en
Feedback
ኢቅረእ ኢስላማዊ መፅሀፍት መሸጫ

ኢቅረእ ኢስላማዊ መፅሀፍት መሸጫ

Open in Telegram

ኢቅረእ ኢስላማዊ መፅሀፍት መሸጫ የተለያዩ ኢስላማዊ ይዘት ያላቸው መፅሀፎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ካሉበት ቦታ እናደርሳለን🚙። አድራሻችን፦ ጎንደር እና አዲስ አበባ @Abuhafss ሰ.ቁ 0918290961 0920960367 0703290961

Show more
510
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአላህ ሥሞች ዙርያ አስደናቂ ትንታኔዎች እና የተለዩ እይታዎች የቀረቡበት ነው፡፡ መጽሐፉ ከአላህ (ሱ.ወ.) ሥሞችና ባህሪያት አንፃር ከዚህ ቀደም ያላየናቸውን በርካታ እይታዎችንና ነጥቦችን ያሳየናል
በአላህ ሥሞች ዙርያ አስደናቂ ትንታኔዎች እና የተለዩ እይታዎች የቀረቡበት ነው፡፡ መጽሐፉ ከአላህ (ሱ.ወ.) ሥሞችና ባህሪያት አንፃር ከዚህ ቀደም ያላየናቸውን በርካታ እይታዎችንና ነጥቦችን ያሳየናል፡፡ አላህን (ሱ.ወ.) ይበልጥ እንድናውቅም ዕድል ይሰጠናል፡፡ የረሳነውን ያስታውሰናል፡፡ ፈጽሞ ያላስተዋልነውንም መንገድም ይጠቁመናል፡፡ የተሰጡት ትንተናዎች የአላህን ሥሞችና ባህሪያት ከመፍራት ይልቅ እንድናፈቅራቸው የሚያደርጉን ናቸው፡፡ ከመሸሽና ከመራቅ ይልቅ በድፍረት እንድንቀርብ የሚጋብዙ ናቸው፡፡ አዘጋጅ ፡ ዐምር ኻሊድ ትርጉም ፡ ሙሐመድ ሰዒድ የገጽ ብዛት ፡ 396 የታተመበት ዓመት ፡ 2007 ከመጽሐፉ ፡ አላህ ሆይ! በስምህ እንኖራለን! … ሀያሉንና የተከበረውን አላህን ማወቅ የጠፋ ሕይወታችንን ለመመለስ የምንጠቀምበት አማራጭ የሌለው መንገድ ነው፡፡ የአላህን ስሞች ከነጥልቅ ትርጉማቸው በማወቅ የኢማን ጥማችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ የአላህ መልካም ስሞችን በጥልቀት የተረዳን እንደሆነ ከውስጣቸው የሚወጣው ብርሃን ሕይወትን በአዲስ መልኩ እንድንኖር ብርታትና ሀይል ይሆነናል፡፡› ኃያሉና የተከበረው አላህ (ሱ.ወ) ‹አል-ዐሊም› /እጅግ አዋቂ/ ነው፡፡ ‹አል-ዐሊም› በሆነው በአላህ ስም እንኖራለን፡፡ በዕውቀት እንኖራለን፤ መሃይምነትን ፈጽሞ አንቀበልም፡፡ ኃያሉና የተከበረው አላህ (ሱ.ወ) ‹አር-ረሒም› /እጅግ አዛኝ/ ነው፡፡ ‹አር-ረሒም› በሆነው በአላህ ስም የእዝነት ህይወት እንኖራለን፡፡ ጭካኔን መንገዳችን አናደርግም፡፡ ኃያሉና የተከበረው አላህ ‹አል-ከሪም› /እጅግ ቸር፤ የተከበረ/ ነው፡፡ ‹አል-ከሪም› በሆነው በአላህ ስም ቸርነትና ክብር የተሞላበት ሕይወት እንኖራለን፤ ስስትን አንወድም፡፡ ኃያሉና የተከበረው አላህ ‹አል-በዲዕ› /ከምንም ያስገኘ/ ነው፡፡ @iqera

መጽሐፉ በዋናነት ኢስላም ወርቃማው የሳይንስ እና የሥልጣኔ ማዕከል መሆኑን ይዳስሳል፡፡ በተለይ ከ8ኛው እስከ 14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን፡፡ ዓለም ጨለማ በነበረችበት ወቅት ኢስላም በሳይንሱ ዘርፍ በተለ
መጽሐፉ በዋናነት ኢስላም ወርቃማው የሳይንስ እና የሥልጣኔ ማዕከል መሆኑን ይዳስሳል፡፡ በተለይ ከ8ኛው እስከ 14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን፡፡ ዓለም ጨለማ በነበረችበት ወቅት ኢስላም በሳይንሱ ዘርፍ በተለይም በዋናነት በአውሮፓ በርካታ ፈርቀዳጅ ግኝቶችን ለዓለም አበርክቷል፡፡ ከጊዜ በኋላ ሌሎቹ ሳይንቲስቶች የሙስሊሞቹን ግኝት የራሣቸው አደረጉት፡፡ መጽሐፉ ይህንና መሰል ጉዳዮችን ይዳስሳል፡፡ ዝግጅት ፡ ሙሐመድ ዐሊ የገጽ ብዛት ፡ የታተመበት ዓመት ፡ ከመጽሐፉ ፡- 1. ኻሊድ ኢብን ዘይድ ይባላል፡፡ እ.ኤ.አ በ701 (በኛ በግምት 693/694 ዓ.ል) እንደሞተ ይነገራል፡፡ የትውልድ ቀኑ በውል አይታወቅም፡፡ በኬሚስትሪ ዘርፍ የተመራመረ ሙስሊም ሳይንቲስት ነው… 2. አውሮፓውያን ‘ገበር’ ይሉታል…፤ ምናልባት የልብስ የውስጥ ሽፋን ለማለት ይሆን? ምክኒያቱም ለታላቁ አንቶኒ ላቮይዘር መሰረት በመጣሉ አደባባይ የማናወጣህ የውስጥ ሊቃችን ለማለት ፈልገው ይሆናል፡፡ ነገሩ ከትርጉምም ችግር የመጣ ሊሆን ይችላል፡፡ የግብፁ መሪ ጀማል አብዱልናስር… ‘ገማል’ መባሉ ይታወቃል፡፡ ግመል የሚለው ቃል በአረብኛ ጀመል ነው፡፡ በእንግሊዝኛ ሲወረስ ደግሞ ካሜል ተብሏል፡፡ ገበር ‘ጃቢር’ ለማለት ነው… @iqera

አስሩ የዙልሒጃ ቀናቶች.pdf3.69 MB

ነገሮችን ስንጀምር ኢማናዊ ወጎች መጽሐፍ በሙሐመድ ስዒድ (ABX) (2) ያስገኘንን አምላክ፣ የሩሓችንን ባለቤት አላህን በቤታችን እናኑረው፡፡ በሱ ሥም ሕይወታችንን እንጀምር፡፡ እሱ የሌለበት ቤት ሰላም አይኖረዉም፡፡ ንትርክ አይለየዉዉም፡፡ በረካ የለዉም፡፡ እሱን ያስገባንበት እንደሆነ ያኔ ቤታችን መሠረቱ ይፀናል፣ ምሰሶው መሬት ይይዛል፣ ግድግዳው ቀጥ ይላል፡፡ አላህ የሠራው ቤት አይፈርስም፡፡ እሱ ያነጸው ህንፃ አይወድቅም፣ እሱ ያቆመው ምሰሶ አይዘምም፡፡ ስለ አላህ፣ ስለፈጠረን አምላክ፣ ስለ አንድዬ ጌታችን አብዝተን እንመሰክራለን፡፡ ሌሎችንም ወደ መንገዱ እንጣራለን፡፡ በዚህች ምድር ላይ የማያልፍ የለምና፤ ላያልፍም የመጣ ነገርም የለምና ፈጣሪያችንን ከፊታችን እናድርገው፡፡ በህይወታችን እናኑረው፡፡ በጉዳዮቻችን ሁሉ ዉስጥ እናስገባው፡፡ እሱን አስበን እንንቀሳቀስ፡፡ መቅደም ያለበትን እናስቀድም፤ የሚከተለውን እናስከትል፡፡ የምንኖረው፣ የምንሮጠው፣ የምንደክመው፣ የምንለፋው … የሱን ዉዴታ ለማግኘት ነው፡፡ ይህም የሰው ልጆች ሁሉ ትልቁ ግብ ነው፡፡ የአላህ ዉዴታ የስኬቶች ሁሉ ጣሪያ ነው፡፡  ምድር ላይ ስንኖር ለዱንያም ሆነ ለአኺራችን እንሠራለን፡፡ ለስጋችንም ሆነ ለነፍሣችን እንተጋለን፡፡ በዋጋ ደረጃ ግን አኺራችን አንደኛ ናት፡፡ ሁለተኛ ደግሞ ዱንያችን፡፡ እዚህ የምንኖረው ለጊዜው ነው፡፡ ዱንያን አልፈናት እንሄዳለን፡፡ ተጓዥ ለነገ ሕይወቱ ዛሬውኑ ነው የሚሰንቀው፡፡ ለነገ ጉዞው ነገ የሚሰንቅ መንገደኛ የለም፡፡ በኛ እጅ ካለው በሱ እጅ ያለውን እንተማመን፡፡ ዛሬ ካለን በላይ በሱ ተስፋ የምናደርገው ይበልጣል፡፡ ኢንሻአላህ አምላካችን ሳይሰስት ይሠጠናል ደስ ይለናልም፡፡  ወዳጆቼ! እኛ ብንቆጥብ ቶሎ ያልቃል፤ ለሱ ብናበድር ግን አጥፍ ድርብ አድርጎ ይከፍለናል፡፡ እኛ ብንበትነው ጠፍቶ ይቀራል፣ ለአላህ ብንሠጠው ግን ይበቅላል፡፡ እና አጥብቀን ብናስረው ይበጠሳል፣ ለአላህ ብንሠጠው ይጠነክራል፡፡ እኛ ብናስቀምጠው ይጎድላል፤ ለአላህ ብንሰጠው ግን ይፋፋል፣ ይበረክታል፣ ይሞላል፡፡ @iqera

ነገሮችን ስንጀምር (1) **** ወዳጆቼ … ነገሮች እኛ ስንሠራቸውና አላህ ሲሠራቸው የተለያዩ ናቸው፡፡ አላህ ሲሠራቸው ያምራሉ፣ እኛ ስንሠራቸው ያስጠላሉ፡፡ አላህ ሲሠራቸው ይለመልማሉ ያብባሉ፤ እኛ ስንሠራቸው ይጠወልጋሉ፡፡ እኛ ስንሰራሉ ይቀጭጫሉ ይሞታሉ። አላህ ሲሰራቸው ሕያው ይሆናሉ። ስለዚህ ከራሣችን በላይ አላህን እንመን፡፡ ጉዳዮቻችንን ለአላህ እንስጥ፡፡ ማንኛውንም መልካም ነገር ስንጀምር አላህን አስበን እንጀምር፡፡ የፈጠረን ጌታ በዉስጥ ጉዳዮቻችን ሁሉ ጣልቃ እንዲገባ ፈቅደን እንጀምር፡፡ የሱ ምልከታና ቅናቻ እንዲኖርበት ተማፅነን እንጀምር፡፡ "ኒያ ከሌለ ሥራ የለም" የተባለው ለዚህ ነው፡፡ ትክክለኛ ኒያ ማለት በበጎ ነገሮች ዉስጥ ሁሉ አላህን ማሰብ ነው፡፡ አላህ ነው ጉልበታችን፡፡ አላህ ነው መሪያችን፤ አላህ ነው ከምናስበው አድራሻችን፤ አላህ ነው አሣማሪያችን፤ አላህ ነው አሳኪያችን፡፡ ካልሆነ የጀመርነውን ነገር አንጨርስም መንገድ ላይ እንቀራለን፤ ማልደን ብንነሳም አንደርስም ጉዞው ላይ እንደክማለን፡፡ ገር ነገር ሁሉ ገር ሊሆን የሚችለው አላህ ሲኖርበት ብቻ ነው፡፡   የቱን ያህል ዕውቀትና ብልሃት ቢኖረንም ሥራችን ዉስጥ የነፍሣችን ጌታ አላህ (ሱ.ወ.) ከሌለበት ሥራችን ሁሉ ከንቱ ነው፡፡ በአላህ ድጋፍ ያልታገዘ፣ የሱ ይሁንታ ያላረፈበት ሥራ አድካሚነቱ ብዙ ነው፡፡ ለማስተካከል የቱን ያህል ብንለፋም እንከኑ እልፍ ነው፡፡ ጉድለቱ የትየሌሌ ነው፡፡ ጠግነን አንጨርሰውም፣ ቀብተን አናሳምረውም፣ አስተካክለን አናቀናዉም፣ አርመን ከዳር አናደርሰውም፡፡ ወዳጆቼ! መልካም ነገሮችን ሁሉ ስንጀምር ‹በአላህ ሥም› ብለን እንጀምር፡፡ መሃል ላይ ስንደርስ፤ ብርታቱንና ፅናቱን እንለምነው፡፡ ስንጨርስ ደግሞ አብዝተን እናመስግን፡፡ ስንቴ እንሥራ ብለን በራሣችን ተማምነን ተነሳንና እንደ ህፃን ልጅ ሥዕል የምናበላሸው በዛ መሠላችሁ! ስንቴ እናውቃለን ብለን ተመፃድቀን የምናጠፋው በረከተ!፡፡ እገዛውን ሳንሻ፣ እርዳታውን ሳንለምን፣ ቅናቻውን ሳንማፀን … ብቻችንን የምንሠራው ቤት ብንሠራውም ዕድሜ የለውም፡፡ ሁለመናው ያረገርጋል፡፡ መሠረቱ ደካማ ነው፣ ጣሪያው ያፈሳል፣ ግድግዳው ይዘማል፣ ምሰሶው ስጢጥ ስጢጥ ይላል፡፡ እና እናማ ይቀጥላል ምንጭ - ኢማናዊ ወጎች መጽሐፍ በሙሐመድ ስዒድ (ABX) @iqera

የጊዜ ጉዳይ እንጂ በዳይ በዚህ ምድር ላይ የእጁን ያገኛል፡፡ ዛሬ ቢፈነድቅ ቢደሠት ለጊዜው ነው፡፡ ዛሬን ሳይቀጣ ቢያልፍ እንኳ ነገ ሌላ ኬላ አለበት፡፡ በትንሳኤ ቀን የሚጠብቀው መዓት ከባድ ነው፡፡ በቂያማ ቀን ለምርመራ ዋናው መርማሪ ፊት ይቆማል፡፡ መልካም ምንዳዉን ሁሉ ዐይኑ እያየ ይነጠቃል፡፡ የበደላቸዉን  ሰዎች እንዲክስ ይደረጋል፡፡ የሚክሰዉም ዱንያ ላይ ከሠራው የመልካም ሥራ ምንዳው እየተወሰደ ነው፡፡ ዐይን እያየ የራስን መልካም ሥራ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ህመም አለ!!፡፡  በዚህ መልኩ  የበደለዉን ሁሉ ይክሳል፤ የሰረቀዉን ሁሉ ሳይወድ በግዱ ይመልሳል፡፡ መልካም ሥራ ከሌለው ወይም ለተበዳዮች ተሠጥቶ ካለ ከተበዳይ መጥፎ ሥራ ተቀንሶ ዕዳ እንዲሸከም ይደረጋል፡፡ በደል የትንሳኤ ቀን ድርብርብ ጨለማ ነው፡፡ በዳይ ሰው ኪሳራው ብዙ ነው፡፡ ማረፊያዉም ጨለማ ነው፡፡ ለበዳይ ሰው እዘንለት እንጂ ተበደልኩ ብለህ አትማረር፡፡ የተበዳይ ዱዓ ምላሽ አለው፡፡ የተበዳይን ጉዳይ አላህ አይረሳም፡፡ አንድ ቀን ይመልስለታል፡፡ እንባዉን በማረ ሁኔታ ያብስለታል፡፡  በደል ጉዳት ቢመስልም ትርፍ አለው፡፡ እናም ምን አሳሰበህ … @ከአላህ ጋር መጽሐፍ @iqera

ነቢያዊ ባህርያት ** 1.  ያገኙትን ሰው በሰላምታ ይቀድማሉ፡፡ 2.  የሚያካብባቸው የሆነ ብርሃንና ሞገስ አላቸው፡፡ 3. በተረጋጋ ሁኔታ ይራመዱ ነበር፡፡ 4. ያለ ጉዳይ ወይም ያለምክንያት አይናገሩም፡፡ 5.  ሲናገሩ ጠቅላይ በሆኑ ቃላቶች ነው፡፡ 6.  በሀሳብ ይሁን በሥራና አምልኮ ሌትም ሆነ ቀን ዕረፍት የላቸውም፡፡ 7. እጅግ ቸርና እጅግ ለጋስ ናቸው፡፡ 8. ዝምታ ያበዛሉ፡፡ ትካዜያቸዉም ተከታታይ ነው፡፡ 9.  ዘወትር የአላህን ፍጥረታት በመመልከት ድንቅ ተዓምራቱን ያስተነትናሉ፡፡ 10. ታጋሽና ቁጥብ፣ ጨዋና ራሳቸውን የገዙ ናቸው፡፡ 11. ለዓለማት ህዝብ ሁሉ መስተካከል ያስባሉ ይጨነቃሉ፡፡ 12. ከኩራት፣ ከመመፃደቅና ከጉራ የራቁ ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች ነቢዩ ዒሳን (ዐ.ሰ.) እንዳጥራሩት ሁሉ ሰዎች እንዲያጥሯሯቸው አይፈልጉም፡፡ 13. ገፍታራና ኮስታራ አይደሉም፡፡ በሻሻ ናቸው፡፡ 14.  ላያቸው ሁሉ የሚስብ ሐቀኛ ፊት አላቸው፡፡ 15.  ትንሿን የአላህ (ሱ.ወ.) ፀጋ እንደ ትልቅ ያያሉ፡፡ በልተዉም ሆነ ጠጥተው ያመሰግናሉ፡፡ 16.  አላህ (ሱ.ወ.) ከሰጣቸው ነገር አንድንም ነገር አያጣጥሉም፡፡ አይንቁም፡፡ 17.  ለራሳቸው አይቆጡም፤ ለራሳቸው አይሞግቱም፣ ለራሳቸውም አይሰሩም፡፡ 18.  ለሐቅ ሲሉ በእጅጉ ይቆጣሉ፡፡ ሐቅን እስኪያነግሱ ድረስም ዕረፍት የላቸውም፡፡ 19.  ወደ አንድ ነገር ሲያመለክቱ በሙሉ እጃቸው ነው፡፡ 20. የተቆጡ እንደሆነ ከቦታው ዘወር ይላሉ፡፡ 21.  ሲደሰቱ ዐይናቸውን ዝቅ ያደርጋሉ፡፡ ድል ሲያገኙ አምላካቸውን ማመስገን ያበዛሉ፡፡ 22. ሳቃቸው አብዛኛውን ጊዜ ፈገግታ ነው፡፡ 23. ወደቤታቸው ሲገቡ ጊዜያቸውን ለሶስት ይከፍላሉ፡፡ ለአላህ፣ ለቤተሰባቸውና ለራሳቸው፡፡ 24. ሰዎችን ያዋድዳሉ፤ የተጣላን ያስታርቃሉ፤ ግንኙነታቸው ተመልሶ እንዲጠናከር ያደርጋሉ፡፡   25. በየማህበረሰቡ ውስጥ ክብር የሚሰጠዉን ሰው ያከብራሉ፡፡ በህዝቦቹ ላይም ሀላፊነት ይሰጡታል፡፡ 26. ስለ ሰሓቦቻቸው ሁኔታ ይጠይቃሉ፡፡ የቸገረውንና የጠፋውን ያጠያይቃሉ፡፡ 27. መልካምን ነገር መልካም፤ መጥፎን ነገር መጥፎ ይላሉ፡፡ 28. በነገራቸው ሁሉ መካከለኛና ሚዛዊ ናቸው፡፡ ወጣ ያሉ አይደሉም፡፡ 29.  ሲታጠቡ፣ ሲለብሱ፣ ሲጫሙ፣ ፀጉራቸውን ሲያበጥሩ እንዲሁም ሌሎች መልካም ነገሮችን ሲሰሩ   ቀኛቸውን ያስቀድማሉ፡፡ 30.  ሰሐቦቻቸው እንዳይዘናጉ ብለው ስለሚፈሩ በየጊዜው ይመክሯቸዋል፡፡ 31.  ሁሉንም ነገር እንደሁኔታው ይቀበላሉ፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) የሻላቸውን ይወዳሉ፡፡ እሱ የመረጠላቸውን ሳይቆረቁራችው ይቀበላሉ፡፡ 32. የሕዝበ ሙስሊም መሪ ቢሆኑም ለየት ያለ ዙፋንም ሆነ መቀመጫ የላቸውም፡፡ አጃቢ ባንድም ሆነ ጠባቂ ሰራዊት አልነበራቸውም፡፡ 33. የቤቶቻቸው ጣሪያ ቅርብ ነው፡፡ አብዛኛው ምግባቸው ተምርና ውሃ ነው፡፡ 34. በከዕባ ዕድሳት ወቅት፣ የመዲና መስጂድ ሲገነባ፣ በኸንደቅ ምሽግ ቁፋሮ ጊዜ ትልቅ ተሳትፎ ነበራቸው፡፡   ይቀጥላል … @iqera

አስላሙዓለይኩም እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ 1  ራስን ፍለጋ ቁ2 2 ትርፋማው ንግድ 3 ዘረኝነት ይብቃ 4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና 5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ 6 ቁርአናዊ ዘይቤ 7 የዘር ካርድ 8 የሀገር ሰላም 11 ቀዷ ወል ቀደር 12 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ 14 የፍቅር በረከት 15 ቁርአን አይጋጭም 18 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ 19 ጣፋጭ ታሪኮች 20 ከአሏህ ጋር 21 ሂክማ 22 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና 23 ጣፋጭ ታሪኮች 24 ልብህን አስመልስ 25 ፍኖተ ጀነት 26 ለውጥ         @iqera

የጊዜ ጉዳይ እንጂ በዳይ በዚህ ምድር ላይ የእጁን ያገኛል፡፡ ዛሬ ቢፈነድቅ ቢደሠት ለጊዜው ነው፡፡ ዛሬን ሳይቀጣ ቢያልፍ እንኳ ነገ ሌላ ኬላ አለበት፡፡ በትንሳኤ ቀን የሚጠብቀው መዓት ከባድ ነው፡፡ በቂያማ ቀን ለምርመራ ዋናው መርማሪ ፊት ይቆማል፡፡ መልካም ምንዳዉን ሁሉ ዐይኑ እያየ ይነጠቃል፡፡ የበደላቸዉን  ሰዎች እንዲክስ ይደረጋል፡፡ የሚክሰዉም ዱንያ ላይ ከሠራው የመልካም ሥራ ምንዳው እየተወሰደ ነው፡፡ ዐይን እያየ የራስን መልካም ሥራ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ህመም አለ!!፡፡  በዚህ መልኩ  የበደለዉን ሁሉ ይክሳል፤ የሰረቀዉን ሁሉ ሳይወድ በግዱ ይመልሳል፡፡ መልካም ሥራ ከሌለው ወይም ለተበዳዮች ተሠጥቶ ካለ ከተበዳይ መጥፎ ሥራ ተቀንሶ ዕዳ እንዲሸከም ይደረጋል፡፡ በደል የትንሳኤ ቀን ድርብርብ ጨለማ ነው፡፡ በዳይ ሰው ኪሳራው ብዙ ነው፡፡ ማረፊያዉም ጨለማ ነው፡፡ ለበዳይ ሰው እዘንለት እንጂ ተበደልኩ ብለህ አትማረር፡፡ የተበዳይ ዱዓ ምላሽ አለው፡፡ የተበዳይን ጉዳይ አላህ አይረሳም፡፡ አንድ ቀን ይመልስለታል፡፡ እንባዉን በማረ ሁኔታ ያብስለታል፡፡  በደል ጉዳት ቢመስልም ትርፍ አለው፡፡ እናም ምን አሳሰበህ … @ከአላህ ጋር መጽሐፍ @iqera

የቀልብ በሽታዎችን ማወቅና ማከም ኢሕያእ ዑሉሚዲን ኢማም አል-ገዛሊ ***** የቀልብ በሽታዎች መነሻ ስሜትን መከተል ነው፡፡ አላህ የዕውቀት እና ከእምነት ብርሃን የሰጠው የቀልብን ችግሮችና በሽታዎች እንዲሁም የበሽታዎቹ መድኃኒቶች ምን እንደሆኑ ይረዳል፡፡ ይህን ያልተረዳ ሰው ያለው አማራጭ በጭፍን መከተል የሚገባዉን ሰው ማመን እና መከተል ብቻ ነው፡፡ ዕውቀት ደረጃ እንዳለው ሁሉ ኢማንም ደረጃ አለው፡፡ ዕውቀት ከኢማን በኋላ ነው የሚገኘው፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) እንዲህ ይላል፡- “አላህ እነዚያን ያመኑትን እና እነዚያም ዕውቀት የተሠጡትን በደረጃዎች ከፍ ያደርጋቸዋል፡፡” (አል-ሙጃዲለህ ፡ 11) ነፍስን ከመግታትና ፍላጎቷን ከመፃረር አንፃር በቁርኣንና ሐዲሥ የተላለፉ መልዕክቶች እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) “ሙእሚን በአምስት ብርቱ ነገሮች መካከል ይኖራል፡፡ እነርሱም - የሚመቀኘው ሙእሚን፣ የሚጠላው ሙናፊቅ፣ የሚጋደለው ካፊር፣ የሚያጠመው ሸይጧን እና የምትቀናቀነው ነፍስ፡፡” ብለዋል፡፡ (አቡበክር ኢብኑ ላል እንደዘገቡት፡፡) ነፍስ ተቀናቃኝ ጠላት እንደመሆኗ እሷን መታገል ግድ ነው፡፡ ታላቁ አላህ ነቢዩ ዳዉድን (ዐ.ሰ.) “ባልደረቦችህ የስሜታቸዉን ሁሉ አግበስብሰው እንዳይመገቡ ከልክላቸው፤ በዱንያዊ ስሜቶች ላይ የተንጠለጠሉ ቀልቦች አዕምሯቸው ከኔ የተጋረደ ነዉና፡፡” እንዳላቸው ተነግሯል፡፡ ነቢዩ ዒሳ (ዐ.ሰ.) “ለማያየው ቃልኪዳን ብሎ የተጣደ የስሜት ፍላጎቱን የተወ ሰው ምንኛ ታደለ!፡፡” ብለዋል፡፡ ነቢያችን (ሶ.ዐ.ወ.) ባልደረቦቻቸው ከጠላት ፍልሚያ ሜዳ ሲመለሱ “ከትንሹ ፍልሚያ ወደ ትልቁ ፍልሚያ እንኳን ደህና መጣችሁ፡፡” አሏቸው፡፡ “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ ትልቁ ፍልሚያ ምንድነው?” ሲሏቸው ፡ “ነፍስን መፋለም ነው፡፡” አሏቸው፡፡ (በይሀቂ ዘግበዉታል፡፡) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) “ታጋይ ማለት ነፍሱን በኃያሉና የተከበረው አላህ ትዕዛዝ ሥር እንድትዉል የሚታገል ነው፡፡” ብለዋል፡፡ (ቲርሚዚ ዘግበዉታል፡፡) ሱፍያን አሥ-ሠውሪይ -አላህ ይዘንላቸው- “ከነፍሴ በላይ ለማከም የከበደኝ ነገር የለም፤ አንዴ አሸንፋታለሁ፣ ሌላ ጊዜ ታሸንፈኛለች፡፡” ብለዋል፡፡ አቡል ዐባስ አል-ሙሲሊ ለነፍሱ እንዲህ ይል ነበር “አንድም በዱንያ ዉስጥ ከንጉሣን ልጆች ጋር አልተንደላቀቅሽ ወይም ደግሞ አኺራን ፍለጋ ከአላህ ባሮች ጋር አልበረታሽ! ምንድነሽ ግን አንቺ!፡፡ አንቺን ይዤ በጀነት እና በእሣት መካከል የታሠርኩ ይመስለኛል፡፡ ለምንድነው የማታፍሪው?!” አል-ሐሰን አል-በስሪ “ካልተገራ አስቸጋሪ ፈረስ በላይ ነፍስህ ናት መለጎም ያለባት፡፡” ይሉ ነበር፡፡ @iqera

አዲስ መጽሐፍ ከነጃሺ የኡስታዝ ሙሐመድ ዑመር መፃሕፍት ጥናትን መሠረት ያደረጉ በከፍተኛ ጥራት እና ልፋት የተዘጋጁ ናቸው። ሰሞኑን ደግሞ "ተምሣሌት" በተሠኘው መጽሐፉ ነቢያዊዉን ሕይወት እና ተምሳሌ
አዲስ መጽሐፍ ከነጃሺ የኡስታዝ ሙሐመድ ዑመር መፃሕፍት ጥናትን መሠረት ያደረጉ በከፍተኛ ጥራት እና ልፋት የተዘጋጁ ናቸው። ሰሞኑን ደግሞ "ተምሣሌት" በተሠኘው መጽሐፉ ነቢያዊዉን ሕይወት እና ተምሳሌትነታቸዉን ያስቃኘናል። ያንብቡት። @iqera