805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ወጣቶች በእግዚአብሔር ሀሳብ በአእምሮቸው እንዲለወጡ ይህንን አለም እንዳይመስሉ
✅ በብዙ መልካም ፍሬ እንዲገለጡ
✅ለሀገራችን ሁሉ በረከት እንዲሆኑ
በጎና ደስ የሚያሰኘውን እንዲሁም ፍፁም የሆነውን የእግዚአብሔርን ፍቃድ አውቀው እንዲኖሩ በ እግዚአብሔር የፀጋው ዙፋን ስር እናስቀምጣቸውለን 🙏
📖 ወደ ሮሜ 12
2፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 1ኛ ዜና መዋዕል 16(23፤25 )
ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ዕለት ዕለት ማዳኑን አውሩ። ክብሩን ለአሕዛብ፥ ተአምራቱንም ለወገኖች ሁሉ ንገሩ። እግዚአብሔር ታላቅ፥ ምስጋናውም ብዙ ነውና፤ በአማልክትም ሁሉ ላይ የተፈራ ነው።
የምህረትና የፍቅር ሁሉ አባት የሆንክ እግዚአብሔር አባት ሆይ ወላጅ ሆነው ልጆችን ስለሚያሳድጉ ስዎች እናመሰግንሀለን :: እግዚአብሄር አባት ሆይ አሁንም ብዙ ቤተሰብ የሌላቸው ልጆች አሉና አሁንም ለእነዚ የሚያሳድጉ ስዎችን ታበዛ ዘንድ ለሚያሳድጉት ስዎች አብዝተህ እንድትባርካቸው ሙሉ በሆነው በረከትህ ጸጋህ ችሎታ አቅም ሁሉ ባርካቸው:
እግዚአብሄር ሆይ ለወደፊትም አባት ለሚሆኑ የአባትነትን ጸጋ የማሳደግን የመንከባከብን ጸጋ ስጣቸው::
እግዚአብሔር አባት ሆይ ጳጳሳትን ካህናትን ወደ አንተ ፊት እናቀርባቸዋለን ጌታ ሆይ የማቃርጠው ምህረትህ እንዲያጸናቸው እንዲጠብቃቸው እንለምንሀለን:: በእርዳታህና በቸርነትህ በጸጋህ በጤነት በርኝም እድሜ ጠብቃቸው:: አንተን በታማኝነት የሚያገለግሉበት ጸጋ አብዛላቸው:: በቃልህ ሙላት አበርታቸው ብለን በጌታ በኢየሱስም እንጸልያለን:: ሁሉን ነገር ትተው አንተን ይዘዋልና ፍሬ ይሁንላቸው ፍሬአቸው በአንተ ዘንድ ያማረ ይሁን:: ሁሉን የሚያስችለውን ጸጋ አብዛላቸው:: አሜን
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ስለ አባቶች
✅ በህይወት ላሉ እና ለሌሉ
✅ እንደ አባት ሆነው ልጆቭን ለአሳደጉ ለሚያሳድጉ
✅ለወደፊት አባት ለሚሆኑ
✅ ለመንፈሳዊ አባቶች ( ቄሶች )
በሰማያዊ አባታችን ፊት እናቀርባቸዎለን
ስለነእርሱ እናመሰግናለን የአባትነትን ትልቅ ሀላፊነት እንዲወስዱ የሚያስችላቸውን ፀጋም እንጠይቃለን
📖 1ኛ ቆሮንቶስ 15
58፤ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌ስለ ልምላሜ
✅ በሚመጣው ጊዜ ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት ተተክለን
ሙቀትም ሲመጣ እንዳንፈራ
በድርቅም ጊዜ እንድናፈራ
በሁኔታዎች ሳንገደብ በእርሱ ቃል እና መንፈስ ላይ ተተክለን እንድንለመልም
በህብረት እንፀልይለን ይህን ልምላሜም ለሀገራችን እናውጃለን
📖 ትንቢተ ኤርምያስ 17
8፤ በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል።
እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሀለን ስለጥበቃህ
▪️እረኛ ስለበጎቹ የሚያስብ ከጥፋት የሚጠብቅ ከተኩላ ከጠላት ከአውሬ የሚጠብቅ የሚያድን
መዝ91 :3
ከአዳኝ ወጥመድ ያድነኛል
ከሚያስደነግጥ ነገር ያድነኛል
▪️ነፍሱን ስለበጎቹ አሳልፎ የሚሰጥ
እረኛ ለበጎቹ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ስለሚያውቅ ያቀርብላቸዋል ያዘጋጅላቸዋል ::
እግዚአብሔር አባታችን ሆይ በቸርነትህ እስራኤላዊያንን ከሰማይ መና አውርደህ እንደመገብካቸው ዛሬም በሀገራችን በችግር ውስጥ ላሉት የገቢ ምንጭ ለሌላቸው የሚበሉት የሚቀምሱት ያጡትን በችግርና በጭንቀት ውስጥ ያሉትን ሁሉ
በየቤቱ ጉብኝትህን በዚህ ምሽት ይድረሳቸው በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሀለን::
▪️በለመለመ መስክ የምትታሳድር ህይወት ባለበት የምታኖር እድገት ያለበት ልምላሜ ባለበት ማፍራት ወዳለበት የምታሳድር የምታኖር አባት ሆይ ዛሬም ያንተን የሚያሳርፍ ህይወት ያላገኙትን ህይወት የደረቀባቸውን ተስፋ የቆረጡትን ሁሉ ፍቅርህን እንዲቀምሱና የእረፍት የሰላም የደስታ ህይወት እንዲሆንላቸው በኢየሱስ ስም እንጸልያለን::
▪️መንፈስ ቅዱስ በእረፍት ውሀ ዘንድ ይመራናል ያሳርፈናል ከፍርሀት ከጭንቀት ነፃ ያወጣናል የህይወትን መንገድ ያሳየናል ያስተምረናል ያጽናናል ያድሰናል ያነጻናል ዛሬም መንፈስ ቅዱስ ሆይ ያላወቀ ይወቅህ ያልቀመሰ ይቅመስህ መንፈስህ ለሁሉም ይዳረስ::
▪️ነፍሴን መለስካት : ነፍሳችንን አዳንካት
ውደአሰብክልን አመጣኸን ወደ አንተ አስጠጋኸን ከሞት ወደ ህይወት ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሀን አመጣኸን እናመሰግንሀለን:: በጨለማ ላሉ በተለያየ ሱስ የተያዙትን ወጣቶች ሁሉ ወደ አንተ ብርሀን ይግቡ በተለያየ እድራት ውስጥ ያሉትን ወገኖች ሁሉ በብርሀንህ ነፍሳቸውን መልስ አድን ብለን በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሀለን::
▪️በሞት ጥላ መካከል እንካን ብሄድ ክፉን አልፈራም: በእግዚአብሔር ላይ ያረፈ እግዚአብሔር የተጠጋ በማንኛውም ጊዜ በህይወት ውጣ ውረድ በችግር
በተለያዩ ችግሮች ሁሉ እግዚአብሄር አብሮን ስለሆነ ልባችንን በቅዱስ መንፈሱ ይጠበቃል አሜን::
ዛሬም በችግር በፍርሀት ስጥ ከለላ ለሌላቸው ሰዎች ሁሉ አንተ ከለላ ሁናቸው አድናቸው ታደጋቸው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን!!!
▪️ቸርነትህና ምህረትህ በህይወት ዘመኔ ሁሉ ይከተሉኛል አሜን
ቸርነትህ ብዙ ምህረትህ ብዙ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው ምህረትህ
ዛሬም የአንተን ፍቅር ቸርነት ምህረት ምዳን ሁሉ ለተቸገሩት ምህረትህ ለሚያስፈልጋቸውብ ፍቅርህ ለተራቡ ማዳንህን ለፈለጉ ሁሉ በኢየሱስም ዛሬ ጉብኝትህ ማዳንህ ያግኛቸው:: አሜን!!! ስለሰማኸን እናመሰግንሀለን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌በዚህ ወቅት ስለተስፉፈው የኢኮኖሚ መናጋት
✅የብዙ ሰዎች የገቢ ምንጭ ቆሞል ወይም እጅግ ቀንሷል
✅ በብዙ ግራ መጋባት እና ጭንቀት ውስጥ ሰው ገብቶል
♦️በዚህ ምሽት ግን እግዚአብሄር እረኛችን ነው የሚያሳጣን የለም !
በለመለመ መስክ ያሰማራናል!
በእረፍት ውሃ ዘንድ ይመራናል !
በፊታችን ገበታን አዘጋጅቶልናል!
በጠላቶቻችን ፊት ራሳችንን ዘይት ይቀባል!
ፅዋችን ይተርፋል!
ቸርነትና ምህርቱ በህይወት ዘመናችን ሁሉ ይከተሉናል
ብለን መዝሙረ ዳዊት 23 ን በልዩ መልክ እናውጃለን
ቃሉም ይሰራል! 🙏
መዝሙረ ዳዊት 23(1:6)
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።
ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።
በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው።
ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።
መጽሐፈ ምሳሌ 03
5 በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤
▪️በፍጽም ልብ በእግዚአብሔር መታመን የእግዚአብሔር ቃል ማመን ማለት ነው::
ቃል እራሱ እግዚአብሔር ነው ::
ዩሐ1 :1 በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።
▪️የእግዚአብሔር ልጆች እንደመሆናችን መጠን አባታችን በዘላለም ፍቅር እንደወደደንና እንደሚጠነቀቅልን መታመን....
▪️አባት ለልጁ የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደሚሰጥ እኛም እግዚ አባታችን ከስጋ አባታችን ይበልጥ የሚያስፈልገንን ሁሉ እንደሚሰጠን እንደሚያቀርብልን መታመን: ...
መዝሙረ ዳዊት 23
1 እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም።
▪️አባታችን በመልካም መንገድ እንደሚመራን መታመን..
መዝሙረ ዳዊት 23
2 በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ይመራኛል
▪️ለእናንተ የማስባትን ሀሳብ መልካምና በጎ ፍጻሜው ያማረ ነው ..
ትንቢተ ኤርሚያስ 29
11 ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።
ጸጋውን እንደሚሰጠን የተስፋ ቃሉ እንደሚፈጸም እርግጠኞች ሆነን ቃሉን መታመን ....
▪️በህይወታችን አስቸጋሪ ሁኔታ በሚገጥመን ጊዜ መንገዳችንን ሁሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት መታመን...
መዝሙረ ዳዊት 36(37)መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።
▪️በራስህ ማስተዋል አትደገፍ ...የእኛ ማስተዋል ውስን ነው ሊሳሳት የሚችል ስለሆነ ከራሳችን እውቀት ችሎታ አቅም ጉልበት ጉብዝና ይልቅ በእግዚአብሔር አቅም ጉልበት ችሎታ መደገፍ መተማመን መጽናት ::
▪️በራሳችን አስተሳስብ አመለካከት ከመመካት ይልቅ በህይወታችን የምናስበውን የምናቅደውን ሁሉ በእግዚአብሔር ሀሳብና ፈቃድ አላማ የእግዚአብሔርን ጥበብ ፈቃድ ያለበትን እንዲሆን መጸለይ በመንፈስ ቅድስ ምሪት መመራት ይሁንልን:: አሜን አሜን አሜን!!!
እግዚአብሄር ሆይ
በችሎታችን አንመካም
በእውቀታችን አንመካም
ባለን ነገር አንመካም
በንብረታችን አንመካም
በቁመናችን አንመካም
በማነታችን አንመካም
በወገኖቻችን አንመካም
በዘምዶቻችን አንካም
ባለን ቤት አንመካም
ባለን መገልገያ መኪና አንመካም
በአቅማችንም አንመካም
በጉልበታችንም አንመካም
በአግልግሎታችን አንመካም
የምንመካው ጌታ ሆይ በአንተ ብቻ አንተ ከእኛ ጋር ስለምትኖር የአንተ ስለሆንን አንተ ብቻ ስላለኸን በአንተ ብቻ እንመካለን እንታመንማለን :: አሜን አሜን አሜን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌በፍፁም ልብ በእግዚአብሔር ላይ ብቻ መታመን
✅ በራሳችን እውቀት ሀብት እና ንብረት ላይ
✅ በምናያቸው በምንሰማቸው ነገሮች ላይ ሳይሆን
በእግዚአብሔር ላይ ብቻ እምንታመንበትን እና እምናርፍበትን ፀጋ እንዲሰጠን እንፀልያለን
🙏
📖 መጽሐፈ ምሳሌ 3
5፤ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤
እናመሰግንሃለን አባ እለት እለት በምስጋና አንደበታችንን ስለምትከፍትልን ጠብቀህ ከልለህ ወደዚች ምሽት አድርሰኸን በሌላ ምስጋና እፊትህ እንድንቀርብ ጊዜያቱን ሰአታቱን ስላዘጋጀህልን ክብር ምስጋና ለአንተ ይሁን !!!
አንተን ለማመስገን ብዙ ምክንያት አለን ቆጥረን የማንዘልቀው ምክንያት ሁኔታዎች የማይገድቡት ጊዜያት የማያቆሙት እንደ ወንዝ ጅረት ዝም ብሎ የሚፈስ ምስጋና አለን! አመስግነን አንጠግብህም ዝም ብለን እናመሰግንሃለን ዝም ብለን እናሞጋግስሃለን ደስ እያለን ስምህን ከፍ እናደርገዋለን ሃሌሉያ ለዘላለም ክበር ለዘላለም ከፍ በል ያላወቁህ ይወቁህ አውቀውህ ፍቅርህን ቀምሰው ከቤትህ የራቁ እንደገና በምስጋና ፊትህ ይቅረቡ !!!
ስለዚህ ጉባኤ እናመሰግንሃለን ስለመጠራታችን በፊትህ ሞገስን ስለ ማግኘታችን እናመሰግንሃለን ስለ ሃገራችን ስለ ሕዝባችን ስለ መሪዎቻችን ስለ ሃገር ሽማግሌዎቻችን ስለ ባለ ስልጣናት ስለ ጳጳሳት ስለ ካህናት ስለ ደናግላን ስለተለያዩ ግን ለአንተ ክብር ስለቆሙ የሃይማኖት መሪዎች እጅግ አድርገን እናመሰግንሃለን ዛሬ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በልዩነት መሪዎቻችንን እና ሽማግሌዎቻችንን በዚህ ጉባኤ አማካኝነት ሊባርክ ወዷልና እኛም ለዚህ ክብር በመጠራታችን ደስ እያለን መሪዎቻችንን እና ሽማግሌዎቻችንን በእምነት በፊትህ ይዘን ቀርበናል በጌታ በኢየሱስ ስም አሜን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 ስለ መሪዎች እና ስለሀገር ሽማግሌዎች
✅ በ ጥበብ እና በማስተዋል
✅ በእውነት እና በሞገስ
እንዲሞሉ እና እንዲወጡ በእየሱስ ስም እንፀልያለን
🙏
📖 1ኛ ጢሞቴዎስ 2
1-2፤ እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 1ኛ ቆሮንቶስ 15
57፤ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
✔️ሮሜ 1
17 ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።
ጻድቅ በእምነት በህይወት ይኖራል በማየት ወይም በሚሰማው ወይም ከሁኔታ ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው
✔️2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 04
13 ነገር ግን፡— አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤
✔️ያመነ ቃሉን ይናገራል ቃሉን
ያውጃል የእግዚአብሔርን ቃል በመገፉ ቁስል ተፈውሳችኃል ይለናል ስለዚህ በህመም ጊዜ በመገረ ፉ ቁስል ተፈውሻለሁ ማለት መቻል አለብን
✔️እመን እንጂ አትፍራ ይለናል ቃሉ ስለዚህ በችግር ጊዜ እልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል ጌታ ይረዳናል ብለን ማወጅ
✔️ተቤዥቼሀለሁ አትፍራ በስምህም ጠርቼሀለሁ አንተ የእኔ ነህ ብሎናል እግዚአብሔር እንደሚወደኝ ማመን በስሜ እንደሚያውቀኝ
✔️በምሄድበት ሁሉ እኔ ከአንተ ጋራ ነኝ ብሎናል ስለዚህ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ከኔ ጋራ ነው ማወጅ መናገር
✔️እነሆ በእጄ መዳፍ ቀርጬሻለሁ ብሎናል ከእጅ መዳፍ ማንም ሊያወጣን እንደማይችል እንንገረው ለሁኔታ ለነገሮች ሁሉ
✔️በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና አይዞህ አትፍራ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝኩህም ::
ሀሌሉያ የእግዚአብሔርን ያው ነው ለኢያሱ የተናገረው ዛሬም ለእኛ ይናገረናል ሁሌም ከእኛ ጋር ነውና
እንግዲህ እግዚአብሄር በቃሉ ብዙ ተናግሮናል ሁሌም ይናገረናል :: ቃሉ የሚለንን ነን በእምነት እናገር እናውጀው: :
✔️እብራዊያን 11:6
ያለ እምነት እግዚአብሔር ማስደስት አይቻልም ይለናል ቃሉ::
እግዚአብሔር የሚደሰተው ቃሉ እንደሚለን ስናምና ስኖረው ነውና ዛሬ አባታችንን የምናስደስትበት የእምነትን ጸጋ በእጅጉ ያብዛልን: : አሜን!!!
✔️2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 05
6-7 እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥
ጌታ ሆይ ታምነህ ተሰማራ ይላል ቃልህና በማመን በእምነት የምንመላለስ ጸጋ በኢየሱስም ስጠን!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው እምነት
✅ እምነታችን እንዲያድግ እና እንዲፀና
✅ እምነት የእግዚአብሔርን ቃል ከመስማት ስለሆነ ወደ ቃሉ እንድንመለስ እንድናሰላስለው (ወደ ሮሜ 10
:17)
ወደ እምነታችን ራስ እና ፈፃሚ ወደሆነው ወደ እየሱስ እንቀርባለን
🙏
📖 የማቴዎስ ወንጌል 17
20፤ ኢየሱስም፡— ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፡— ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።
📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው ቸርነት እና በጎነት
✅ ሰማያዊው አባታችን እጅግ ቸር እና በጎ እንደሆነው ,
✅የእርሱ በጎነት እና ቸርነት ብቻ እስካሁም ስላቆመን
✅ እኛም ደግሞ የእርሱ መንፈስ ማደሪያዎች ስለሆንን
ቸርነታችን እና በጎነታችን ከዚህ በላይ እንዲገለጥ , ምሳሌ እንድንሆም , እንዲሁም ይህ ፍሬ የሁሉም ክርስቲያኖች መገለጫ እንዲሆን
በህብረት አባታችንን እንጠይቃለን 🙏
📖 መጽሐፈ ምሳሌ 19
17፤ ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።
ጌታ ኢየሱስ ሆይ ሀገራችንን ህዝቦቿንም በአንተ ሰላም ጎብኘን እንደ እኛ ሀጢአት እና በደል ሳይሆን እንደ አንተ ምህረት እና ቻይነት ታጋሽነት ይሁንልን ከውስጥም ከውጭም ወራሪ ጠላት ነፃ የወጣች ሀገር አድርግልን ከዘመኑ ወረርሺኝ ህዝብህን አድን ለመሪዎቻችንም ሆነ ለተቃዋሚዎች የልብ እና የአይምሮን ሰላምን ስጣቸው የአንተን ትእግስት አልብሳቸው ከአንተ የተማሩ አድርጋቸው አባት ለልጁ እንደሚራራ ለህዝባቸው የሚራሩ ለሰላም የሚተጉ ፊትህን የሚፈልጉ አስተዋይ ብልህ እና ጥበብ የሞላባቸው መሪዎች አድርገህ ባርካቸው!!! እኔ ሳይሆን እኛ የሚሉ ለእኔ ሳይሆን ለእኛ የሚሉ ቅን ታማኝ እና ሩህሩህ ትእግስት የሞላባቸው አገልጋዮች የሚሆኑበትን ፀጋ እና ጥበብን አውርሳቸው !!!
በጌታ በኢየሱስ ክቡር እና ድንቅ ስም እንለምንሃለን!!!🙏🏽
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ)
📌 የመንፈስ ፍሬ ስለሆነው ትእግስት
✅ ለብዙ ስራ እና አገልግሎት እንድንወጣ የሚያግዘንን
✅ ለሁሉም አይነት relationship መዝለቅ ቁልፍ የሆነውን ይህን አስፈላጊ የመንፈስ ፍሬ እንዲፈራ በየስፍራው
በህብረት አባታችንን እንጠይቃለን 🙏
📖 የያዕቆብ መልእክት 1
2-3፤ ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት
