SOS HGS Jimma primary School
Open in Telegram
1 676
Subscribers
+124 hours
+27 days
-730 days
Posts Archive
GoogleReal-time meetings by Google. Using your browser, share your video, desktop, and presentations with teammates and customers.
Kabajamtootaa fi jaalatamtoota hojjettoota, barattootaa fi maatii barattootaa hordoftoota amantaa muslimaa mana barumsaa SOS JIMMAA hundi baga kabaja ayyaana IDAL ADAHA(ARAFAA) bara 2018tiin nagaan isin gahe. Ayyaanichis kan nagaa, kan jaalalaa fi kan gammachuu isiniif haa ta'u.
IID MUBARAK!
Mana Barumsaa SOS JIMMA
የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የ ኤስ ኦ ኤስ ትምህርትቤት የእስልምና እምነት ተከታይ ሠራተኞች ፣ ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም የኢደል አደሃ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ። በዓሉም የሠላም የጤና የደስታ ይሁንላችሁ። ኢድ ሙባረክ!
ጅማ ኤስ ኦ ኤስ ትምህርትቤት
+1
Kabajamtoota hojjettoota keenyaa, barattootaa fi maatii barattootaa hordoftoota amantaa kiristaanaa mana barumsaa SOS Jimmaa hundi baga kabaja ayyaana du'aa ka'uu gooftaa Iyyasuus Kiristoos bara 2018tiin nagaan isin gahe. Ayyaanichis kan nagaa kan jaalalaa fi kan gammachuu isiniif haatahu. Ayyaana Gaarii!!!
የተከበራችሁ የ ኤስ ኦ ኤስ ትምህርትቤት የክርስትና እምነት ተከታይ ሠራተኞች ፣ ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም የትንሳዔ በዓል በሠላም አደረሳችሁ። በዓሉም የሠላም የጤና የደስታ ይሁንላችሁ። መልካም በዓል!
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
በጅማ ' ሄርማታ ት/ቤት ' የተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊት ምንድነው ?
⚠️ ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ ፣ ውሏቸውን ፣ ባህሪያቸውን ፣ የሚያደርጉትን ተከታተሉ !
የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጅማ ቤተሰብ አባል ሄርማታ ትምህርት ቤት መምህር ፦
" የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ዕለት በጅማ ከተማ ሄርማታ ትምህርት ቤት ነው።
ሟች ሙሳብ መሃመድ ይባላል። ገዳይ ሙአዝ ቢላል ይባላል።
አንዱ የ16 ዓመት አንዱ ደግሞ የ17 ዓመት ታዳጊዎች ፤ የአንድ ክፍል ተማሪዎች ናቸው።
የተለየ ጠብ በመካከላቸው አልነበረም። ሟች የክፍል አለቃ ሲሆን ከትምህርቱ ጎን ለጎን የክፍሉን ፀጥታ የማስከበር ተግባር ላይ ነበር።
በእለቱ ገዳይ አስተማሪ አለመኖሩን ጠብቆ በክፍል መስኮት ለመዝለል ይሞክራል። በዚህም ጊዜ ሙሳብም ' ድርጊትህ ስነምግባራዊ አይደለም ትክክልም አይደለህም ' በማለት ይናገረዋል።
ገዳይም ' አንተ ምን ያገባሃል ? አይመለከትህም ' ብሎ ይመልሳል። ሙሳብ ' እኔ አለቃ እስከሆንኩ ድረስ ይመለከተኛል ' ሲል ይመልስለታል።
በኋላም እሰጣ ገባ ውስጥ ይገባሉ።
ከዚህ በፊትም ልጁ የባህሪ ችግር ስለነበረበት ስሙን ፅፎ ለመምህራን ሰጥቶበታል።
አሁን ፀቡ ሲፈጠር ' ከዚህ በፊትም እንዲህ አድርገኸኛል አለቅህም ' ይለውና ይያያዛሉ። በስፍራው የነበሩ ተማሪዎች ለማገላገል ቢሞክሩም ገዳዩ ተማሪ ስለት አውጥቶ አንገቱ ላይ ይወጋዋል።
ያን በኃይል ለመጣል ሲሞክር ድጋሚ ይወጋዋል። ይህን አሰቃቂ ወንጀል ከፈጸመ በኋላ አብረውት ከነበሩ 3 ግብረአበሮች ጋር ተያይዞ ይሮጣል።
ልጁን ለማተረፍ ተሞከረ። መምህራን ልጁን ይዘው ሆስፒታል ለመሄድ ሲሞከር በመንገድ ላይ ህይወቱ አልፏል።
ገዳይም የ17 ዓመት ልጅ የሆነው ሙአዝ ሊያመልጥ ቢሞክርም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
ልጁ ያጨሳል፣ ሲጋራ፣ ጋንጃ፣ ሃሺሽ እና የመሳሰሉትን አደንዛዥ እጾች ይጠቀም እንደነበር ታውቋል ፤ በባህሪም አስቸጋሪ ልጅና ከሌሎች ትምህርት ቤቶች ተባሮ የመጣ ነው።
ሟች ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል። ሰዎች ፍትህ እንዲሰጥ ሰልፍ ለመውጣት ሞክረው ነበር።
እንዲህ ያለ ተማሪ አደንዛዥ እፅ የሚጠቀም በባህሪም የሚያስቸግር ሆኖ ሳለ እንዴት አትከታተሉም በሚል የታሰሩ መምህራን ነበሩ። ጥበቃውም ታስሯል። ልጁ ደም እየፈሰሰው " ነገሩ እስኪረግብ " ብሎ አቆይቶ ነበር።
እናት በሰላም ደብተር አስይዛ የሸኘችውን ልጅ በደም ተለውሶ፤ ህይወቱ አልፎ አስክሬን ስትቀበል ምን ያህል መሰበርና ምን ያህል መሪር ሃዘን ውስጥ እንደምትወድቅ አስቡት።
ልጁም ህይወቱ አለፈ ፤ ገዳይም ለእስር ተዳረገ። ፖሊስ የምርመራ ስራ እየሰራ ነው።
ይህ ጉዳይ ተሸፋፍኖ እንዳይቀር ነው ያጋራሁት። ነገ በኔ የሚባል ነገር አለ። ነገ በእኔ ልጆችስ ቢደርስ ? እውነታን መናገር ይገባል።
ሟቹን በጉርብትና በትምህርት ቤትም በደምብ አውቀዋለሁ። ነገር ግን ገዳዩ ተማሪ ለኔ የቀረበ ነው። በቤተሰብ ደረጃም ከፍተኛ ኢኮኖሚ ያላቸው ናቸው።
ቤተሰብ ልጆቹን በአግባቡ ሊይዝ ሊጠብቅ፣ ሊቆጣጠር ይገባል። ባህሪያቸውንም መከታተል አለበት።
ዛሬ ላይ የ17 ዓመት ታዳጊ ስለት አንስቶ ጓደኛውን ገደለ ማለት አስቡት ነገ ምን አይነት ልጆች ሊመጡ እንደሚችሉ።
ወላጆች ልጆቻችንን በአግባቡ እንያዝ። ትምህርት ቤት ለቀን ብቻ መተው የለብንም። የት እንደሚውሉ ፣ ምን እንደሚሰሩ ፣ የሚጠቀሙት ነገ ካለ፣ የሚያደርጉት ነገር ካለ እንወቅ። ማህበረሰቡም የባህሪ ችግር ያለባቸውን ልጆች ' እኔ ምን አገባኝ ' ብሎ ከማለፍ ተከታትሎ ማረም አለበት። ነገ ወደሱም ይመጣል።
መንግሥት ፣ የፀጥታ አካሉም ትልቅ ኃላፊነት አለበት። በሌላ ነገር ትኩረት እየተደረገ ትውልድ መጥፋት የለበትም።
ሌላው ' ቲክቶክ ' የተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ከመጣ በኋላ በሃላል በአደባባይ መቦዘን፣ ማጨስ ፣ መጠጣት ፣ መሰዳደብ፣ በቡድን መደባደብ ልክ እንደፋሽንና ጥሩ ነገር ተቆጥሮ ትንንሽ ልጆች እንዲያዩት እየተደረገ ነው። ወጣቶች ገና በለጋነታቸው ወደ ወንጀል እንዲገቡ እየተገፉ ነው። በአደባባይ ወጥተው ይህን ኢ-ስነምግባራዊ የሆነ ባህሪ የሚያሳዩ ልጆች እንዲታረሙ ማድረግ ይገባል። የሚመለከታቸው አካላት ልጆችን፦
- ማጨስ፣
- መሰዳደብ፣
- መደባደብ
- መቦዘን፣ የሚያስተምሩ አካላትን አደብ ማስገዛት አለባቸው። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ጅማ
#TikvahEthiopiaFamilyJimma
@tikvahethiopia
ነገ በ 24/07/2018 ዓ/ም በከተማ ውስጥ በሚደረግ ሰልፍ ምክንያት መንገድ ስለሚዘጋጋ ትምህርት የሌለ መሆኑን እንገልጻለን።
Sababa Hiriira magaala keessa gaggefamuuf bor gaafa guyyaa 24/07/2018 barnoonni kan hin jirre ta'uu isaa beeksifna.
Sababa Hiriira magaala keessa gaggefamuuf bor gaafa guyyaa 24/07/2018 barnoonni kan hin jirre ta'uu isaa beeksifna.
Mana Barumsaa SOS Heermaan Gimaayinar Jimmaa
ኤስ ኦ ኤስ ሄርማን ግማይነር ትምህርት ቤት ጅማ
Guyyaa 11/05/2018
Yadanno/ማስታወሻ
Amajjii 12/05/2018A.L.I Barnoonni idilee guyyaa guutuu jira.
ጥር 12/05/2018 ት/ርት መሉቀን አለ።
ት/ቤቱ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
