድን ናቸው? ንሰሐ ያስፈልጋል ብለህ ታምናለህ? መልስህ አዎ ከሆነ ራስህን ጠይቀው? ሙሉ መልሱን በዚህ ሊንክ ግባና ታገኘዋለህ @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#ንስሐ #ክፍል_አራት #ንስሐ_ልባዊ_ትህትና_ማሳየት_ነው “እኔ ባሪያህ ዛሬ በፊትህ ስለ ባሪያዎችህ ስለ እስራኤል ልጆች ሌሊትና ቀን የምጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ ጆሮህ ያድምጥ፥ ዓይኖችህም ይከፈቱ፤ በአንተ ላይም ያደረግነውን የእስራኤልን ልጆች ኃጢአት እናዘዝልሃለሁ፤ #እኔና_የአባቴም_ቤት_በድለናል።” — ነሀምያ 1፥6 👉 ነህምያ ብዙ ምክንያት መደርደር እየቻለ ከምክንያት አልፎ ራሱን ወቀሰ ልባዊ ትህትና በደልን ማላከክ፣ ሰበብ መደርደር፣ ‘እነ አገሌም አድርገዋል’ እያሉ እኩያ መፈለግ፣ ሲከፋም ስለ በደላችን አገልጋዮችን መውቀስ ወይም በስውር ልብ ማማት ከንስሓ መንገድ መራቅ ነው። “እኔ በድያለሁ” የሚል ትሑት ሰው፣ ልቡ በእግዚአብሔር የተማረከ ውጤታማ ንስሐ የሚያደርግ ነው። ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ሲተያይ ሌላ ቋንቋ ሊኖረው አይችልም። “በደረሰብንም ነገር ሁሉ አንተ ጻድቅ ነህ፤ አንተ እውነት አድርገሃልና፤ እኛም ኀጢአት አርገናል።” (ነህ 9፥33) 👉 የእግዚአብሔር ፍጹም ጻድቅነት ባይኖር ኖሮ መናዘዣ ቦታም፣ ይቅርታ የሚለመንም አይኖርም ነበር። የእኛ ኀጢአት ከእርሱ ጽድቅ ጋር ሲፋጠጥ የሚጠብቀን ቅጣት እንዲነሣልን መማጠኛም ነው ንስሓ። እንኳን እርሱ ጻድቅ ሆነ! የዓለሙ ሁሉ እንቅስቃሴ በምን ይመዘን ነበር? የሚምረን እኮ ጽድቁን አዛንፎ ሳይሆን ፍቅሩን አብዝቶ ነው። በዚህ ደግሞ ደስ ሊለን ይገባል። እግዚአብሔርን “አንተ ጻድቅ ነህ” ማለት ክብሩን መግለጽ፣ ልባዊ ትሕትናም ማሳየት ነው። #የመለወጥ_መገለጫ 👉 የፀፀት እና የንስሐ ሂደት ኢየሱስ መሀሪውን አባት ምሳሌ ባደረገው የጠፋው ልጅ ታሪክ ገልፆታል። በሕልም ዓለም ነፃነት መማረኩ የአባቱን ቤት ጥሎ መሄዱ ገንዘቡን ካባከነ በኋላ አስከፊ መከራ ውስጥ መውደቁ አሳማ ጠባቂ እስከመሆን መገደዱ አሳማዎቹ የሚመገቡትን ገለባ ለመብላት እስከ መፈለግ ክፉኛ መዋረዱ ይሄ ሁሉ ችግር የደረሰበት ቢሆንም ወደራሱ ወደልቡ ተመልሶ ማሰላሰሉ እና መፀፀቱ ከዚያም አልፍ በአባቱ ፊት ጥፋተኝነቱን ለማመን መወሰኑ የመልሱ ጉዞ ሕይወት ዘመኑን ያሳመረ ሆነለት ። ከዚያም አልፎ የአባቱ ቸር አቀባበል የአባቱ ደስታ ድግሱ ሁሉ እነዚህ ሁሉ የልጁ ለመለወጥ ያደረገው ውሳኔ ያስከተለው ክስተት ነው። “ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥”— ሉቃስ 15፥18 👉 ከዚህ ክስተት የምንማረው ዋነኛው ነገር ምንድን ነው። ዛሬ ነገ ንስሐ እገባለው እያልን ለዘገየን ይህ ጥሩ ምሳሌ ነው ብዬ አስባለው። ይህ ልጅ ከዚህ በላይ ቢዘገይ ኖሮ ምናልባት በረሀብ ሟች ነው ብዬ አስባለው። ዛሬስ እኛ ለንስሐ በመዘግየታችን ስንት ነገር በሕይወታችን እየተከናወነ ይሆን ? በማይመች እና በማይጠቅም ሕይወት ልንኖር አልተጠራንም ዛሬም ፍቅር የሆነው እግዚአብሔር እጁን ዘርግቶ ሊቀበለን እየጠበቀን ነው። ውሳኔ ያስፈልገናል። ወደ ቤቱ ተመልስን በእረፍት ልንኖር ይገባናል። “እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።”— ሉቃስ 15፥10 ይቀጥላል @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#ፍሬያማ_ንስሐ #ክፍል_3 “ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።” — ኢሳይያስ 1፥18 👉 ፍሬያማ ንስሐ በቃሉ መለኪያ ራሱን ይፈትሻል ንስሓ የሚያስገባን ነገር ምንድን ነው? ሰው ስለተቀየመን ነው? እኛ በውስጣችን ቆሻሻነት ስለተሰማን ነው? ‘ንስሓ ግቡ’ ተብለን ስለተወተወትን ነው? ወይስ እንዲያው ሰዎች ሲገቡ ስላየን አኔም ልግባ ብለን ነው? እውነተኛ የኀጢአት ወቀሳ ከእውነተኛው መለኪያ መንሸራተታችን ሲገባን የሚመጣ ነገር ነው። በቅዱስ ቃሉ ውስጥ ባሉት መለኪያዎች ራሳችንን ስንፈትሽና ከደረጃው የወደቅን መሆናችን ሲገባን ዋይታችን ፍሬያማ እና እውነተኛ መሠረት ያገኛል። #ባሉበትም_ቦታ_ቆመው_ከአምላካቸው_ከእግዚአብሔር_ሕግ_መጽሐፍ_ሩብ_ቀን_አነበቡ_የቀረውን_ሩብ_ቀን_ደግሞ_ንስሓ_በመግባትና_ለአምላካቸው_ለእግዚአብሔር_በመስገድ_አሳለፉ።” (ነህ 9፥3)። 👉 አሁን በእኛ መካከል ሰዎች ‘ንስሓ ገብተዋል፣ አልገቡም’ እያልን ግራ እስኪገባን የሚያደርሰን ምን ይሆን? የኀጢአት ወቀሳው በእግዚአብሔር ቃልና በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ወደየሰዉ ልብ ስላልገባ ይሆን? ንስሓችን እውነተኛ የሚሆነው ያደረግሁት፣ የኖርኩት በፍጹሙ የእግዚአብሔር ቃል ፊት ሊቆም የሚችል ነውን? ብዬ የምሬን የጠየቅሁ እንደሆን ነው። ‘የወቀሰኝ የሰማይና የምድር ጌታ ልዑል እግዚአብሔር ነው’ ያልሁ ጊዜ ነው። የንስሐችን ፍሬ የሰማይ ብርሃን በልባችን ቷ ብሎ እንዲበራ፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር ተቆጣጥሮን በታደሰ ማንነት ለጌታ ክብር የምንኖረው አዲስ ሕይወት ሊሆን ይገባዋል። 👉 አንዳንድ ግዜ የንስሐ መንገዳችን ፍሬያማ የማይሆንበት ምክንያት አለ። ለምሳሌ አብዛኛው ሰው ንስሐ ማድረግ የሚፈልገው የጌታን ስጋ እና ደም መውሰድ ሲፈልግ ነው። ይህ አካሄድ ፍሬያማ አያደርገንም ምክንያቱም ንስሐ ከውስጥ በሚመጣ ፀፀት እና ጩኸት የታጀበ ሊሆን ይገባል። ጊዜ ወስደን ራሳችንን መርምረን ለመለወጥ ቁርጥ ፈቃድ አድርገን ዝግጁ መሆን አለብን። ያለበለዚያ ታላቅ የሆነውን ምስጢር ልምድ እናደርገው እና ኃይሉን እናጣበታለን። 👉 ሌላው የንስሐን ፍሬያማነት የሚከለክለው ነገር ቁርጥ ፈቃድ አለማድረግ ነው። አንዳንድ ግዜ ከኃጢአት ጋር ፍቅር የያዘን እስኪመስል አንለቅ የምንለው የኀጢአት አይነት አለ። ንስሐ ገብተን ደግመን እዚያ ላይ የምንገኝበት ግዜ አለ። ይህ ሁኔታ ቁርጥ ፈቃድ ካለማድረግ እና ወደ እግዚአብሔር የፀጋ ዙፋን ካለመቅረብ የሚመጣ ችግር ነው። ወደ ፀጋው ዙፍን በመቅረብ እንጂ ከአሁን በኋላ እተዋለው በሚል ፉከራ እና ሽለላ ኃጢአትን ለማቆም ውጤታማ አያደርገንም። #እንግዲህ_ምሕረትን_እንድንቀበል_በሚያስፈልገንም_ጊዜ_የሚረዳንን_ጸጋ_እንድናገኝ_ወደ_ጸጋው_ዙፋን_በእምነት_እንቅረብ።”— (ዕብራውያን) 4፥16 ወደ ፀጋው ዙፋን በእምነት መቅረብ አለብን ቃሉን ግዜ ሰጥተን ማጥናት እና መፀለይ አለብን። የእግዚአብሔር ቃል ዋናው የእግዚአብሔር ፀጋ ነው ቃሉ በሙላት እኛን ከተቆጣጠረን የማናሸንፈው ኃጢአት አይኖርም። ሰው የተሞላውን ነው ኑሮው የሚሆነው ስለዚህ ቃሉን እንሞላ። ቃሉ የከበደንን ሁሉ ያሸንፍል። “የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤” — ዕብራውያን 4፥12 ይቀጥላል @eccrm @eccrm @eccrm

#ንስሐ ክፍል 2 #ንስሐ_ፈዋሽ_መድሐኒት_ነው 👉 ንስሓ የመጽሐፍ ቅዱስ ቋንቋ ነው። መሠረታዊ የክርስትና አስተሳሰብ ነው። ሁሉን ነገር ውብ አድርጎ የሠራው ጥበበኛ አምላክ ፍጥረቱ ተበላሽቶበታል። ኀጢአት የሚባል የንጽሕና ጉድለት ዐመፅና መሳሳት ወደ ሰው ልጅ ልብ ዘልቆ ሰውንም ፍጥረትንም በክሏል። ቅዱሱንና እውነተኛውን አምላክ አሳዝኗል። ስለዚህ ለበደል ይቅርታ መለመን፣ የኀጢአት ኑዛዜ ማቅረብ፣ ከተሳሳቱበትም መመለስ የመጽሐፍ ቅዱሱ ንስሓ ዐይነተኛ ባሕርያት ናቸው። ለንስሓ ባይተዋር የሚሆነው ሰው ለመጽሐፍ ቅዱስም ባይተዋር የሆነ ነው። ከዘፍጥረት እስከ ራእየ ዮሐንስ የተዘረጋው የንስሓ ጎዳና ነው። #እውነተኛ_ንስሐ_ውሰጣዊ_ነው 👉 እንድንለወጥ እና ነስሐ እንድንገባ የቀረበው የኢየሱስ ጥሪ ከእርሱ በፊት እንደነበሩት ነቢያት ጥሪ በመጀመሪያ ደረጃ ማቅ በመልበስ አመድ በመነስነስ እንዲሁም በፆም እና ተጋድሎ ላይ የሚያተኩር ውጫዊ ሳይሆን ልባዊ ወይም ውስጣዊ መለወጥን የሚጠይቅ ነው። ያለዚህ ንስሐ ፍሬ ቢስ ከንቱ ይሆናል። “ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ።” — ኢዮኤል 2፥13 ውስጣዊ ንስሐ የመላ ሕይወታችን ስርነቀል ለውጥ ፀፀት በሙሉ ልባችን ወደ እግዚአብሔር መመለስ የኀጢአት ማክተሚያ እና የፈፀምናቸው መጥፎ ተግባራትን በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው። ይህ ሁኔታ በእግዚአብሔር ምህረት ተስፋ በማድረግ እና በፀጋው ኃይል በመተማመን ሕይወትን የመለወጥ ምኞት እና ውሳኔ ያስከትላል። ይህ ውስጣዊ መለወጥ የመንፈስ ስብራት እና ልባዊ ፀፀት በሚሏቸው ውጤታማ ሕመም እና ሀዘን የታጀበ ነው “አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።” — ሰቆ. 5፥21 #የልባችን_ፀፀት_ዋና_ነገር_ነው 👉 እግዚአብሔርን የሚያስደስተው እውነተኛ የተሰበረ የተፀፀተ ለመለወጥ የቆረጠ ልብ ነው። #የኀጢአታችን_ትልቅ_መሆንና_ትንሽ_መሆን_አይደለም የእግዚአብሔር ምህረት እንዲያገኘን የሚያደርገው። የኔ ኃጢአት ይቅር ማይባል ነው ብለን ከእግዚአብሔር ምሕረት (ከንስሐ) ልንረቅ አይገባም። የልባችን ተፀፅቶ መመለስ ዋናው ነገር ነው። በሳኦል ውድቀት እና በዳዊት እንደልቤ ያስባለ ስኬት ውስጥ ያለው ልዩነት የተሰበረ እና የተዋረደ ልብ ነው። ሁለቱም ስህተት ቢሰሩም ከሁለቱ የበለጠ ትልቅ ኃጢአት የሰራው ዳዊት ነው የሰው ሚስት ደፈረ ከዛም አልፎ በስልጣኑ ተጠቅሞ ንፁህ ሰውን አስገደለ ነገር ግን በደሉ ሲገባው በእውነተኛ በተፀፀተ ልብ በእግዚአብሔር ፊት ተነኘ። ዛሬም እኛ የእግዚአብሔርን ምህረት አስበን በእውነተኛ በተዋረደ ልብ በፊቱ ብንቀርብ ሁልግዜ በፍቅር የሚያየን አምላክ #አጥቦ_ቀድሶ_አንፅቶ_እንደገና_ለአዲስ_ሕይወት_ያዘጋጀናል። ይቀጥላል @eccrm @eccrm

#የንስሐ_ሕይወት 👉 ንስሐ ማለት ለሰሩት ኃጢአት በመናዘዝ ለአዲስእና ንፁሕ ሕይወት ራስን ማዘጋጀት ማለት ነው። ንስሐ መታጠብ ልንለው እንችላለን። ንስሐ የመጀመሪያ ወደ እግዚአብሔር የመመለስ የመዳን እርምጃ ነው። በኃጢአት ምክንያት ከአብ የራቀውን ማንነት እንደገና በኢየሱስ በኩል የምናድስበት ታላቅ ምስጢር ነው። “አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።” — መዝሙር 51፥10 #ከጥምቀት_በኃላ_ለምን_ንስሐ_አስፈለገ ? 👉 በክርስቶስ ማመን የጥምቀት አዲሱ ልደት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታና የምንወስደው የክርስቶስ ስጋ እና ደም ቤተክርስቲያን ቅድስትና አለነውር እንደሆነች ሁሉ እኛንም ቅዱስ እና አለነውር አድርጎናል። “እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።”— ኤፌሶን 5፥27 ይሁን እንጂ ክርስትናን በመቀበል ያገኘነው አዲስ ሕይወት የሰውን ተፈጥሯዊ ድክመት በስጋ ያለ የኀጢአት ፈተናን ማዘንበልን ሙሉ በሙሉ አላቆመም። ለዚህም ነው የንስሐ ምስጢር የተዘጋጀልን። #ንስሐ_ከውስጥ_የሆነ_ጩኸት_ሊሆን_ይገባል 👉 ወደ እግዚአብሔር የመመለስ እና የመለወጥ ጥሪ ግን አንድ ጊዜ የሚያበቃ ሳይሆን በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ቀጣይነት ያለው ነው። ንስሐ የመግባት የመመለስ ሕይወት ድርጊት ብቻ መሆን የለበትም። ንስሐ ለተረዳነው ለእግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ ለመስጠት በፍቅሩ የተማረከ እና የተሸነፈ የተፀፀተ ልብ ጩኸት ሊሆን ይገባል። “የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።” — መዝሙር 51፥17 ይቀጥላል @eccrm @eccrm

#የንስሐ_ሕይወት 👉 ንስሐ ማለት ለሰሩት ኃጢአት በመናዘዝ ለአዲስእና ንፁሕ ሕይወት ራስን ማዘጋጀት ማለት ነው። ንስሐ መታጠብ ልንለው እንችላለን። ንስሐ የመጀመሪያ ወደ እግዚአብሔር የመመለስ የመዳን እርምጃ ነው። በኃጢአት ምክንያት ከአብ የራቀውን ማንነት እንደገና በኢየሱስ በኩል የምናድስበት ታላቅ ምስጢር ነው። “አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።” — መዝሙር 51፥10 #ከጥምቀት_በኃላ_ለምን_ንስሐ_አስፈለገ ? 👉 በክርስቶስ ማመን የጥምቀት አዲሱ ልደት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታና የምንወስደው የክርስቶስ ስጋ እና ደም ቤተክርስቲያን ቅድስትና አለነውር እንደሆነች ሁሉ እኛንም ቅዱስ እና አለነውር አድርጎናል። “እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።”— ኤፌሶን 5፥27 ይሁን እንጂ ክርስትናን በመቀበል ያገኘነው አዲስ ሕይወት የሰውን ተፈጥሯዊ ድክመት በስጋ ያለ የኀጢአት ፈተናን ማዘንበልን ሙሉ በሙሉ አላቆመም። ለዚህም ነው የንስሐ ምስጢር የተዘጋጀልን። #ንስሐ_ከውስጥ_የሆነ_ጩኸት_ሊሆን_ይገባል 👉 ወደ እግዚአብሔር የመመለስ እና የመለወጥ ጥሪ ግን አንድ ጊዜ የሚያበቃ ሳይሆን በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ቀጣይነት ያለው ነው። ንስሐ የመግባት የመመለስ ሕይወት ድርጊት ብቻ መሆን የለበትም። ንስሐ ለተረዳነው ለእግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ ለመስጠት በፍቅሩ የተማረከ እና የተሸነፈ የተፀፀተ ልብ ጩኸት ሊሆን ይገባል። “የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።” — መዝሙር 51፥17 ይቀጥላል @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው እርስ በእርሳችሁ #ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ ሌላውን የሚወድ ህግን ፈጽሞታልና። ሮሜ 13:8 *#እርስ_በእርሳችሁ_ተዋደዱ የሚለውን ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለያየ ክፍል ተደጋግሞ እናገኘዋለን።በዚህም ክፍል እግዚአብሔር እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ይነግረናል። *በመጀመሪያ እርስ በእርስ #ለመዋደድ ምን ያስፈልጋል? #ፍቅር ያስፈልጋል። ⨳ፍቅር ምንድነው ? *ፍቅር ማለት ያለምንም ምላሽ ሰውን #መውደድ ማለት ነው።እንዲሁም ፍቅር መስዋዕትነት እስከ መክፈል ያደርሳል። ለዚህም ክርስቶስ በፍቅር ሃጥያት ሳይኖርበት ስለኛ ሃጥያት ሲል ያለምንም ልዩነት (ሃጥያተኛ , ፃድቅ , ሴት , ወንድ , ትንሽ , ትልቅ) ብሎ ሳይከፋፍል ስለ ለሁላችን ያን ሁሉ መከራ ስለ ፍቅር ተቀብሎ መክፈል ማንችለውን እዳ ከፍሎ አዳነን , ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን , ልጆች አደረገን። ⨳ "እርስ በእርስ #ከመዋደድ_በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ።" *በምድር እስካለን ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ዕዳ ቢኖር እርስ በእርሳችን #መዋደድ ነው። ⨳ዕዳ ማለት ከአንድ ሰው በብድር ለመመለስ የተቀበልነው ሲሆን የተቀበልነውን ሙሉ በሙሉ እስከምንመልስ ባለ እዳ ነን። ⨳እግዚአብሔር እኛን በንፁህ ፍቅር ወዶናል።አንድያ ልጁን ለኛ ካለው ፍቅር የተነሳ እስከ ሞት አድርሶታል እና እሱ ለኛ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሰጠንን ንፁህ ፍቅር እኛም ከጎናችን ላሉት ሰዎች በነፃ መስጠት እንዳለብን ይነግረናል።#ይህን_ማድረግ_እስካልቻልን_ድረስ_ባለ_ዕዳዎች_ነን። ⨳አጠገባችን ያሉትን ሰዎች #መውደድ ያለብን ክርስቶስ እንዳስተማረን ያለ አንዳች ልዩነት (በሃይማኖት , የሃብት ደረጃ , የእውቀት ደረጃ , በብሔር ,...) ሳንመርጥ በእግዚአብሔር አምሳል በመፈጠራቸው ብቻ #ንፁህ_ፍቅር መስጠት እንዲሁም በምናስፈልጋቸው ሰዐት መስዋዕትነትን እስከመክፈል መውደድ እንዳለብን አስተምሮናል። ⨳እግዚአብሔር ህግን ሁሉ አቅልሎ #እርስ_በእርሳችሁ_ተዋደዱ በሚል አንድ ቃል ጠቅልሎ ሰቶናል።ይህን ፈጸምን ማለት ሌሎች ህጎችን ሁሉ በተዘዋዋሪ ፈጽመናል ማለት ነው። ምክንያቱም በፍቅር ውስጥ ጥላቻ, ውሽት, ራስ ወዳድነት, አለመከባበር, መገዳደል... አይኖርም። ⨳በፍቅርም ከሃጥያት ሁሉ እንርቃለን። ⨳እግዚአብሔር ወደ ምድር የጠራን በፍቅር ተሳስረን በአንድነት እንድኖር ነው። #ስንቶቻችን የተጠራንበትን ምክንያት ተረድተን እየኖርነው ነው? ሮሜ13:11 "ከእንቅልፍ የምትነሱበት ሰዐት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ ካመንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።" እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm@eccrm @eccrm@eccrm

እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው #መስማትም_በእግዚአብሔር_ቃል_ነው።” — ሮሜ 10፥17 🧏🧏🧏🧏🧏🧏🧏🧏🧏 👉 እምነት ማለት ሀይማኖት አይደለም። እምነት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት እና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር በመስማማት የሚገኝ አስደናቂ ኃይል ነው። ብዙ ሰዉ ሀይማኖት አለው ነገር ግን እምነት የለውም። እግዚአብሔርን ከሚያስደስተው ዋና ነገር ሀይማኖተኛ መሆን ሳይሆን የእምነት ሰው መሆን ነው። “ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።” — ዕብራውያን 11፥6 👉 የእግዚአብሔር ቃል #የእምነት ሰው ያደርገናል። ከዚያም አልፎ ከመጥፋት እና የማይጠቅመንን ሕይወት ከመኖር ያድነናል። ሰው የእግዚአብሔርን ዕውቀት ባጣበት ነገር ላይ ሁልግዜ ተሸናፊ ሲሆን #የእግዚአብሔርን_እውቀት_መገለጥ_ባገኘበት_ነገር_ሁልግዜ_አሸናፊ_ነው። በዚህ ምድር አሸናፊ ሆነን ለመኖር ብቸኛው መሳሪያችን የእግዚአብሔር ቃል ነው።