en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 36 7፤ አቤቱ፥ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ! የሰው ልጆች በክንፎችህ ጥላ ይታመናሉ።8፤ ከቤትህ ጠል ይጠጣሉ፥ ከተድላም ፈሳሽ ታጠጣቸዋለህ።9፤ የሕይወት ምንጭ ከአንተ ዘንድ ነውና፤ በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች ✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን 📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው 📖 መዝሙረ ዳዊት 66 19፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ሰማኝ፤ የልመናዬን ድምፅ አደመጠ።20፤ ጸሎቴን ያልከለከለኝ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይመስገን።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች ✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን 📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው 📖 መዝሙረ ዳዊት 66 19፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ሰማኝ፤ የልመናዬን ድምፅ አደመጠ።20፤ ጸሎቴን ያልከለከለኝ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይመስገን።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌በአንበጣ መንጋ እየተጠቁ ላሉ ቦታዋች ✅የእግዚያብሄርን ምህረት ለህዛብችን ሁሉ እንጠይቃለን እርሱም እንደቃሉ ምድሩን ይፈውሳል 🙏 📖 2ኛ ዜና መዋዕል 7 13፤ ዝናብ እንዳይወርድ ሰማያቱን ብዘጋ፥ ወይም ምድሪቱን ይበላ ዘንድ አንበጣን ባዝዘው፥ ወይም በሕዝብ ላይ ቸነፈር ብሰድድ፥14፤ በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢልፈጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።15፤ አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ።

ውድ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች የጌታ ሰላም ይብዛላችሁ እያልን መጸበኛ የእሁድ ፕሮግራማችን ነገ ጥቅምት 1 ሚካኤል ቤተክርስቲያን በሚገኘዉ ACS አዳራሽ ከ9:00 ሰዓት ጀምሮ ይኖረናል።

ወደ ኤፌሶን 5 2፤ ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ። እግዚአብሔር ለእኛ ያደረገው ሁሉ እንዲሁ በጸጋ እንደሆነ ሁሉ እኛም እግዚአብሔር በመምሰል እንዲሁ በተወደድንበት ፍቅር ኢየሱስ እኛን እንደወደደን እንዲሁ እንድንወድ የሚያስችለውን ጸጋ እጅግ ያብዛልን:: ኢየሱስ መስዋት ሆኖ እራሱን ለእኛ አሳልፉ እንደሰጠን ሁሉ እኛም እርሱ እንዳደረገው ራሳችንን ለሰዎች አሳልፈልን የምንሰጥበት አቅም መረዳትና ማስተዋልን እጅግ እንዲበዛልን በኢየሱስ ስም እንጸልያለን:: ወደ ሮሜ 12 1፤ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። ሰውነታችንን ህያው መስዋት አድርገን ሲል ሁለንተናችንን መንፈሳችንን ነፍሳችንን ስጋችንን ለእግዚአብሔር መስዋት አድርገን መስጠት ሀጢያት የማይነግስበት አዲስ የሆነውን የተለወጠውን ማነት በእግዚአብሔር ፈቃድ ቁጥጥር ስር ህያው ሆኖ ነውር የሌለበት ህያው መስዋት ሆነን መቅረብ ነው:: እግዚአብሔር ምህረቱን ስለሰጠን እኛም ሁለንተናችንን ሰውነታችንን ለእግዚአብሔር መስዋት አድርገን እግዚአብሔር ከእኛ የሚፈልገውን ደስ የሚያሰኘውን አምልኮ ማቅረብ ይሁንልን አሜን!!! የተወደድንበትን ፍቅር በመረዳት በመንፈሳችን በነፍሳችን በስጋችን ለእግዚአብሔር መስዋእት ሆነን እንደ ብርሀል ልጆች መኖር በፍቅር መመላለስ ይሁንልን አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌በፍቅር ስለመመላለስ ✅ ልክ ክርስቶስ እኛን እንደወደደን ✅ እርሱም በፍቅር እንደተመላለሰ በህብረት እንፀለያለን 🙏 📖 ወደ ኤፌሶን 5 2፤ ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።

🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏 ✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏 📖 ትንቢተ ኤርምያስ 24 7፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ የሚያውቅ ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ በፍጹምም ልባቸው ወደ እኔ ይመለሳሉና ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።

1ኛ ተሰሎንቄ 5 23፤ የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ። አሜን የሰላምም አምላክ ሁለንተናችንን ይቀድስ አሜን!!! እግዚአብሔር ልጆች ቅዱሳን መሆን አለብን አሜን:: የሚቀድሰን እራሱ እግዚአብሔር ነው:: በራሳችን ብርታት በራሳችን ችሎታ አቅም እራሳችንን መቀደስ አንችልም:: ለመቀደስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሀይል ያስፈስገናል:: ዛሬም የእግዚአብሔር ቃል ሁለንተናችን መንፈሳችን ነፍሳችንና ስጋችን ያለነቀፋ ይሁኑ ይለናል:: ጠቅላላ እኛነታችን መንፈሳችን ነፍሳችና ስጋችን ለእግዚአብሔር መቀደስ መለየት የክብር እቃ እግዚአብሔር የሚከብርበት የሚቀድሰው የሰላም አምላክ ይቀድሰን ይለየን ያልተለየ ያልተቀደስ ነገራችን ዛሬ ይለይ ለክብሩ ይሁን አሜን:: ሀሌሉያ!!! መንፈሳችን ከእግዚአብሔር አባታችን ጋር ህብረት የምናደርግበት :- ወደ ሮሜ 8 16፤ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ነፍሳችን ሀሳባችን ስሜቶቻችን ፍላጎታችን የሚመነጭበት ልባችን ወይም አይምሮአችን:- የያዕቆብ መልእክት 1 14፤ ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል። ስጋችን ከመንፈስና ከነፍሳችን የሚሉትን የሚመሩትን የሚያደርግ ነው:: ወደ ሮሜ 8 13፤ እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ። ስለዚህ በእግዚአብሔር ፊት ጤናማ እና ቅዱሳን ሆነን እንድንገኝ ነፍሳችንን ከሀጢያት ከክፉ ምኞት መጎምጀት ሀሳባችንን ስሜቶቻችንን ለእግዚአብሔር በማስገዛት መጠበቅ የምንችልበትን መለኮታዊ የእግዚአብሔር ጸጋ ይብዛልን:: መንፈሳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሁል ጉዜ ህብረት እንድናደርግ እግዚአብሔር በሀይሉ በጸጋው በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ያበርታን:: ስጋችንን የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ በመሆኑ በስጋችን ሀጢያት እንዳይነግስ የሚያስችል የእግዚአብሔርን መለኮታዊ ጸጋ ያብዛልን:: የሚቀድስ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መንፈሳችንን ነፍሳችንን ስጋችንን ይቀድሰን አሜን!!! 1ኛ ተሰሎንቄ 3 12-13፤ ጌታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ሲመጣ፥ በአምላካችንና በአባታችን ፊት በቅድስና ነቀፋ የሌለበት አድርጎ ልባችሁን ያጸና ዘንድ፥ እኛ ደግሞ ለእናንተ እንደምንሆን ጌታ እርስ በእርሳችሁ ያላችሁን ለሁሉም የሚሆን ፍቅራችሁን ያብዛ ይጨምርም።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌የሰላም አምላክ ሁለንተናችንን እንዲቀድስ እንፀልያለን 1ኛ ተሰሎንቄ 5 23፤ የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 36 7፤ አቤቱ፥ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ! የሰው ልጆች በክንፎችህ ጥላ ይታመናሉ።8፤ ከቤትህ ጠል ይጠጣሉ፥ ከተድላም ፈሳሽ ታጠጣቸዋለህ።9፤ የሕይወት ምንጭ ከአንተ ዘንድ ነውና፤ በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን።

እግዚአብሔር አባት ሆይ ወደ አንተ እንጸልያለን እንተን የማያውቁ ብርሀን ያልበራላቸው አለም የዋጣቸው በድንግዝግዝ ያሉ በልማድ ቤተክርስትያን የሚመላለሱ ሁሉ በእስራት ላሉ ሁሉ የማዳንህ ብርሀን ይብራላቸው የመስቀሉ ብርሀን ያግኛቸው:: 1ኛ ቆሮንቶስ 1 18፤ የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና። የመስቀሉ ሀይል ያግኛቸው እውነት ይብራላቸው ከጨለማ ይውጡ ከእስራት ይፈቱ ከልምድ ከድንግዝግዝ ይውጡ የቃልህ ብርሀን ይብራላቸው ህይወታቸው ይቀየር አንተን ይወቁህ ጌትነትህን አዳኝነትህን የሚረዱበት የምስራቹን ቃል የሚሰሙበት ጆሮአቸውን ልባቸውን የሚከፍት መላእክቶችህን ላክላቸው አንተን ይወቁ አንተን የሚረዳ የሚያውቅ ትውልድ ይሁን ይቀየር ምድራችን አንተን በማወቅ ትሞላ በየአብያተ ክርስቲያኑ ሁሉ መነሳት ይሁን መለወጥ በቃልህ መኖር በቃልህ መመራት ይሁን!!! ጌታ ሆይ ማዳን ልማድህ ነውና ፍቅርህም ወሰን የለውም እናመሰግንሀለን: የዮሐንስ ወንጌል 3 16፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። አለምን እንዲሁ የወደድክ ማንም እንዲጠፋ የማትፈልግ የፍቅር ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ህዝብህን አድን ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን ይሁን ማምለጥ ይሁን:: ይቅር ባይ አምላክ በደልን የማትቆጥር ጌታ ሆይ አሳዳጅ የነበረውን ጳውሎስን በቀትር በብርሀን እንደተገናኘኸው ዛሬም ሕዝብህን በብርሀንህ አግኛቸው ማዳንህ ለሁሉም ይዳረስ በሰማይ ያለው መንግስትህ እንደሆነች እንዲሁም በምድር ይሁን በየሰው ልብ ይሁን በኢየሱስ ስም ጸለይን!!! ስለሰማኸን እናመሰግንሀለን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች ✅ በእኛ ላይ ስላሉ ወይም በምናቃቸው ላይ በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን 📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው 📖 መዝሙረ ዳዊት 116 1፤ እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት።2፤ ጆሮውን ወደ እኔ

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ስለ ነገው በሚካኤል ቤተክርስቲያን አዳራሽ ስለሚደረገው የምስጋና ፕሮግራም ✅የመንፈስ ቅዱስ በሙላት እንዲገለጥ ✅ አገልጋዮች ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንዲያገለግሉ ✅ በቦታው ለሚገኙ ቤተሰቦች መገኘትም ለማይችሉ ላይ የክብር እሳት እንዲያገኛቸው በእምነት እንፀልያለን የማቴዎስ ወንጌል 3 11፤ እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ ✅ሰላም መረጋጋት እንዲሆን ✅ ጠላት በሀገራችን ላይ የሚያስነሳውን አቧራ ሁሉ በእየሱስ ህያው ስም ሰጥ እንዲል በልጅነት ስልጣን እንናገራለን እንፀልያለን🙏 📖 የማቴዎስ ወንጌል 28 18፤ ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ።

የዮሐንስ ወንጌል 5:21 አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል የወደድከን ስለኛ የሞትክልን የዘለዓለም ህይወትን የሰጠኸን ዛሬም አንተን ከሞት ያስነሳው የእግዚአብሔር መንፈስ ከአሸናፊዎች የሚያስበልጠው ኃያል መንፈስ ከእኛ ጋር ስላለ እናመሰግንሃለን ከዚህም በላይ በሙሉ ሃይል በውስጣችን እንዲንቀሳቀስ እና የከበዱብንን ነገሮች ከመንገዳችን ከአምልኳችን ከመንፈሳችን ከቤታችን ከኑሮአችን ከትዳራችን ከልጆቻችን ከቤተሰቦቻችን በጌታ በኢየሱስ ስም ይነሳልን!!! ከአሸናፊዎች የሚያስበልጠው ክርስቶስን ከሙታን ያስነሳው የእግዚአብሔር መንፈስ ይሙላን በህይወታችን ይትረፍረፍ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም !!!!! አሜን 🙏🏽

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ህይወት ስለሚሰጠው ስለ ክርስቶስ መንፈስ ✅ በእኛ ውስጥ ስላለው ,ክርስቶስን ከሞት ስላስነሳው መንፈስ እናመሰግናለን ✅ በሙሉ ሀይሉ በውስጣችን እንዲቀሳቀስ ✅እንዳይቀሳቀስ የደፈነውንም ነገር ከእኛ እንዲነሳ በህብረት እንፀልያለን 🙏 📖 ወደ ሮሜ 8 11፤ ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።

የ2013 ዓ.ም የምስጋና የመክፈቻ ፕሮግራም መስከረም 24 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አዳራሽ።

Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌 ስለ ሰላም ✅አእምሮን የያዘን ከሰማይ ያልሆነ ሀሳን ፈርሷ ✅ የሰላም ንፋስ በሀገራችን ላይ እንዲፈስ ደግመን ደጋግመን እንፀልያለን 📖ወደ ፊልጵስዩስ 4 6፤ ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።7፤ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።