en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ለብርታት እና ለሀይል መንፈስ ✅ ለግላችን, ለቤተሰብ ወዳጆች ✅ለቤተክርስቲያችን እና ለመሪዎች ✅ ለደከሙ ነፍሳት ሁሉ ትንቢተ ኢሳይያስ 40 31፤ እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።

01 Track 1_(ALLConverter_1).mp36.30 MB

Worship song

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በዚህ ጊዜ ላይ የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ እየጣሉ ስለሚይገለግሉ የህክምና ባለሞያዎች እና የተለያዩ አገልግሎትን እየሰጡ ስላሉ ሰራተኞች ሁሉ ✅ የእግዚአብሔር መንፈስ በጥበብ , በማስተዋል , በፍቅርና በሰላም እንዲሞላቸው ✅ ሁሉን በሚችል ጥላው ስር እንዲያሳድራቸው በጌታችን በእየሱስ ስም እንፀልይለን መዝሙረ ዳዊት 23 1፤ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። 2፤ በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። 3፤ ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። 4፤ በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። 5፤ በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። 6፤ ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።

የአልዓዛር ከሞት መነሳት ደግሞ አማኙ በምስጢረ ጥምቀት አማካይነት በክርስቶስ የፋሲካ ምስጢር ውስጥ መግባቱን የሚያመለክት የእድሳት ምልክት ነው። በመንፈስ ቅዱስ ተግባር እና ኃይል ክርስቲያን እንደ አዲስ ፍጥረት በመሆን በሕይወቱ የሚራመድ ሰው ነው - ለሕይወት የተፈጠረ እና ወደ ሕይወት የሚሄድ ሰው ነው። ሐዘናችንን ሐዘኑ በማድረግ ርህራሄውን የሰጠንን ልጇን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳየንን ተምሳሌት በመከተል  ርህሩህ እንድንሆን ድንግል ማርያም እንድትረዳን ልንማጸናት ይገባል። በፈተና እና በመከራ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እያንዳንዳችን ቅርብ እንሆን ዘንድ፣ ለእነሱ ሞትን የሚያሸንፍ እና ሕይወትን የሚሰጥ የእግዚአብሔር ፍቅር እና ርህራሄ ነፀብራቅ መሆን እንችል ዘንድ እርሷ እንድትረዳን አማላጅነቷን መማጸን ይኖርብናል።

ዛሬም ቢሆን ኢየሱስ “ድንጋዩን አንሱ” በማለት ይናገራል። እግዚአብሔር ለመቃብር አልፈጠረንም፣ እርሱ የፈጠረን ለሕይወት፣ ለውብት እና ለደስታ ነው የፈጠረን። ነገር ግን መጽሐፈ ጥበብ እንደ ሚናገረው “ሞት ወደ ዓለም የገባው በዲያብሎስ ቅናት ነው” (መ. ጥበብ 2፡24) ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከእዚህ ሰይፍ ሊያድነን መጣ። ስለሆነም የሞት ጣዕም ያላቸውን ድንጋዮች ሁሉ እንድናስወገድ ተጠርተናል፣ ለምሳሌ በእምነታችን ውስጥ ያለው ግብዝነት በራሱ ሞት ነው፣ ሌሎችን የሚጎዳ ትችት በራሱ ሞት ነው፣ በደል መፈጸም፣ ስም ማጥፋት ሞት ነው፣ ድሆችን ማግለል ሞት ነው። ጌታ እነዚህን ድንጋዮች ከልባችን እንድናስወግድ ይጠይቀናል፣ ይህንን በምናደርግበት ወቅት ሁሉ ሕይወት አሁንም በዙሪያችን ያብባል።  ክርስቶስ ህያው ነው ፣ እሱን የተቀበለ እና እሱን የሚከተል ሁሉ ከሕይወት ጋር ይገናኛል። ያለ ክርስቶስ ወይም ከክርስቶስ ውጭ በሕይወት የመኖር ያለመኖር ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ አንድ ሰው ወደ ሞት የሚወስደውን መንገድ ይከተላል ማለት ነው።

ዮሐንስ 11፡1-45 እዚህ ላይ እግዚአብሄር ሕይወት መሆኑን እና ሕይወት ሰጪ መሆኑን ተጨባጭ በሆነ መልኩ እንመለከታለን። ኢየሱስ ወዳጁ የነበረውን የአልዓዛር ሞት አስቀድሞ ማስቅረት ይችል የነበረ ሲሆን ነገር ግን የምንወዳቸው ሰዎች ከእኛ በሞት በሚለዩበት ወቅት የሚሰማንን ከፍተኛ ሐዘን ኢየሱስ የራሱ ሐዘን አድርጎ በመቁጠር እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እግዚአብሔር በሞት ላይ ያለውን ስልጣን ለማሳየት ይፈልጋል። በዚህ የቅዱስ ወንጌል ክፍል ውስጥ የሰዎች እምነት እና የእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት፣ የእግዚአብሔርን ፍቅር የሚፈልጉ ሁሉ በመጨረሻም እንደሚያገኙት እናያለን። ማርታ እና ማርያም እንዲሁም ሁላችንም “አንተ አዚህ ብትኖር ኖሮ . . . ” ብለን የምናሰማውን ጩኸት እናያለን። የእግዚአብሔር መልስ ግን ወሬ አልነበረም፣በፍጹም እንዲህ አልነበረም! ሞት ላስከተለው ችግር የእግዚአብሔር መልስ ኢየሱስ ነው-“ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ… በእኔ እምነት ይኑራችሁ! ለቅሶ ሲያጋጥማችሁ በእኔ ማመናችሁን ቀጥሉ፣ ሞት አሸናፊ ሆኖ የሚወጣ ቢምስላችሁ እንኳን በእኔ ማመናችሁን ቀጥሉ። ድንጋዩን ከልባችሁ ላይ አስወግዱት! ሞት ወዳለበት ስፍራ እግዚአብሔር ቃል ገብቶ መልስ ይሰጥ ዘንድ ፍቀዱለት”።

📢ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ “ሐዘናችንን ሐዘኑ በማድረግ ርህራሄ የሚያሳየውን ኢየሱስ ምሳሌ ልንከተል ይገባል" አሉ!

Mstudio record 20200330 165013.wav11.74 MB

worship song

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 1ኛ ተሰሎንቄ 5 17-18፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።

በብዙም ከደበደቡአቸው በኋላ ወደ ወኅኒ ጣሉአቸው፥ የወኅኒውንም ጠባቂ ተጠንቅቆ እንዲጠብቃቸው አዘዙት። እርሱም የዚህን ዓይነት ትእዛዝ ተቀብሎ ወደ ውስጠኛው ወኅኒ ጣላቸው፥ እግራቸውንም በግንድ አጣብቆ ጠረቃቸው። በመንፈቀ ሌሊት ግን ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ እግዚአብሔርን በዜማ ያመሰግኑ ነበር፥ እስረኞቹም ያደምጡአቸው ነበር ድንገትም የወኅኒው መሠረት እስኪናወጥ ድረስ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፤ በዚያን ጊዜም ደጆቹ ሁሉ ተከፈቱ የሁሉም እስራት ተፈታ። 🤲🏽👏🏽🤲🏽Your worship will shift atmospheres And break things open! Let’s worship our good God on the most difficult times. Worship over fear 💪🏽

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ቤተክርስቲያን የምትነቃበት ህዝቡ እግዚአብሔርን የሚፈልግበት ታላቅ የመንፈስ መታደስ እንዲመጣ ✅ የእግዚአብሔርን አብሮንት ሰው ሲያውቅ በእሳትም ሆነ በጥልቅ ውሃ ውስጥ ቢሆን ያርፋልና ✅ ሰው ወደ እግዚአብሄር እንዲመለስ ✅ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ በሀይል ተሞልቶ የእግዚአብሔርን ቤት እንዲያገለግል 🔥የእየሱስን መንፈስ በእምነት በምእመን እና በቤተክርስቲያኑ አገልጋይዎች ሁሉ እንልካለን ትንቢተ ኢዮኤል 2 28፤ ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልምን ያልማሉ፥ ጐበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፤ደግሞም በዚያ ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ መንፈሴን አፈስሳለሁ፤ በላይ በሰማይ ድንቆችን አሳያለሁ፥ በታች በምድርም ደምና እሳት የጢስም ጭጋግ።

ለአዲስ አበባ ሀገረስብከት ቆሞሳት በሙሉ፤ ከሰበካው ጽ/ቤት ኦፊሴላዊ ደብዳቤ እስኪመጣ ድረስ ከዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች በእሑድ ቅዳሴ ላይ ማስታወቂያ በመንገር እንድታሳውቁ እናሳስባለን፡፡ 1. የኮሮና በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል ሲባል ከሰኞ መጋቢት 21 ጀምሮ ማንኛውም የኅብረት ጸሎትና ፕሮግራም ቅዳሴንና የመስቀል መንገድን ጨምሮ እስከ ዳግማዊ ትንሣኤ ድረስ እንዳይካሄድ ሰበካው ወስኗል፤ 2. ካህናት በያሉበት በየዕለቱ የግል ቅዳሴ ያደርጋሉ፤ ምእመናን በየዕለቱ በግል እና በቤተሰብ ጸሎት በማድረስ እንዲተጉ እናሳስባለን፤ 3. ለግል ጸሎት ቤተክርስቲያን በማናቸውም ሰዓት ክፍት ይሆናል፤ 4. የሕማማትና የትንሣኤ የሥርዓተ እምልኮ መርሐግብር በቴሌቪዥን እና በሶሻል ሜድያ የሚተላለፍበት መንገድ እየተመቻቸ ሲሆን ዝርዝር መረጃው በቅርቡ በየቁምስናው በሚሠራጭ የማስታወቂያ ፖስተር ይገለጻል፤ 5. በሰበካው ሐዋርያዊ ጽ/ቤት አማካኝነት ከስኞ እስከ ዐርብ በየዕለቱ ከቀኑ 6 - 6:30 ስዓት የሚካሄደው የቅዱስ ቁርባን ቡራኬ በሶሻል ሜድያ የሚሠራጭ ሲሆን ምእመናን በሰዓቱ የጥሞና ጊዜ በመውስድ መንፈሳዊ ትስስር እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡ በቅርቡም በሶሻል ሜድያ የቀጥታ ሥርጭት (livestream) ይደረጋል፤ 6. እያንዳንዱ ምእመን በያለበት ይህ አስክፊ የኮሮና ወረርሽኝ እንዲጠፋ አብዝቶ እንዲጸልይ እናሳስባለን፡፡

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ ጭንቀት ውስጥ ላሉ ሰዋች ✅ከእየሱስ ብቻ የሆነውን እና አእምሮን የሚፈሰውን ሰላም ለተጨነቁ ሰዎች በእምነት እናፈሳልን ወደ ፊልጵስዩስ 4 7፤ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በአለም ላይ በአሁኑ ሰአት እየሰራ ያለውን የጠላት ሀሳብ ማፈራረስ ✅በኛ ውስጥ ያለው አለም ውስጥ ካለው ስለሚበልጥ( 1ዮሀንስ 4:4) ዛሬ ምሽት በሀይል እንወጣለን ⚔️ወደ ኤፌሶን 6 12፤ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ስለ ሀገራችን እና ስለ አለም ፈዉስ ✅ በሀገራችን እና በአለም ላይ በCOVD-19 virus ለሚሰቃዩ በሽተኞች ✅ በተለያዩ በሽታዎች ምክንያት በየሆስፒታሎች ለተኙ ✅ ለአእምሮ ህመምተኞች ❤️ በእምነት በክርስቶስ ክቡር ደም እንሽፍናቸው 🙏 1ኛ ጴጥሮስ 2 24፤ ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።

‼️‼️‼️ የፀሎት ሰንሰለት ( chain prayer ) ሊጀመር ነው! የማቴዎስ ወንጌል 18 20፤ ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። ውድ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች -ከዛሬ ምሽት 3 ሰአት ጀምሮ የፀሎት ሰንሰለ ይጀምራል! ✅ በቀኑ በተዘጋጀው የፀሎት ርእስ ላይ በየቤታችን ሆነን በመንፈስ እንፀልያለን🙏 ✅ በየማታው 3 ሰአት ባለንበት እንደተመቸን ሆነን በአባታችን ፊት በህብረት እቀርባለን🙏 ✅በእዚሁ channel 2:30 ላይ የፀሎት ርእሱ ይለቀቃል. ✅ በአንድ ልብ በአንድ ሀሳብ ሆነን በየ ምሽቱ 3 ሰአት በመንፈስ እንገናኝ 🤗 1ኛ ቆሮንቶስ 15 58፤ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።

WHAT DO YOU TELL YOURSELF EVERY MORNING AS YOU START THE DAY?​​ ● ​​Moses would say, "Lord, if You don't go with us or before us, we are not going anywhere."​​ ● ​​Abraham would say, "The Lord will provide."​​ ● ​​Jacob would say, "I won't let go of You unless You bless me."​​ ● ​​Joshua would say, "As for me and my house, we will serve the Lord."​​ ● ​​Samuel would say, "Speak, Lord, for Your servant is listening."​​ ● ​​Nehemiah would say, "The joy of the Lord is my strength."​​ ● ​​David would say, "The Lord is my Shepherd, I shall not want."​​ ​_and "This is the day that the Lord has made and I will rejoice and be glad in it."​_ ● ​​Solomon would say, "Trust in the Lord, oh my soul, and lean not on your own understanding, in all your ways acknowledge Him and He shall direct your path."​​ ● ​​Isaiah would say, "Arise and shine for my Glory has come." and "No weapon formed against me shall prosper."​​ ● ​​Jeremiah would say, "The Lord has plans to prosper me and not to harm or fail me."​​ ● ​​Jabez would say, "Oh, that you may bless me and enlarge my territory."​​ ● ​​Shadrach, Meshach and Abednego would say, "We will not bow down to any image but will serve the Lord."​​ ● ​​Ezekiel would say, "Any dry bones in my life, live again."​​ ​Choose your daily statement of faith. Meditate on it! Speak it every morning. 🙏 Could you please share this with someone else, and let them know that God loves them?