en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ለቤተሰቦች ሰላም ✅ በአሁኑ ሰአት 2.6 billion ሰዎች በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በlock down ( ቤት ውስጥ ) ይገኛሉ ✅ ይሄ ጊዜ ለአንዳንድ ሰላም ለሌለበት ቤት አስጨናቂ ጊዜነው በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ለሚኖሩ ሰዎች በተለይ ለሴቶች እና ለህፃናት የሰላሙን ጌታ እየሱስን እየጋበዝን የጠላትን ስራ እናፈርሳለን 📖 ትንቢተ ኢሳይያስ 61 1፤ የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤ ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ ለተማረኩትም ነጻነትን ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል።

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን! ለአብያተ ክርስቲያናት በተሰጠው የአየር ሰዓት መርሐግብር መሠረት ዛሬ ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ፍራንቺስኮስ ጋር በመላው ዓለም የሚደረገውየመስቀል መንገድ ጸሎት በአዲስ ቲቪ በቀጥታ ሥርጭት ይተላለፋል። ይኸውም በሁለት ምዕራፍ የሚደረግ ሲሆን ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ልዪ ልዪ ዝማሬዎችና የመስቀል መንገድ ገለጻ ይደረጋል። በመቀጠልም ከምሽቱ 4:00 ጀምሮ ከሮም የሚተላለፈው የመስቀል መንገድ በአማርኛ አብረን እንጸልያለን። በመሆኑም ምዕመናን ሁላችን ይህንን ምሽት በአንድነት በጸሎት እንድናሳልፍ ተጋብዘናል። ለቡ: ከላይ የተጠቀሰው ሰዓት በሙሉ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር መሆኑ የታወቀ ይሁን!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌መፅናናት እንዲሆን ✅ በአለም ዙሪያ እስከ ዛሬ ድርስ ከ90,000 በላይ ሰዎች በCOVID-19 ምክንያት ህይወታቸውን አጥተዋል , ለሞቱት የዘላለም እረፍትን ለቤተሰቦቻቸው ደግሞ መፅናናትን እንዲሰጥ በጌታችን በእየሱስ ስም እንፀልያለን 📖 2ኛ ቆሮንቶስ 1 3፤ የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 4፤ እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል፥ ስለዚህም እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር በምንጽናናበት መጽናናት በመከራ ሁሉ ያሉትን ማጽናናት እንችላለን።

ሚያዚያ 3 እና 4 ቅዳሜ እና እሁድ በመስጠት እግዚአብሔርን እናመልካለን የተከራችሁ ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ከቤተክርስቲያን በተላለፈልን ጥሪ መሠረት በ covid 19 ምክንያት በከፋ ችግር ላይ ለሚወድቁ ወገኖች በቻልነው መጠን እርዳታ እንድናደርግ ጥሪ ቀርቦልናል ። ከምግብ ዓይነቶች (ፓስታ፣ መኮረኒ፣ ሩዝ፣ ዱቄት፣ ስኳር፣ ጨው ፣ ምስር፣ ቂንጬ፣ ወዘተ..) የንፅህና መጠበቂያ (ኦሞ፣ ሳሙና፣ ወዘተ) እና የመተኛ ቁሳቁስ (ፍራሽ ፣ አንሶላ ፣ ብርድ ልብስ ወዘተ...).በገንዘብ መርዳት ለምትፈልጉ ደግሞ መመሪያው ላይ በተጠቀሰው የባንክ አካውንት ማስገባት ትችላላችሁ። የተከበራችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች አቅማችሁ በፈቀደ ሁሉ ለዚህ ዓላማ እንድትተባበሩ እያሳሰብን ብዙ የተሰጠው ብዙ ስለሚጠበቅበት እኛ ደግሞ ብዙ የተሰጠን ነን ስለዚህ በተለይ ተግባራዊ በሆነ ክርስትና ልንገለጥ ይገባል። አሁን ጌታን በመስጠት የምናመልከው ግዜ ነው። አመልኮአችን አይቆምም ይቀጥላል ጌታ ይባረክ!!! የማህበራችን የመሰብሰቢያ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እሰከ 9 ሰዓት በመድሀኒአለም ቅጥር ግቢ ይሆናል። “እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።” — ዕብራውያን 6፥10

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌የትንሳኤው ሀይል እንዲገለጥ ✅ በእኛ , በቤተሰቦቻችን , በወዳጆቻችን ✅በቤትክርስቲያችን በሀገራችን እንዲሁም በመላው አለም ላይ ወደ ሮሜ 8 11፤ ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።

Prayer against novel coronavirus Heavenly Father, loving and merciful God, we worship and adore You. In faith, we come before You asking for mercy and forgiveness for our sins against You and Your creation. In this time of anxiety and distress, we lift up to You the COVID-19 situation throughout the world. Abba Father, we beg You to halt the spread of this disease and to grant healing and comfort to those afflicted. Please cover everyone with the Precious Blood of Your Son, Jesus and protect all of us, especially those in the medical field, from any infection and harm. Lord Jesus, we beseech You to grace government leaders and medical experts with wisdom and knowledge to combat the spread of COVID-19 and to find a cure for it. Holy Spirit Lord, please breathe peace and new life into everyone. May You grace us with a strong sense of social responsibility to do the necessary, and to be prudent and considerate in our actions. Bless all people to work together as one family of God and to be compassionate to one another. Most Holy Trinity, we believe in You and we place all our hope in You. You are our strength and our shield; in You our hearts trust; so we are helped, and our hearts exult, and with our song we give thanks to You. (Psalm 28:7) Immaculate Conception, Mary our Mother, we seek your intercession for us, our loved ones, our communities and everyone in this world. Most Sacred Heart of Jesus, our Messiah and King, we trust in You. (X3) Amen.

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ለዚህ ለበሽታ ጉዳይ መፍትሄ እየፈለጉ ላሉ በተለያዩ የስራ ዘርፍ ላይ ላሉ መሪዎች ✅ከእግዚያብሄር የሆነ ምሪት እና ጥበብ እንዲመራቸው መጽሐፈ ምሳሌ 8 14፤ ምክርና መልካም ጥበብ የእኔ ነው፤ ማስተዋል እኔ ነኝ፥ ብርታትም አለኝ። 15፤ ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፥ ሹማምቶችም የቀናውን ነገር ይደነግጋሉ።

#ኮሮናቫይረስን በተመለከተ የ #ፓፓፍራንቼስኮስ መልዕክት ለቤተሰቦች! ወዳጆቼ እንዴት ዋላችሁ? ዛሬ (ምሽት) ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ወደ እያንዳዳችሁ ቤት የመምጣት እድል አግኝቻለሁ፡፡ በዚህ የጭንቅና የችግር ጊዜ ፈቃደኛ ከሆናችሁ ከሁላችሁም ጋር ለጥቂት ደቂቃዎች መነጋገር እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ወረርሽኝ እንዳያገኛችሁ ከቤተሰብ ዘንድ ሆናችሁ ከለመዳችሁት ኑሮ ለየት ያለ ጊዜ እየገፋችሁ እንዳለ አያለሁ፡፡ ከቤት ወደ ውጭ መውጣት የማይችሉ፣ ትምህርት ቤት መሄድ የማይችሉና የቀን ተቀን ሕይወታቸውን ማስኬድ የማይችሉ ልጆችና ወጣቶች በአዕምሮዬ ይመጣሉ፡፡ ቤተሰቦች በሙሉ በልቤ ውስጥ ይመላለሳሉ፣ በተለይም በሕመም ላይ ያለ ወዳጅ ያሏቸው ቤተሰቦች፣ ወይም በኮሮናና በሌሎች ምክንያቶች ኃዘን ውስጥ ያሉ ቤተሰቦች በልበ ውስጥ ናቸው፡፡ ስለ ብቸኛ ሰዎች ብዙን ጊዜ አስባለሁ፣ ይህችን የችግር ጊዜ መጋፈጥ ይበልጥ ለእነርሱ ከባድ ናትና፡፡ ከሁሉም በላይ አረጋውያን ለልቤ ቅርብ ሆነው ይታሳቡኛል፡፡ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ታመው ሆስፒታል የተኙትን ሕሙማን መርሳት አልችልም፡፡ ይህን ወረረስሽኝ ለማከም ራሳቸውን ለአደጋ ያጋለጡትን ባለሙያዎችና የማኅበረሰብ መሠረታዊ አገልግሎቶች እንዳይጓደሉ የሚሰሩትን ሰዎች ልግስና እረዳለሁ፡፡ እኚህ በየዕለቱና በየሰዓቱ የሚሰሩ ጀግኖች ናቸው! በገንዘብ ችግር ውስጥ ያሉትንና ስለ ሥራቸውና የወደፊት ሕይወታቸው የሚጨነቁትን ሁሉ አስታውሳቸዋለሁ፡፡ በዚህ ወረርሽኝ ምክንያት ስለራሳቸውና ስለወዳጆቻቸው ፍርሃት ለሚገባቸውና ሥቃያቸው ለሚበዛ የህግ ታራሚዎች፣ ሐሳቤ ከእነርሱ ጋር ነው፡፡ ራሳቸውን የሚከላከሉበት ቤት ለሌላቸው ጎዳና ተዳዳሪዎችም በሐሳቤ ይመላለሳሉ፡፡ ይህ ጊዜ ለሁሉም ሰው ከባድ ጊዜ ነው፡፡ ለብዙ ሰዎች እጅግ ከባድ ጊዜ ነው፡፡ ፓፓ ይህንን ያውቃሉ! በዚህ ንግግሬም ከሁላችሁ ጋር ያለኝን መንፈሳዊ ቅርበትና ለእናንተ ያለኝን ልባዊ ፍቅር ልገልጽላችሁ እወዳለሁ፡፡ ከቻልን ይህን ጊዜ በፍሬያማነት ለመጠቀም እንሞክር፡፡ ለጋስ እንሁን፣ በጎረቤታችን እርዳታችንን የሚፈልጉትን እንርዳቸው፡፡ ብቸኝነት እጅግ የሚሰማቸውን በስልክና በማኅበራዊ መረብ እንፈልጋቸው፡፡ በኢጣሊያንም ሆነ በመላው ዓለም በችግር ውስጥ ያሉትን ሁሉ ወደ ጌታችን በጸሎት እናቅርባቸው፡፡ ራሳችንን በአካል ከሌሎች ለይተን ብንቆይም፣ ፍቅር ከታከለበት በሐሳብና በመንፈስ ሩቅ መጓዝ እንችላለን፡፡ ዛሬ የሚያስፈልገን በፍቅር የተሞላ አዲስ አሰራር ነው፡፡ ከፊታችን ያለውን የሕማማት ሣምንት በተለየ ሁኔታ እናከብራለን፡፡ ይህ ሣምንት የወንጌልን ዋና መልዕክት ይገልጥልናል፤ ይህም የእግዚአብሔር ገደብየለሽ ፍቅር ነው፡፡ ከተሞቻችን በዝምታ ቢዋጡም፣ የትንሣኤ ወንጌል ድምጽ በውስጣቸው ያስተጋባል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ይላል፣ ‹‹በሕይወትም ያሉት ስለእነርሱ ለሞተውና ለተነሳው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ (ኢየሱስ) ስለ ሁሉ ሞተ›› (2 ቆሮ 5. 15)፡፡ በትንሣኤው ኢየሱስ ውስጥ ሕይወት ሞትን ድል ነስቷል፡፡ ይህ የፋሲካ እምነት ተስፋችንን ያለመልማል፡፡ ይህ ዛሬ ማታ ለእናንተ ማጋራት የምፈልገው ሐሳብ ነው፡፡ የሕማማት ሣምንት የተሻለ ጊዜ ለማየት ተስፋ የምናደርግበት ወቅት ነው፣ እኛም የተሻልን ሰዎች የምንሆንበት፣ ከክፋትና ከዚህ ወረርሽን ነጻ ወጥተን የምናይበት ተስፋ! ተስፋ አያስከፋም፣ ተስፋ ቅዠት አይደለም፣ ተስፋ ይህ ነው! በፍቅርና በትዕግስት ከተደጋገፍን የተሻለ ቀን ለማየት መዘጋጀት እንችላለን፡፡ ወደቤታችሁ ስለአስገባችሁኝ አመሰግናለሁ፡፡ በስቃይ ውስጥ ላሉት ሰዎች፣ ልጆችና አረጋውያን የርኅራኄ እጆቻችሁን ዘርጉላቸው፡፡ ፓፓ ለልባቸው ቅርብ እንደሆኑና እንደሚጸልዩላቸው እንዲሁም ጌታችንም ከክፉ ፈጥኖ እንደሚሰውረን ንገሯቸው፡፡ እናንተም አኔን በጸሎታችሁ አስቡኝ! መልካም እራት! በቅርብ እስከምንገናኝ ድረስ ደህና ሁኑ! ፓፓፍራንቼስኮስ መጋቢት 25፣ 2012 ዓ.ም

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 1ኛ ተሰሎንቄ 5 17-18፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።

Bemnet metseleye.m4a7.77 MB

Teaching about faith filled Prayer

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌የእግዚያብሄር ክብር እንዲገለጥ ✅ መልስ ለሌው ለሚመስል ወረርሽኝ ✅ በጭንቅ ውስጥ ላለ ሕዝብ ክብሩ እንዲገለጥ ሁሉም በርሱ እንደሆነ እንዲያውቅ በእየሱስ ስም እንፀልያለን የዮሐንስ ወንጌል 2 11፤ ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ህይወት ለጨለመባቸው እና ተስፋ ላጡ ሰዎች ✅ ህይወት እና ብርሃን የሆነውን የእየሱስ መንፈስ ባሉበት ቦታ እንልክላቸዋለን . . . ወደ ሮሜ 15 13፤ የተስፋ አምላክም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተስፋ እንድትበዙ በማመናችሁ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌በእግዚያብሄር ላይ ያለን እምነት እንዲጨምር ✅ በቃሉ እና በመንፈሱ ላይ እንድንተከል ትንቢተ ኤርምያስ 17 7፤ በእግዚአብሔር የታመነ እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። 8፤ በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በዚህ ወቅት በጎዳና ህይወታቸውን ለሚመሩ እና ለስደተኛ ሰዎች ✅በሀገራችን እንዲሁም በሁሉ አለም ለሚገኙ ✅በእግዚአብሔር የፀጋው ዙፋን ስር በእምነት እናስቀምጣቸዋለን እኛንም በእነዚህና በተለያዩ ችግር ላይ ለሚገኙ ወጎቻችን በቻልነው እንድንረዳ መንፈስ ቅዱስ እንዲመራን በእየሱስ ስም እንፀልይል ማቴዎስ 25 40፤ ንጉሡም መልሶ፡— እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።

worship song