805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 63
5፤ ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ።6፤ በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ፤7፤ ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌 ስለ እግዚአብሔር ምህረት
✅ የማያልቀውን ማለዳ ማለዳ አዲስ ስለሆነው ምህረቱ እግዚአብሔርንእናመሰግናለን
✅ እስካሁን እንደጠበቀንም በሚመጣው ዘመን እንዲጠብቀን እንፀልያለን
📖 ሰቆቃወ ኤርምያስ 3: 22 -23
ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።
ጌታ ሆይ ተመስገን ክበርልን ንገስልን እናወድስሀለን እናከብርሀለን ከፍ ከፍ እናደርግሀለን በዘመናችን በቀናችን በእድሜአችን ሁሉ እናመሰግንሀለን:: የዘላለም ጌታ ተመስገን ቸሩ አባታችን መሀሪ አምላካችን እጅግ እናመሰግንሀለን::
ስለሀገራችን ኢትዮጵያ እናመሰግንሀለን አምናን በምህረትህ ዘንድሮንም በቸርነትህ ስለምትዳደጋት ስለምታድናት ስለምትሸፍናት እናከብርሀለን:: ጌታ ሆይ በአንተ እንታመናለን እንድንድንበት የሰጠኸን ከስሞች ሁሉ በላይ የሆነ ስም አባቱ ያከበረውን በሰማይም በምድርም ሁሉም ለኢየሱስ ስም የሚንበረከኩለት ምላስ ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ጌታ ነው ብለው የሚመሰክሩለት ሁሉም የሚታዘዙለት ዛሬም በሀገራችን ላይ ስለሰላም ኢየሱስ አልን ስምህን እንጠራለን በኢየሱስ ስም በአራቱም መአዘን ኢየሱስ አልን ክብርህ ህይልህ ሁሉ ይገለጥ በሀገራችን ሰላም ይሁን በህዝባችን ላይ ሁሉ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ስምህ ሀይል አለው የጸና ግንብ ነው በሁሉም ነገር በምንሰማው በምናየው በሚሆነው ሁሉ ላይ ኢየሱስ አንተን ከፍ አደረግን ስምህን ከፍ አደረግነው አንተ ተቆጣጠር አንተ እለፍ ግዛን ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ በሀገራችን ላይ ስምህን አክብረው !!!
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን
✅ ጠላት በሀገራችን ላይ የሚያስነሳውን አቧራ ሁሉ በእየሱስ ህያው ስም ሰጥ እንዲል በልጅነት ስልጣን እንናገራለን
እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል
🙏
📖 ወደ ፊልጵስዩስ 2
9፤ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤10፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥11፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌እርስ በእርስ ስለመዋደድ
✅ ከእርስ በራሳችን በመጀመር በቤታችን በአከባቢየችን እና ሀገራችን ላይ ሁሉ ፍቅር እንዲሆን
ለእግዚአብሔር የሚሆን ቤት ለማዘጋጀት
ፀጋው እና መንፈሱ እንዲበዛልን እንፀልያለን
📖 1ኛ ዮሐንስ 4
12፤ እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል።
መዝሙረ ዳዊት 66
8፤ አሕዛብ ሆይ፥ አምላካችንን ባርኩ፥ የምስጋናውንም ድምፅ አሰሙ።
አሜን አምላካችን አባታችን ጌታችን እናመሰግንሀለን ምስጋናችንን እናሰማለን የምስጋና ነዶ ለአንተ እናቀርባለን!!!
ለታላቅነትህ ለአምላክነትህ ሁሉ ምስጋና ይገባሀል ትልቅ ነህ የእኛ አይምሮ ከሚችለው በላይ ሀያል ነህ ከሀያላን በላይ ገዥ ነህ ከገዥዎች ሁሉ በላይ ንጉስ ነህ ከነገስታት ሁሉ በላይ እናወድስሀለን እንቀኛለን እንሰግዳለን እናመልክሀለን ይገባሀልና አንሶብህ አይደለም ስለሚገባህ ነው ምስጋና እንሰዋለን አሜን!!!
ጸጋህ የበዛልን ምህረትህ የበዛልን ቸርነትህ የያዘን ሰላምህ የበዛልን ጥበቃህ የበዛልን ጌታ ሆይ እናመሰግንሀለን:: በክንፎችህ ጥላ የምታኖረን ክበርልን በአንተ ደስ ይለናል በታላቅነትህ እንሰግዳለን እናከብርሀለን ክቡር ነህና ክበር ንገስ እንልሀለን!!!
ተመስገን ተመስገን በነገር ሁሉ ከልብ የሆነ ምስጋናችንን እናቀርባለን አንተ ግሩም ነህ ድንቅ ነህ ፍቅር ነህ አዳኝ ነህ ያደረክልን ብዙ ነው የሆነልን ብዙ ነው እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሀለን ምስጋና ይገባሀል
ምህረትና ቸርነትህ በህይወት ዘመናችን ይከተለናል ለዘለአለም በአንተ ቤት እኖራልን እናመልክሀለን እናመሰግንሀለን በጌታ በኢየሱስ ስም አሜን!!!
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 63
5፤ ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ።6፤ በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ፤7፤ ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና።
2013 ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሴሚናር በቅርቡ ይጀምራል።
የሚሰጠው ጥቅሞች
* አዕምሮን በማደስ ወደ አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት የሚያመጣ ነው (ሮሜ 12:2)
*የእግዚአብሔርን ቃል በመረዳት በቃሉ መኖር እንድንችል ያደርገናል
*ከከበደን የኃጢአት ሕይወት ልምምድ ነፃ ያወጣናል
“እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።”
— ዮሐንስ 8፥32
*ከጭንቀት እና ከፍርሀት ሕይወት ነፃ ያወጣናል
*ወደ አዲስ የፀሎት ሕይወት ያስገባናል
እነዚህንና በጣም ብዙ መንፈሳዊ ጥቅሞችን የሚሰጠን መሆኑን ትምህርቱን የወሰዱ ሰዎች የመሰከሩት እውነት ነው። ስለዚህ ማንኛውም በዚህ አቅጣጫ ሕይወቱን መቀየር የሚፈልግ ሰው ቢማረው እጅግ በጣም ይጠቀማል ብለን እናስባለን። ለግዜው ጥቂት ተማሪዎችን ብቻ የምንቀበል ስለሆነ ቀድመው የተመዘገቡ 10 ተማሪዎችን ብቻ የምናስተናግድ ይሆናል።
ለመማር ሲመጡ መፅሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ መፃፊያ ደብተር መያዝ ግዴታ ነው።
እያንዳንዱ ክፍል ተያያዥነት ያለው በመሆኑ መቅረት አይቻልም ሲመዘገቡ እንደሚመቾ እርግጠኛ ይሁኑ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች
✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ
በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን
📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው
📖 መዝሙረ ዳዊት 116
1፤ እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት።2፤ ጆሮውን ወደ እኔ
ትንቢተ ኢሳይያስ 57
15: ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል፦ የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ :-የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ
18: መንገዱን አይቻለሁ እፈውሰውማለሁ እመራውማለሁ ለእርሱና ስለ እርሱም ለሚያለቅሱ መጽናናትን እመልሳለሁ
19: የከንፈሮችን ፍሬ እፈጥራለሁ በሩቅም በቅርብም ላለው ሰላም ሰላም ይሁን እፈውሰውማለሁ ይላል እግዚአብሔር
ጌታ ኢየሱስ ሆይ አንተ የሰላም ንጉስ ነህ የበሽተኞች ፈውስ ነህ የብቸኞች አፅናኝ ነህ የተናቁ የተዋረዱትን መንፈስ ህያው ታደርጋለህ ከፍ አድርገህ በከበረው ሰረገላ ታስቀምጣለህ ወደ እውነት መንገድ ትመራለህ ያዘኑትን የሚያለቅሱትን ታፅናናለህ ሰላምህን ታበዛለህ ታድናለህ ትታደጋለህ ትፈውሳለህ አቤቱ ስራህ እንዴት ብዙ ነው ከአይምሮ በላይ ነው ዛሬም እየሰራህ ነው ትላንት የፈወሰው ጣትህ ዛሬም እየፈወሰ ነው ነገም ይፈውሳል ለዘለዓለም ይፈውሳል እረፍትን አያውቅም ደከመኝ ሰለቸኝ አትልም ዛሬም በተለያዩ በሽታዎች ተይዘው በቤታቸው በሆስፒታሎች በጎዳናዎች
እየተሰቃዩ ያሉ ፈውስህን የሚሹ አንተን የሚያውቁም የማያውቁም አንተ ግን በስም የምታውቃቸውን ልጆችህን ሁሉ እፊትህ አፈሰስናቸው ፍፁም የሆነው ፈውስህ ያረስርሳቸው ሰላምህ ይውረሳቸው ፀጋህ ያቁማቸው!!!
በጌታ በኢየሱስ ስም!!! ሃሌሉያ!!!
Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ቅዳሜን ስለፈወስ
✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች
✅በሆስፒታሎች,በጎዳናዋች እና በቤታቸው ውስጥ ብቻቸውን ስላሉ ህመምተኞች ሁሉ
ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸውበህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል
ትንቢተ ኤርምያስ 17
14፤ አቤቱ፥ ፈውሰኝ እኔም እፈወሳለሁ፤ አድነኝ እኔም እድናለሁ፤ አንተ ምስጋናዬ ነህና።
መዝሙረ ዳዊት 104
33: በሕይወቴ ሳለሁ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ ለአምላኬም በምኖርበት ዘመን ሁሉ እዘምራለሁ
34: ቃሌ ለእርሱ ይጣፍጠው እኔም በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል
በደስታ እናመሰግንሃለን በደስታ እንሰግድልሃለን ደስታህ ሃይላችን ነው በጠላቶቻችን ላይ ደስ አሰኝተኸናል አንተን ተጠግተናል እና እድል ፈንታችን ደስታ ነው አንተ ባለህበት ስምህ በተጠራበት ሁሉ ስፍራውን ሃይልህ እና ደስታህ ሲሞላው አይተናል እንመሰክራለን ምስክርህ ለልባችን ደስታ ነውና አቤቱ ቅዱሳንህ በደስታ ደስ ይበላቸው ዝማሬአችን ደስታ ነው በዓላችን የደስታ ነው ከአንተ ጋራ መንገዱ ሁሉ የደስታ ነው ደስታችን ከሩቅ ይሰማል በመንገዳችን ሁሉ ደስታ ይበቅላል ፊትህን በደስታ አሳይተኸናል ከስንዴ ፍሬ እና ከወይን ፍሬ ከዘይትም ይልቅ ልባችንን በደስታ ሞላኸው የዘላለምን በረከት አውርሰህ በፊትህ ደስታ ደስ አሰኝተኸናል እና እናመሰግንሃለን በደስታችን ለዘላለም አንታወክም ለቅሶን ወደ ደስታ ቀይረህ ማቅን ቀድደህ ደስታን አስታጠከን ከከበቡን አድነህ ደስታን ሸለምከን የደስታ ዘይትን ቀባኸን በደስታ ወደ እልፍኝህ አስገባኸን እጃችንን እናጨበጭብልሃለን በደስታ ቃልም እልል እንልልሃለን አጥንቶቻችንን ደስ አሰኝተሃል ሃሴትን እና ደስታን አሰምተኸናል ከንፈሮቻችን ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ ብርሃን ለፃድቃን ደስታም ለልበ ቅኖች ወጣ በደስታ ለእግዚአብሔር ተገዙ በእልልታም ለክብሩ ውጡ!!! ሃሌሉያ
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌በእግዚአብሄር ላይ ብቻ ደስታ እንዲኖረን
✅ እርሱ ብቻ ክብር ምስጋና እና ጊዜአችን ስለሚያስፈልገው
✅ እርሱን በመፈለግ እና በእርሱ በመደሰት
እኛ ያሰብናችውን ሳይሆን እርሱን ህልውናውን ለማግኘት
በእርሱ ላይ ማተኳር መደሰት መተከል እንዲሆንልን ፀጋውእንዲበዛልን እንፀልያለን🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 37
4፤ በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል።5፤ መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።
1ኛ ጢሞትዎስ 2:1-3
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።
ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።
አሜን አሜን አሜን ቅዱስ አባት ሆይ ተባረክ የወደድከን በምህረትህ ማለዳ ማለዳ የምትጎበኘን በሀገራችን ሠላምህን ያበዛኽልን የሚቆጣጠረንን መንፈስ ቅዱስን የላክህልን አባ ከፍ በልልን ንገስልን ተወደስልን ጌታ ሆይ አንተን እንድንመስልና እንደፈቀድክልን በጸጥታና በዝግታ መኖር እንድንችል ማስተዋል ይብዛልን አምላክ አባታችን ሆይ በአገራችን በተለያዩ ችግር ጭንቅና መከራ ያሉትን እንዲሁም ከአንተ የራቁትንና እንተንና እውነትን ሳያውቁ የሚኖሩትን ህዝቦች ሁሉ በፊትህ ይዘን ቀረብን የምህረትና የሠላም አባት ስዎች ሁሉ እንዲድኑና አንተን ማወቅና በአንተ ፊት መልካምና ደስታ ብቻ እንደሆነ እንዲበራላቸው ሰምተህ የምትመልስ አባት እንዳለኸን በመተማመን እኛ ልጆችህ በህብረት በፊትህ ወድቀን ምህረትህን ደግመን ደግመን እንጠይቅሀለን በእየሱስ ክርስቶስ ሰም 🙏🏾🙏🏾🙏🏾
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏
📖 2ኛ ዜና መዋዕል 33
12፤ በተጨነቀም ጊዜ አምላኩን እግዚአብሔርን ፈለገ፥ በአባቶቹም አምላክ ፊት ሰውነቱን እጅግ አዋረደ፥13፤ ወደ እርሱም ጸለየ፤ እርሱም ተለመነው፥ ጸሎቱንም ሰማው፥ ወደ መንግሥቱም ወደ ኢየሩሳሌም መለሰው፤ ምናሴም እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ አወቀ።
ኦሪት ዘጸአት 34
6፤ እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ፦ እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥7፤ እስከ ሺህ ትውልድም ቸርነትን የሚጠብቅ፥ አበሳንና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፥
እግዚአብሔር አባታችን ይቅር ባይ መሀሪ ታጋሽ ባለብዙ ምህረትህ ቸርነትና እውነት እግዚአብሔር ዛሬም ለእኛ ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ለህዝቦችዋ ምህረትህን ያበዛህ ምህረትህን ያወረድክ በቸርነትህ የጠበከን እጅግ እናመሰግንሀለን::
ለምህረትህ ለፍቅርህ ወደር የለውም ሁሌም ይቅር ባይ ሁሌም መሀሪ ደግ ሁሉን ቻይ መሆንህን በልዩ ሁኔታ እንድናውቅህ ምህረትህ የገነነ ይቅር ባይ አምላክ መተላለፍን ሀጢያትን ሁሉ ይቅር የምትል አምላክ አባት መሆንህን የምንረዳበት የምናውቅበት ጸጋህን አብዛልን:: የልቦና አይኖቻችንን አብራልን የአንተን ታላቅነት የምንገልጽበት ጸጋ በልባችን ብርሀንህን አብራልን የመርዳት ባለጸግነትህን አብዛልን አሜን!!!
ትንቢተ ኤርምያስ 29
11፤ ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።
አሜን እግዚአብሔር አባታችን ሆይ ለእኛ ለልጆችህ ያለህ ሀሳብ የማዳን የፍቅር የሰላም የእረፍት የደስታ ሀሳብ ነውና እጅግ እናመሰግንሀለን:: የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ አንተ ነህና ለእኛ የምታስበው ሀሳብ መልካም ነው በጎ ነው ፍጻሜው ያማረ ነውና እናመሰግንሀለን::
ከመልካምነትህ ከበጎነትህ ብዛት ገና አለም ሳይፈጠር በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ መረጥከን ከመሀጸን ሳንወጣ የጠራኸን በልጅህ በክርስቶስ ኢየሱስ ደም እንዲሁ በጸጋ ያዳንከን ልጆችህ ያደረከን አባ ብለን የምንጠራበት የልጅነትን መብት የሰጠኸን ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሀን ያመጣኸን በቅዱስ መንፈስህ ያተምከን በክርስቶስ ደም የገዛኸን ለአንተ ለክብርህ ምስጋና ያደረከን ለርስትህ የተለየ ወገን ያደረከን የአንተን በጎነት እንድናገር የጠራኸን የንጉስ ካህናት ቅዱስ ህዝብ ያደረከን ምህረትን ያገኘን መልካም ሀሳብህ የተፈጸመልን ልጆችህ በሙሉ ሀይላችን እናመሰግንሀለን:: አሜን!!!
ክብርም ምስጋናም ስግደትም አምልኮም ከዘለእለም እስከዘለአለም ለአንተ ይሁን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌እውነተኛ ስለሆነው አምላክ ማንነት መረዳት
✅ እግዚአብሔር አዳኝ ይቅር ባይ የሆነ አምላክ እንደሆነ እንድረዳ
✅ በኛ በልጆቹ ላይ ያለእ ሀሳብ የማዳን እንጂ
የፍርድ እንዳሆነ የምንረዳበት ፀጋ እንዲበዛልን
እንፀልያለን
🙏
📖 የዮሐንስ ወንጌል 3:17
ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።
የሐዋርያት ሥራ 2:44-47
44: ያመኑት ሁሉ በአንድነት ነበሩ ያላቸውንም ሁሉ የጋራ አደረጉ
45: ሀብታቸውንና ንብረታቸውንም እየሸጡ ለእያንዳንዱ ሰው የሚያስፈልገውን ያህል ይሰጡት ነበር
46: በየዕለቱ በቤተ መቅደስ በአንድነት እየተገናኙ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ በደስታና በቀና ልብ ይመገቡ ነበር
47: እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው ጌታም የሚድኑትን በቍጥራቸው ላይ ዕለት በዕለት ይጨምር ነበር
እግዚአብሔር አባት ሆይ በልግስና መስጠትን ያስተማርከን አንድ ልጅህን ለእኛ ስትል በመሰዋት ነው ልጅህም ጌታችን መድሃኒታችን ለነፍሱ ሳይሰስት እኛን ከሐጢአት ባርነት ነፃ ሊያወጣን ለዘለዓለም ህያው ሆነን እንድንኖር ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ ደስ እያለው በልግስና እራሱን ሰጠን ! ክብር ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ለእርሱ ይሁን!
እኛም ከተሰጠን ላይ ደስ እያለን በልግስና እንድንሰጥ ስላስተማርከን እናመሰግንሃለን የሚስጥ በደስታና በልግስና ይስጥ እንዳልከን ገንዘብ ወይንም ቁስ ብቻ ሳይሆን እራሳችንን ከመስጠት እንድንጀምር ፀጋህ ይብዛልን!! እራሱን የሚሰጥ ገንዘቡን ወይንም ቁሱን ደስ እያለው ይሰጣል እራሱን የማይሰጥ ግን በደስታ እና በልግስና አይሰጥም! መስጠት በልግስና እና በደስታ ካልሆነ ከንቱ ነው ! በልግስና እና በደስታ መስጠት በረከት ነው!!!
ስንሰጥ በደስታ እና በልግስና እየሰጠን የእግዚአብሔር ሞገስ እንዲበዛልን እና ከሚድኑት መካከል እንድንገኝ የሰማያዊ በረከቱ ተካፋዮች እንድንሆን እግዚአብሔር ይርዳን!!! በኢየሱስ ስም አሜን 🙏🏽
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ መስጠት
✅ ከመቀበል ይልቅ በመስጠት ብዙ ደስታ እና በረከት ስላለ
✅ እራሱን እንኳ ሳይሰስት ሰጥቶ እርሱን እንድንመስል እየሱስ ስላስተማረን
እግዚአብሔር በአዲስ አመት አዲስ የመስጠትን ፀጋ እንዲያለብስን
እንፀልያለን
📖 የሐዋርያት ሥራ 20
35፤ እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፡— ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው፡ እንዳለ፡ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 65
4፤ አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።
