en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
ክፍል 3 ከእናታችን ከማርያም ትህትናን እንማር ⨳እናታችን ማርያም የትህትና አስተማሪያችን ናት። ⨳በመጀመሪያ ትህትና ማለት ምን ማለት ነው? #ትህትና ማለት በእግዚአብሔር የተሰጠንን ነገር ተቀብለን በእርሱ መኖር ማለት ነው። ⨳ለዚህም ደግሞ ማርያም ትልቅ ምሳሌያችን ናት።እግዚአብሔር የሰጣትን (ያሰበላትን) ህይወት በእሺታ ተቀብላ የኖረች። የራሷን ሀሳብ ሳታስቀድም እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ የኖረች።ትህትና ማለት ይሄ ነው እግዚአብሔር ያሰበልንን የሰጠንን ነገር በእምነት ተቀብለን መኖር መቻል። #እኛስ በህይወታችን ምን ያህል በትህትና ኖረናል? #እንደ ፍቃድህ አኑረኝ ብለን ስንፀልይ ፍቃዱ በእኛ እንዲሰራ ፈቅደን ነው ወይስ በልምድ? ⨳በትህትና መኖር ስንጀምር ከራሳችን ሀሳብ ይልቅ ለእግዚአብሔር ፍቃድ ቅድሚያ እንሰጣለን። የፀለይነው ባይሳካልን ከማማረር ይልቅ ለመልካም ነው የእግዚአብሔር ፍቃዱ ሌላ ነው ብለን እናመሰግናለን።ምክንያቱም የጠየቅነው ነገር የማይጠቅመን ይሆን ይሆናል። አንዳንዴ እኮ እራሳችን ለእራሳችን ባለማወቅ የምንፀልየው ነገር መጥፊያችን (የማይጠቅመን) ይሆናል። #የእግዚአብሔር ሀሳብ ግን በእኛ ላይ ሁሌም መልካም ነው።ይህን ሀሳብ ከተረዳን በትህትና መኖር (የተሰጠንን ,የተፃፈልንን) ነገር ተቀብለን መኖር ቀላል ነው ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሀሳብ በእኔ በአንተ እና በአንቺ ላይ ሁሌም መልካም ነው። ⨳ሊከብደን ወይም የተለያዩ ፈተናዎች ሊገጥሙን ይችላሉ።ነገር ግን እግዚአብሔርን በማመን እነዚህን ሁሉ የምናልፍበት የፀጋ ሀይል እግዚአብሔር ይሰጠናል። ⨳ማርያምም የተሰጣትን ህይወት ተቀብላ ስትኖር ችግሮች ገጥመዋታል እንደ ስደት ,የልጅዋ ስቃይ ,የልጅዋ ሞት ድረስ ነገር ግን እነዚህን ሁሉ በእግዚአብሔር በማመኗ በፀጋው ሀይል አልፋቸዋለች።

ክፍል ሁለት እንደ ማርያም መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን እንዲሰራ እንፍቀድለት ⨳እናታችን ማርያም ለመንፈስ ቅዱስ ታዛዥ የሆነ ህይወት አላት።ለመንፈስ ቅዱስ ታዛዥ የሆነ ህይወት ስለነበራት መላኩ መቶ ሲያበስራት እውነተኛ መልዕክት እንደሆነ እንድታውቅና እንድታምን ያደረጋት መንፈስ ቅዱስ ነው። ሉቃ 1:34-35 34-ማርያምም መልአኩን ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?አለችው። 35-መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል። የልዑልም ኃይል ይፀልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። ⨳ኤልሳቤጥን ለመጎብኘት በሄደች ጊዜ ሰላምታ ስታቀርብላት በማህፀኗ ያለው ህፃን በደስታ ዘለለ።መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሲሰራ ተግባራችንና ቃላቶቻችን ለሌሎች ሰዎች ሰላምና ደስታ ይሰጣሉ። መንፈስ ቅዱስ በህይወታችን ሲሰራ በምግባራችን ሌሎች እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ። ከአንደበታችን የሚወጣው ሁሉ የምስጋና ቃላት ናቸው።ከማማረር ህይወት እኖጣለን። ⨳እኛም በህይወታችን እንደ እናታችን ልባችንን ለመንፈስ ቅዱስ ክፍት ማድረግ አለብን። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን እንዲሰራ እንፍቀድለት።ስንፈቅድለት ወደ እውነት የህይወት መንገድ ይመራናል። እንዲሁም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች የሆኑትን ማስተዎል ,ጥበብ ,እውቀት ,ፈሪሀእግዘብሔር ,ምክር ,ሀይል በእኛ ውስጥ ይሰራሉ።እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በህይወታችን መልካም ፍሬ ማፍራት እንጀምራለን።ትህትና ,የዋህነት ,በጎነት ,ደግነት ,ትዕግስት ,ራስን መግዛት ,ፍቅር ,ርህራሄ.... እንገለጣለን #መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን በሙላት እንዲሰራ ልባችንን እንክፈትለት።

ክፍል 1 ማርያም እናታችን ናት ዮሐ 19:26-27 26-ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀመዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት እነሆ ልጁሽ አላት። 27-ከዚህ በኃላ ደቀመዝሙሩን እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰአት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት። ⨳በዚህ ክፍል ክርስቶስ ለሚወደው ደቀመዝሙሩ እናቱን እንደ እናት አድርጎ ይሰጠዋል።ደቀ መዝሙሩም በደስታ ተቀብሎ ወደ ቤቱ ወሰዳት። ⨳ዛሬም ክርስቶስ እኛን ስለሚወደን እናቱን እነሆ ልጆችሽ ብሎ እናታችን አድርጓታል። #እኛስ ምን ያህል የተሰጠንን ልጅነት ተቀብለን እናትነቷን አምነን ወደ ቤታችን ወስደናታል ወደ ውስጣችን አስገብተናታል? ⨳እናትነቷን ተቀብለን ስንኖር ክርስቶስ ወንድማችን እግዚአብሔር አባታችን እኛ ልጆች ነን። ⨳ብዙ ጊዜ ልጅ በአንድ ቤተሰቡ ፀባይ ነው ሚወጣው። #እኛስ ከእናታችን ማርያም የቱን ፀባይ ወስደናል? ከክርስቶስስ? ⨳ከክርስቶስ- ፍቅር ,ምህረት , ይቅር ባይነት , ቸርነት..... ⨳ከማርያም-ትህትናዎን , ዝቅባይነቷን, ታዛዥነቷን ,አሰለሳይነቷ(ማገናዘቧን) , ፅናቷን... መውሰድና እንደሷ ለመኖር መጣር አለብን። ⨳ብዙ ጊዜ እናቶች ልጆች ጥፋት ሲያጠፋ ከአባቶች ጋር አስታራቂዎች ናቸው። እናታችን ማርያምም ጥፋት ስንሰራ ወደ ልጇ ታቀርበናለች አስታራቂያችን አማላጃችን ነች።ስለዚህ የተሰጠንን እናትነት ተቀብለን ወደ ውስጣችን ቤታችን እናስገባት ።

የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች ነገ እሁድ ግንቦት 1 ሳምንታዊ የከሰአት ፕሮግራማችን እንደማይኖር እናሳውቃለን።

ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ እያለ ከተናገረው የመጨረሻ ቃላት መካከል “...አባት ሆይ፤ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው...” — ሉቃስ 23፥34 የሚለው አንዱ ነው የበደሉንን ሰዎ
ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ እያለ ከተናገረው የመጨረሻ ቃላት መካከል “...አባት ሆይ፤ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው...” — ሉቃስ 23፥34 የሚለው አንዱ ነው የበደሉንን ሰዎች በሙሉ ይቅር ማለትን ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ አስተምሮናል ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ካደረገ በኋላ ከተናገረው የመጀመሪያ ቃላት መካከል “...ሰላም ለእናንተ ይሁን...” — ሉቃስ 24፥36 የሚለው አንዱ ነው ሰላም በትንሣኤ የተሰጠን የመጀመሪያው ስጦታ ነው በዚህ የትንሣኤ በዓል እርስ በእርሳችን ይቅር እንድንባባልና የክርስቶስን ሰላም ለዓለም እንድናውጅ እግዚአብሔር ይርዳን። እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ክርስቶስ በመስቀል ..... ፫ ዓለምን ዓዳነ ፣ እየሱስ የሞተው ለዓለም ሁሉ ነው፣ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሁሉ እንዲድን ይፈልጋል [1 ቲቶ 2፡3-6 ፣ 2 ጴጥ 3፡9] ስለዚህም ልጁ እየሱስ በአብ ዘንድ ጠበቃ ሆነልን [1 ዮሐ 2፡1-2] እየሱስ ለዓለም ያላት ብቸኛ ተስፋ ነው፣ እየሱስ ወደ አብ የሚወስድ ብቸኛ መንገድ ነው [ዮሐ 14፡6]። እንድንበት ዘንድ ለሰዎች የተሰጠ ከዚህ ስም በስተቀር ሌላ ስም ከሰማየ በታች የለም [ሐዋ 4፡12] ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ የለውም [1 ዮሐ 2፡23] በክርስቶስ ትምህርት የሚኖር ግን አብም ወልድም አለው [2 ዮሐ 9]ይህ መስቀል የሚያነሳሳን የጌታችን እየሱስ ክርስቶስ የማዳን ኃይል በኅጢአት ለታሰሩ ሰዎች እንድናውጅ ነው [2 ቆሮ 5፡18] ክርስቶስ በመስቀል ..... ፬ መስዋእት እንድንሆን ምሳሌ ሆነን ፤ እየሱስ በሞቱ ትህትናን አስተማረን [ፊል 2፡3-8] እንዲሁም በስቃዩ ትዕግስትን አስተማረን [1 ጴጥ 2፡20-24]። እየሱስ በመስቀል ለኛ፣ በፍቅር እንድንመላለስ [ኤፌ 5፡2]፣ በትህትና እንድንመላለስ [ፊል 2፡3-5]፣ መልካም ላደረግነው በክፉ ለሚመልሱ ትዕግስት እንዲኖረን [1 ጴጥ 2፡20-24]፣ ራሳችንን ለሌሎች አሳልፈን እንድንሰጥ [2 ቆሮ 8፡9 ፣ 1 ዮሐ 3፡16-18] ምሳሌ ሆነ የክርስቶስ የመስቀል ሞት ብዙ ሚስጥራትን የያዘ ነው። ሆኖም ለዛሬ ከላይ ባነሳንው ነጥብ ላይ ወደ ውስጣችን ገብተን ራሳችንን እንድንመረምር እጋብዛችኋልሁ። ሐዋሪያው ጳውሎስ እንዳለው “ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ እንደ መሆናችን መጠን፣ የተቀበላችሁትን የእግዚአብሔርን ጸጋ ከንቱ እንዳታደርጉት ዐደራ እንላችኋለን።” — 2ኛ ቆሮንቶስ 6፥1

#ዓርብ_ስቅለት የጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ስቅለት እጅግ አሳዛኝ ክስተት ነው ። በአንድ በኩል ከባድ የሆነ ስቃይ የተሞላ ሞት ሲሆን [ማቴ 27፡32-35] በሌላ በኩል ደግሞ ውርደትንና ፌዝን እንዲሁም ከወንበዴ መሃል መቆጠርን የያዘ አሳፋሪ ሞት ነው [ማቴ 27፡36-44]። ክርስቶስ በሞት መሃል ሆኖ እንኳን ሰዎች ስለሱ እንዲያለቅሱ አልፈለገም [ሉቃ፡23 26-31] ይልቁንስ ስለራሳቸው እንዲያለቅሱ ነገራቸው። የዓርብ ስቅለት ዋና ዓላማ ለክርስቶስ ከንፈር እንድንመጥ እና እንድናዝን ማድረግ ሳይሆን ስለኛ የተከፈለውን መስዋእት እንድንረዳ ነው። ክርስቶስ በመስቀል ..... ፩ ስለኅጢአታችን ዋጋን ከፈለ፤ እየሱስ በመስቀል የሞተው ስለኛ ኅጢአት ሲል ነው [1 ቆሮ 15፡3 ፣ ኢሳ 53፡5-6] ኅጢአታችንን በእንጨት መስቀል ላይ ተሸከመ [1 ጴጥ 2፡24] ይህ መስቀል የሚያስታውሰን ሁላችንም ኅጢአትን መስራታችንና ኅጢአታችንን ብንናዘዝ ከኅጢአታችን ይቅር እንደሚለን ነው [1 ዮሐ 8-10] ክርስቶስ በመስቀል ..... ፪ ታላቅ ፍቅሩን ገለጸ፣ እየሱስ ለመስቀል ሞት ያደረሰው ፍቅር ነው ። እግዚአብሔር ዓለምን እንደወደደ [ዮሐ 3፡16 ፣ ሮሜ 5፡8] እንዲሁም ልጁ እየሱስ እኛን ይወደናል [ኤፌ 5፡2] [1 ዮሐ 4፡9-10] እየሱስ እውነተኛ ፍቅርን አሳየን፣ እኛም የፍቅርን ትርጉም በመስቀሉ ተረዳን [1 ዮሐ 3፡16 ፣ ዮሐ 15፡13] የሱ ፍቅር ለኛ መዋደድ መነሻው ነው [ዮሐ 13፡ 34-35 ፤ 15፡12] ይህ መስቀል የሚያስታውሰን ክርስቶስ ባሳየን ፍቅር እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ነው [1 ዮሐ 4፡11]

#ፀሎተ_ሐሙስ: ልናስባቸውና ልናሰላስላቸው የሚገቡን ክርስቶስ በፀሎተ ሐሙስ ያስተማረን ትምህርቶች ። 1. ቅዱስ ቁርባን (የማቴዎስ ወንጌል 26 ) ------------ 26፤ ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። 27፤ ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ 28፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው። ............................//.............. 2. ክርስቶስ የሐዋሪያትን እግር አጠበ (የዮሐንስ ወንጌል 13 ) ------------ 14፤ እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። 15፤ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። ............................//.............. 3.ክርስቶስ የአሰቆሮቱ ይሁዳን እግር አጠበ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጠው እያወቀ በፍፁም ፍቅር አቀረበው "፤ እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። " (የማቴዎስ ወንጌል 5: 44-45) ............................//.............. 4. ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን "በትህትና የሚያገለግል በእግዚአብሔር ፊት ትልቅ እንደሆነ" አስተማረ (የሉቃስ ወንጌል 22 ) ------------ 24፤ ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ። ... 26፤ እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን። ............................//.............. 5. ክርስቶስ መንገድ እውነት ህይወት እንደሆነ አስተማረ "፤ ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። " (የዮሐንስ ወንጌል 14: 6) ............................//.............. 6. ክርስቶስ የገባው ቃልኪዳን "፤ ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። " (የዮሐንስ ወንጌል 14: 27) ............................//.............. 7. እውነተኛ የወይን ግንድ (የዮሐንስ ወንጌል 15 ) ------------ 1፤ እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው። ... 5፤ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።

"...፤ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። " (የማቴዎስ ወንጌል 16: 24) መስቀል የህመም ምልክት ነው ። አብዛኞቻችን ህመምን ማስተናገድ አንፈልግም ። ነገር ግን ህመም ለመዳን አስፈላጊ ነው ። ሰውነታችን ህመምን በመጠቀም በውስጡ ስላጋጠመው በሽታ ያሳውቀናል ። ይህ ባይሆን ኖሮ ዝም ብለን በሞትን ነበር ። የመስቀል ህመም ለህይወታችን መዳንን ያመጣል ። ካለበት ሁኔታ የዳነ ሰው ለእግዚአብሄር ክብርና ምስጋናን ያቀርባል ። ከጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በፊት አንድም ሰው በፈቃዱ ወደ መስቀል የሄደ የለም ።እሱ ግን መከራና ስቃይ የበዛበትን መስቀል በመሸከም በሰውና በእግዚአብሔር መሀከል የነበረውን የሞት ግርግዳ አፈረሰው ። እየሱስም አለ "...፤እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። " (የማቴዎስ ወንጌል 16: 24) በየቀኑ የየራሳችንን መስቀል በተሸከምን ቁጥር እምነታችን እኛ ከምናውቀውና ከምናስበው በላይ እያደገ ይመጣል ። የመንፈስ እድገትም በልባችን ስር ይሰዳል ።

የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች ነገ እሁድ ሚያዚያ 17 በሚኖረዉ የሆሳዕና በአል እንዲሁም በቀጣይ ሳምንት እሁድ ሚያዚያ 24 በፋሲካ በአል ምክንያት ሳምንታዊ ፕሮግራማችን እንደማይኖር እናሳውቃለን።

#ብርሃናችንን_እናብራ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”— ማቴዎስ 5፥16 ዛሬ እስኪ አንድ ነገር ለሕይወታችን እንጠይቅ ዛሬ
#ብርሃናችንን_እናብራ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”— ማቴዎስ 5፥16 ዛሬ እስኪ አንድ ነገር ለሕይወታችን እንጠይቅ ዛሬ በምድር ላይ ብዙ ችግሮች አሉ በተለይም በሀገራችን። ነገር ግን ለእነዚህ ችግሮች መፍትሔ ምን አስተዋፆ እያደረኩ ነው ብለን ራሳችንን እንጠይቅ በታማኝነት? ወይስ በተቃራኒው ለችግሮች አስተዋጽኦ እያደረግን ይሆን ሳናውቀው? የሁሉም መልስ በልባችን እና በድርጊታችን ውስጥ አለ እናስተውል። “እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” — ኤፌሶን 2፥10 እኛ የተጠራነው መልካምን ስራ ለማድረግ ነው ስለዚህ ምን እያደረኩ ነው ብለን ራሳችንን ጠይቀን ለትውልድ መፍትሔ እንሁን እግዚአብሔር አብሮነቱን የሚገልጠው ለተጠራንበት አላማ ስንቆም ነው። #ደስታችንም_እረፍታችንም_ያለው_አዚያ_ውስጥ_ነው። ስለዚህ ዛሬ አሁን ራሳችንን ጠይቀን ጥሪያችንን ለመኖር እንዘጋጅ እናድርግ እንጀምር እንስራ። ሌላው ምክሬ መስራት እንኳን ካቃተን በሚሰሩት ላይ አንናገር ዝም እንበል እሱም ቢሆን አስተዋጽኦ ነው። ዋጋው ጥቂት ቢሆንም የማይገባ ከመናገር ይሻላል። #መልካም_የተባረከ_ቀን @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው በወጣት ዲቦራ ጌቱ የመጨረሻ ክፍል ሮሜ 12:9-10 ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን።ክፉውን ነገር ተፀየፉት።ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ። በወንድማማች መዋደድ እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ እርስ በእርሳችሁም ተከባበሩ። ⨳ክፋውን ነገር ተፀየፉት ሲል ሀጥያትን ጥሉት ወይም ራቁት ማለት ነዉ።ከሀጥያት ለመራቅ መጀመሪያ ሀጥያትን እንደ ሀጥያት ማመን ያስፈልጋል።ያለበለዚያ ሀጥያቱን ሳናምንበት ንስሃ ብንገባም ፍሬያማ ንስሃ አይሆንም።አንዳንዴ ሀጥያት ሰርተን ሀጥያት እንደሆነ እያወቅን ግን ሀጥያቱን ሀጥያት ላለማድረግ ብዙ ምክንያት እንደረድራለን።ውጤቱ ግን አያምርም። ንሰሃ ስንገባ በእግዚአብሔር ፊት መዋረድ አለብን። ሃጢአትን ትንሽ ነው እያልን አንተወው ኃጢአት ከተውነው አድጎ ያስጨንቀናል። *ለምሳሌ አንድ አባት ልጁን ትልቅ ስብሰባ ላይ ይዞት ይሄዳል።ልጁ እየተሯሯጠ ስብሰባውን ረበሸው። አባትየውንም በትልቁ ስብሰባ ላይ አዋረደው።ከዚህ በመማር ከዛ በኋላ አባትየው ልጁን እንደዛ አይነት ፕሮግራም ላይ አንዴ ስላዋረደው ይዞት አይሄድም። *በተመሳሳይ እኛም ሃጥያታችንን በካህን ፊት ስንናዘዝ ካልተዋረድን ያን ሀጥያት ለመድገም ምንም አይዘንም።በካህን ፊት ከተዋረድን ግን አባትየው ልጁን ድጋሚ ይዞ እንደማይሄድ እኛም ድጋሚ ያን ሃጥያት ከማድረግ እንቆጠባለን። እግዚአብሔር ደግሞ የሚፈልገው የተሰበረና የተዋረደ ልብ ነው። እርሱንም አይንቅም። መዝ 51:16-17 መስዋዕትን ብትወድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መስዋዕት ደስ አያሰኝህም። የእግዚአብሔር መስዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። *ሀጥያት ፍቅርን ይሸረሽራል። ⨳ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ ሲል ሀጥያትን መስራት ማቆም ብቻ ለመንፈሳዊ እድገት ህይወታችን ሙሉ ፍሬ መስጠት እንደማይችል ይነግረናል።ሀጥያት መስራት አቁመን በሱ ፋንታ መልካም ነገር መስራት እንዳለብን ያስገነዝበናል። ኤፌ 4:28 የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ ነገር ግን በዚያ ፈንታ ለጎደለው የሚያካፍለው እንዲኖርለት በገዛ እጆቹ መልካምን እየሰራ ይድከም። ⨳እርስ በእርሳችን እየተዋደድን እንድንከባበር ይነግረናል። መዋደድ ከቻልን መከባበሩ ይመጣል። ለሁሉም ነገር መሰረቱ ፍቅር ነው። # ስለዚህ በፍቅር ውስጥ -ከሀጥያት መራቅ -መልካም ነገር ማድረግ -መከባበር -ይቅር መባባል - መዋደድ አለ። ⩩አሁን ላይ ለሃገራችን የሚያስፈልገው ምንድን ነው? -ብለን ስንጠይቅ ብዙ መልስ እናገኛለን በዋናነት ግን ሚያስፈልጋት ነገር ቢኖር ፍቅር ነው። ⨳በፍቅር ሲኖር ሁሌ የሰላም ,የእረፍት , የደስታ ዜና እንሰማለን።አሁን ላይ በሀገራችን ምንሰማው ግን በተቃራኒው ነው። ⨳ይህ የመጣው ከምን ይሆን? -ሀጥያትን እንደ ሀጥያትነቱ ባለመቀበል? -በራስ ወዳድነት? -ባለመከባበር? -ይቅር ባለመባባል? ወይስ ሌላ? ⨳ለሀገራችን ሰላም ሁላችንም የየራሳችን ሀላፊነት አለብን።እግዚአብሔር በቃሉ እንዳለን በፍቅር ከሁሉም ሰው ጋር እርስ በእርስ በመዋደድ ከጎናችን ካለ ሰው በመጀመር ከቃል ይልቅ በተግባር አርያ መሆን መቻል አለብን።በምድር እስከኖርን ያንዳችን መኖር ለሌላው መኖር አስፈላጊ ነው።ያንዱ ጉዳት የሌላውም ጉዳት ነው። ሮሜ 12:5 እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን።እርስ በእርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን። ⨳እኛም ሀላፊነታችንን ለመወጣት ትንሽ ነን ,ተሰሚነት ሊኖረን አይችልም ብለን ተስፋ ሳንቆርጥ የራሳችንን ሃላፊነት መወጣት አለብን። ⨳ለምሳሌ ከቧንቧ ውሃ መቅዳት ፈልገን ሃይል የላትም የሚንጠባጠብ ውሀ ነው ያለው።ውሃውን ከፈለግነው እና ካልዘጋነው ጊዜ ይወስዳል እንጂ ባልዲው ይሞላል።እያንዳንዱ ጠብታ ለባልዲው መሙላት የራሱ የሆነ አስተዋፆ (ጥቅም) አለው። ⨳እንደዚሁ በቁጥር ትንሽ ብንሆንም እራሳችንን ሳንገድብ በትዕግስት ልክ እንደ ጠብታዎቹ ሁላችንም የየራሳችንን አስተዋጽኦ በአንድነት በማድረግ የሃገራችንን ሰላም :- -በፀሎት -በፍቅር እና -በእግዚአብሔር ሀይል (መንፈስ ቅዱስ) ለመመለስ እንትጋ። 🙏 እኛ እርስ በእርስ በመዋደድ በፍቅር መኖር ስንጀምር በመጀመሪያ ለራሳችንን ከዛምለቤተሰባችን ,ለጎደኞቻችን ,ለአካባቢያችን ,ለቤተክርስቲያናችን ,እና ለሀገራችን እንዲሁም ለአለማችንም ሰላም ውጤት የለውም ብለን ሳንሰለች በትዕግስት የራሳችንን አስተዋጽኦ ማድረግ እንችላለን። በፍቅር ሁሉ ይቻላል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው በወጣት ዲቦራ ጌቱ ክፍል አምስት #ሁሉም_አገልግሎት_ከፍቅር_ይጀምራል 1ቆሮ 13:1-3 በሰዎችና በመላዕክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚ ሚንሸዋሸው ጽናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምስጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ ተራሮችንም እስካፈርስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል ስጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ⨳እያንዳንዱ ተግባራችን መነሻው ፍቅር ሊሆን ይገባል።እያንዳንዱ አገልግሎታችን መዘመር, ማስተማር, የበጎ አድራጎት ስራ ... የመሳሰሉት አገልግሎቶች መነሻቸው ፍቅር ካልሆነ ከጊዜ በኋላ መሰልቸት, ጊዜ ባለመስጠት ሊሆን ይችላል በጀመርነው ነገር ላይ ውጤታማ አለመሆን ይመጣል። ⨳ነገር ግን ወደነው የምንጀምረው ከሆነ ለአገልግሎቱን ፍቅር ይኖረናል። ከወደድነው ደግሞ ጊዜ በመስጠት እንሰራዋለን ። ጊዜ እየሰጠን የምንሰራው ከሆነ ደግሞ ከጊዜ ጊዜ በአገልግሎታችን እያደግን ውጤታማና ፍሬያማ እንሆናለን። ⨳ስለዚህ ለሁሉም ነገር መነሻው ፍቅር ሊሆን ይገባል።ያለበለዚያ እግዚአብሔር በቃሉ እንደነገረን እምነት ቢኖረን, ለድሆች ያለንን ብናካፍል, የትንቢት ስጦታ ቢኖረን መልካም መስለውን ያደረግናቸው ነገሮች ሁሉም ያለፍቅር ግን ከንቱ እንደሆኑ ይነግረናል። “ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።” — ዮሐንስ 21፥15 ኢየሱስ ለጴጥሮስ ያቀረበውን ጥያቄ ለእኛም ያቀርብልናል። ከአገልግሎታችን በፊት ጌታ እንደምንወደው ማወቅ ይፈልጋል። በእውነት ጌታን የምንወደው ከሆነ አገልግሎቶች ፍሬያማ ይሆናል። ሀሉ አገልግሎቶቻችን ከፍቅር የመነጩ ሊሆን ይገባል። 1ቆሮ 13:13 እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ። ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው በወጣት ዲቦራ ጌቱ ክፍል አራት #የፍቅር_ባህሪያቶች 1ቆሮ 13:4-8 ፍቅር ይታገሳል ቸርነትንም ያደርጋል ፍቅር አይቀናም ፍቅር አይመካም አይታበይም። የማይገባውን አያደርግም የራሱንም አይፈልግም አይበሳጭም በደልን አይቆጥርም ። ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ አመፃ ደስ አይለውም። ሁሉን ይታገሳል ሁሉን ያምናል ሁሉን ተስፋ ያደርጋል በሁሉ ይፀናል። ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም። ⨳እርስ በእርስ በእውነት በመዋደድ በፍቅር ስንኖር ከላይ የተዘረዘሩትን የፍቅር ባህሪያቶች በተግባር እንኖራቸዋለን።ይህም ደግሞ ከሰዎች ጋር ያለንን ግንኙነት እና አስተሳሰብ በመልካም እና እግዚአብሔር በሚወደው መንገድ እንድናረግ (እንድናስብ) ይረዱናል። ፍቅር ይታገሳል ማንም ሰው ፍፁም እንዳልሆነ ሁልግዜ ልናስተውል ይገባል። ሁላችንም ብንሆን የራሳችን የሆነ ስህተት ፣ ጉድለት ፣ ልዩ የሆነ ጠባይ ፣ የመቆጣት ባህሪ ወይም ያልተለመደ የንግግር ጠባይ ሊኖረን ይችላል። መፅሐፍ ቅዱስ ትእግስት ለሚለው ቃል በመከራ ውስጥም ሆነን የምናሳየው በፅናት የመቆየት ባህሪ እነደሆነ አድርጎ ይገልፀዋል። ትእግስት ያለው ሰው የማይገባ ነገር ከመናገርና ፍርድን ከመስጠት በፊት ነገሮችን በእርጋታ መረዳት ይፈልጋል። ፍቅር ካለን ማንኛውም ግንኙነት ውስጥ ትእግስት አለን ማለት ነው። ፍቅር ያለበት ትእግስት በፀጋ የተሞላ ነው። ትእግስት ስህተትን ከመፈለግ ይልቅ ሌላ ሰው ሙሉ አቅሙንና በክርስቶስ ያለውን ማንነቱን እንዲገልጥ ለመርዳት ያስችላል። ፍቅር ቸርነት ያደርጋል። ቸርነት ማለት ለሌላው መልካምን ነገር ማሳየት ወይም ትርፍን ሳይፈልጉና ምላሽን ሳይጠብቁ የደግነት ተግባር መፈፀም ነው። ቸር የሆነ ፍቅር ሁልግዜም ለሌላው ሰው ፍላጎት እጅግ ጥሩ የሆነውን የሚፈልግ ነው። ሁልግዜም ለመርዳት ፣ ለማፅናናት ፣ ለማበረታታት እና የወደቁትን ለማንሳት ነቅቶ የሚመለከት ነው። አንዳንድ ግዜ ትልቁ የቸርነት ተግባር የሚገለፀው የምንወዳቸውን ከውድቀት ለማዳን በአስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ጣልቃ መግባት ነው። ቸርነት ጠንካራ የሆነ ፍቅር ነው። ፍቅር አይቀናም እውነተኛ ፍቅር በግንኙነት ውስጥ ተረጋግቶ የሚቆም ፍቅር ነው። በፍቅር ውስጥ ስንኖር አብረን ካለነው ሰው ጋርና ከሌሎች ሁሉ ጋር ባለን ግንኙነት ምቾት ይሰማናል። በስኬታቸው እና በለውጣቸው ቅር አንሰኝም በደስተኝነታቸው አንቀናም። እንደውም አብረናቸው እያመሰገንን ሀሴት እናደርጋለን። መቅናት ማለት በአንድ ሰው ላይ ለሚሆን ማንኛውም መልካም ነገር በውስጣችን የሚፈጠር ምቾት የሚነሳ ስሜት ልንለው እንችላለን። ፍቅር ግን እንዲህ አይነቱን ባህሪ ያስወግድልናል። ቅናት የሌለበት ሕይወት ደስተኛ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ግንኙነቱን የሚያጠነክር እርካታ ያለው ሕይወት ነው። ፍቅር አይመካም መመካት ማለት ጉረኝነት ማለት ነው። ጉረኛ የሆነ ሰው ሁልግዜም ለራሱ ምስጋናን የሚያመጣ የራሱንም ክብር የሚያውጅ ነው። ጉረኛ ሰው ስላከናወናቸው ነገሮች ሌላ ሰው ማወቁን እርግጠኛ መሆን ይፈልጋል። እንደ እውነታው ከሆነ ጉረኛ ሰዎች ብዙውን ግዜ ለማንም ቢሆን ያላቸው ጠቀሜታ ጥቂት ነው። ምክንያቱም ግዜያቸውን የሚያጠፉት የጉራ ወሬያቸውን በመንዛት ስለሆነ ። ፍቅር ግን ለሌሎች መልካም ለማድረግ ስለሚቻልበት ሁኔታ በመነጋገር ግዜውን የሚሰጥ ነው። በፍቅር የሚኖሩ ጉራን ለመንዛት አይፈልጉም ምክንያቱም ስኬታማነታቸውንና ዓላማቸውን የሚያገኙት በስዎች ባገኙት ትኩረት እና ምስጋና ሳይሆን ይልቁንም የሰዎችን ፍላጎት ለማሟላት በክርስቶስ ኢየሱስ ስላገኙት ፀጋ አመስጋኝ ናቸው። እውነተኛ ፍቅር ራሱን የሚገልፀው በተግባር ነው በተገለፀ ግዜ ሁሉ ሰው ያውቀዋል። በፍቅር ሁሉም ቀላል ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነው በወጣት ዲቦራ ጌቱ ክፍል ሦስት እግዚአብሔርን ስንወድ መገለጫዎቹ ምንድን ናቸው? እግዚአብሔርን ትወደዋለህ? እግዚአብሔርን ከልብህ ስለምትወደው ፍቅርህን በምን መልኩ እየገለፅክ ነው? ራስህን ለእርሱ ወስነህ ሊሆን ይችላል። እንዲያውም እግዚአብሔርን እንደ ቅርብ ወዳጅህ አድርገህ ትመለከተው ይሆናል። በእርግጥ አንተ እግዚአብሔርን ከመውደድህ በፊት እርሱ ወዶሃል። መጽሐፍ ቅዱስ “እርሱ አስቀድሞ ስለወደደን እኛም እንወደዋለን ” ይላል።—1 ዮሐንስ 4:19 እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ያሳየባቸውን ብዙ ተዘርዝረው የማያልቁ መገለጫዎች አሉ። እኛስ ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር እንዴት እየገለጥን ነው። እግዚአብሔርን ስንወድ የተለያዩ መገለጫዎች አሉት።ከእነዚህም:- 1-#ከእግዚአብሔር_ጋር_የጠበቀ_ወዳጅነት_መጀመር። ለአንድ ሰው ፍቅር ካለን ግለሰቡን “እወድሃለሁ” በማለት ብቻ አንወሰንም። ለግለሰቡ ያለን ፍቅር ሕብረት በማድረግ እና ግዜ በመስጠት እርሱን የሚያስደስተውን ነገር በማድረግ መገለጥ አለበት። በተመሳሳይም ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር እርሱን በሚያስደስት መንገድ ለመኖር እና ከእርሱ ጋር ጊዜ ሰጥቶ ሕብረት በማድረግ የሚገለጥ ሊሆን ይገባል። ሮሜ 8:15 አባ አባት ብለን የምንጮኸበት የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነት መንፈስ አልተቀበላችሁምና። ⨳እግዚአብሔርን ስንወድ አባቴ ብለን የምንጠራበትን የነፃነት መንፈስ እናገኛለን።ከእርሱም ጋር እውነተኛ የአባትና ልጅ የጠበቀ ግንኙነት እንፈጥራለን። 2-#ትዕዛዙን_እንጠብቃለን። ዮሐ 15:9-12 አብ እንደወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኳችሁ በፍቅሬ ኑሩ።እኔ የአባቴን ትዕዛዝ እንደጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር ትዕዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈፀም ይህን ነግሬአችኋለሁ። እኔ እንደወደድኋችሁ እርስ በእርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትዕዛዜ ይህች ናት። ⨳አንድን ሰው ስንወድ በቻልነው መጠን የማይወደውን ላለማረግ የሚወደውን ለማድረግና ለማስደሰት እንጥራለን። ⨳እግዚአብሔርንም ስንወድ እርሱን ለማስደሰትና ትዕዛዙንም ለመፈፀም መጣር አለብን።ትዕዛዙም በተደጋጋሚ እንደሚነግረን እርሱ እኛን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደወደደን እኛም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሰዎችን እንድንወድ ነው። 3-#እርስ_በእርሳችን_በመዋደድ። ዕብ 2:3 ትፀልዩ ዘንድ በመጠን ኑሩ ፍቅር የኋጥያትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በእርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ። ⨳አንድ ሰው አባቱን ሲወድ የአባቱ ልጆች የሆኑትን ማለትም እህትና ወንድሞቹን ይወዳቸዋል። ⨳እግዚአብሔርንም ስንወድ ከእርሱም ጋር የአባትና የልጅ ግንኙነት ከፈጠርን የእርሱ የሆኑትን የፈጠራቸውን ሰዎች ሁሉ እንደ እህትና ወንድም በመውደድ ፍቅራችንን መግለፅ እንችላለን። በፍቅር እንኑር። እግዚአብሔር ፍቅር ነው። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#እግዚአብሔር_የጠራን_ለፍቅር_ነውበወጣት ዲቦራ ጌቱ ክፍል ሁለት 1ዮሐ መልዕክት 4:20 ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሀሰተኛ ነው።ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል? ⨳ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሀሰተኛ ነው። *ምክንያቱም እውነት እግዚአብሔርን ከልብ እንወደዋለን ስንል በተዘዋዋሪ ሁሉንም በአምሳሉ የተፈጠሩትን ሰዎች ያለ አንዳች ልዪነት እንወዳቸዋለን እያልን ነው።ለዚህም ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል። “ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው።” — ሐዋርያት 9፥5 ⨳ይህን ቃል ስንመለከት ሳውል እያሳደደ የነበረው ክርስቲያኖችን ነው።በመንገዱ ኢየሱስ ሳውልን ሲገናኘው እና ጌታ ሆይ አንተ ማነህ ሲለው እኔ አንተ የምታሳድደኝ ኢየሱስ ነኝ ነው ያለው እንጂ እኔ አንተ የምታሳድዳቸው ክርስቲያኖች አምላክ ወይም ጠባቂ ነኝ አላለውም። ⨳ስለዚህ ከዚህ ምንረዳው በእያንዳንዱ ክርስቲያን ውስጥ ኢየሱስ እንደሚገኝ ። ምክንያቱም ክርስቲያኖች ሲሳደዱ ኢየሱስ እንደሚሳደድ አይተናል። ስለዚህ አጠገባችን ባለው ወንድማችን ውስጥ ኢየሱስን እናገኘዋለን።እንደዚህ ከሆነ ደግሞ አጠገባችን ያለን ሰው ወደድን ማለት እግዚአብሔርን በተግባር መውደድ ችለናል ማለት ነው። #በፍቅር_እንኑር #እግዚአብሔር_ፍቅር_ነው። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm