Ethio engineering Group
Open in Telegram
1 673
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-1130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
January '26
January '26
+12
in 0 channels
December '25
+29
in 0 channels
Get PRO
November '25
+43
in 0 channels
Get PRO
October '25
+26
in 0 channels
Get PRO
September '25
+28
in 0 channels
Get PRO
August '25
+22
in 0 channels
Get PRO
July '25
+30
in 0 channels
Get PRO
June '25
+30
in 0 channels
Get PRO
May '25
+23
in 0 channels
Get PRO
April '25
+7
in 0 channels
Get PRO
March '25
+42
in 0 channels
Get PRO
February '25
+22
in 0 channels
Get PRO
January '25
+16
in 0 channels
Get PRO
December '24
+48
in 0 channels
Get PRO
November '24
+38
in 0 channels
Get PRO
October '24
+32
in 0 channels
Get PRO
September '24
+43
in 0 channels
Get PRO
August '24
+45
in 0 channels
Get PRO
July '24
+29
in 0 channels
Get PRO
June '24
+22
in 0 channels
Get PRO
May '24
+26
in 0 channels
Get PRO
April '24
+29
in 0 channels
Get PRO
March '24
+23
in 0 channels
Get PRO
February '24
+23
in 0 channels
Get PRO
January '24
+1 595
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 26 January | +2 | |||
| 25 January | 0 | |||
| 24 January | 0 | |||
| 23 January | 0 | |||
| 22 January | 0 | |||
| 21 January | +1 | |||
| 20 January | 0 | |||
| 19 January | 0 | |||
| 18 January | 0 | |||
| 17 January | 0 | |||
| 16 January | +3 | |||
| 15 January | 0 | |||
| 14 January | 0 | |||
| 13 January | +1 | |||
| 12 January | 0 | |||
| 11 January | +1 | |||
| 10 January | +1 | |||
| 09 January | +1 | |||
| 08 January | 0 | |||
| 07 January | 0 | |||
| 06 January | +1 | |||
| 05 January | +1 | |||
| 04 January | 0 | |||
| 03 January | 0 | |||
| 02 January | 0 | |||
| 01 January | 0 |
Channel Posts
+4
ጥቅምት 18/2018 ዓ/ም(ኢኢግ) ለኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ፓወር ኢኩፕመንት ማምረቻ ኢንዱስትሪ አመራርና ሰራተኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ከአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በአመራር ጥበብ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የኢንዱስትሪው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያደኑ ትርፌሳ ባስተላለፉት መልዕክት በኢንዱስትሪው ይህን መሰል ስልጠና መዘጋጀቱ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልፀዋል። አመራሩና ሰራተኛው በትኩረት መሰልጠንና ወደ ተግባር መቀየር እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡
በስልጠናው ላይ 87 አመራሮች እና ሰራተኞች ስልጠናውን በመሰልጠን ላይ ይገኛሉ።
| 2 | ጥቅምት 14/2018 ዓ/ም(ኢኢግ) በብየዳ ሙያ ለሁለተኛ ዙር ለሰለጠኑ የኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ባለሙያዎች የዕውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተ፡፡
ስልጠናው የተሰጠው በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አማካኝነት ነው፡፡
የተሰጠው ስልጠና በአርክ ብየዳ (Arch wellding)፣ በሚግ ብየዳ (MIG wellding) ዘርፎች እና የብየዳ ጥራት መፈተሻ መሳሪያዎች እና የአፈታተሸ ሂደቶችን ያካተተ ነው፡፡
ስልጠናው የነበሩ ክፍተቶችን ለመሙላትና የምርት እና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ አስተዋፅኦው የጎላ ነው፡፡
የግሩፕ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የምርምርና ቢዝነስ ዲቨሎፕመንት ዘርፍ ኃላፊ አብዱልፈታህ ሼክ ቢሂ(ዶ/ር) ግሩፑ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በተለያዮ የትኩረት መስኮች በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት መተግበር፣ ማሻሻል እና ለሌሎች ባለሙያዎች ማስተላለፍ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከሁሉም ኢንዱስትሪ የተውጣጡ 20 የብየዳ ባለሙያዎች ለ10 ተከታታይ ቀናት የተሰጠውን የተግባር ስልጠና ወስደዋል፡፡ | 1 234 |
| 3 | ጥቅምት 13/2018 ዓ/ም(ኢኢግ)ለኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና መ/ቤት ሴት ሰራተኞች የጡት ካንሰር እና የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ቅድመ ምርመራ ግንዛቤ ማስጨበጫ እና ምርመራ ተሰጠ፡፡
የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አገልግሎት ሀላፊ ሐና ታምራት (ሲ/ር) ወሩ ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር መሆኑን ጠቅሰው ሁሉም ሴቶች ቅድመ መከላከልን እንደ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫው አላማ የሴቶች ጤና አጠባበቅ ስርዓትንን ለማዘመንና ዘመናዊ አኗኗርን ለመከተል ያግዛል፡፡ የተገኘውን ግንዛቤ ከራሳችን ባሻገር ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
መርሃ ግብሩ የግሩፑ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አገልግሎት ከአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ጋር በመተባበር ከለቡ ጤና ጣቢያ በመጡ ባለሙያዎች እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡ | 1 275 |
| 4 | ጥቅምት 12/2018 ዓ/ም(ኢኢግ) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የግሩፑ ዋና መ/ቤት በመገኘት አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የመስክ ምልከታ አካሄዱ።
በዚሁ ወቅት የግሩፑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ ባለፉት አምስት አመታት በግሩፑ ተመርተው በሀገሪቱ የተሰራጩ ምርቶችን አቅርበዋል። በተጨማሪም የ2018 በጀት አመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ አመት የስራ አፈፃፀም ላይ ገለጻ አቅርበዋል።
ግሩፑ ተኪ ምርቶችን በማምረት፣ የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን ከፍተኛ ተልዕኮ ይዞ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በተያዘው በጀት አመት በዝግጅት ምዕራፍ ቀደም ሲል የተዘጋጁ መመሪያዎችን መከለስ፤ ለፋብሪካዎች የግብአት ዝግጅት ማካሄድ፣ የፋይናንስ አቅም ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት ከግሩፑ ሰራተኞች ጋር ውይይት ያካሄዱ ሲሆን የተለያዩ የስራ ክፍሎችንም ጎብኝተዋል፡፡
ቋሚ ኮሚቴው በሰጠው ግብረ መልስ ግሩፑ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሚገኝ እና ማኔጅመንቱና ሰራተኛው ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን መገንዘባቸውን ገልጸዋል፡፡
በእቅድ ላይ የውል ስምምነት መፈረሙ ሁሉም እቅዱን በደንብ እንዲያውቅ ያደረገ መሆኑን መገንዘባቸውን ገልጸው ከዚህም ባሸገር የሃላፊነት እና የተጠያቂነት አሰራር እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል፡፡
በግሩፑ ምቹ የስራ ከባቢን ከመፍጠር አንፃር በዋናው መ/ቤት የተከናወነው የሪ ኢኖቬሽን ስራ፣ የአመራሩና ሰራተኛው ቅንጅት እና ቁርጠኝነት ፣የህፃናት ማቆያ ማእከል ስራ እና ጤና ጣቢያ በተደራጀ መልኩ አገልግሎት መስጠቱ ጠንካራ ጎን መሆኑን አንስተዋል።
የግሩፑን የምርምር ዘርፋን ማጠናከር ፣ የተቋሙን ኦዲት ሪፖርት ማጥራት፣ ኢ አር ፒን ሙሉ በሙሉ መተግበር፣ እንዲሁም ከህግ አንፃር የተያዙ ጉዳዮች እልባት እንዲገኙ ማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ የተባሉ ናቸው።በዚህ ረገድ ቋሚ ኮሚቴው የበኩሉን ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መለሰ መና በማጠቃለያ ንግግራቸው ግሩፑ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው መልካም ዕድሎችን በመጠቀም ዕቅዶችን ማሳካት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የተቋሙ ህልውና በጊዜ እና በጥራት ማምረት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ሊተኮርበት ይገባል ብለዋል፡፡
የደንበኛ እርካታን ማረጋገጥ፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚያግዙ አሰራሮችን ማዘመን ፣ ምርታማነትና ተወዳዳሪትን ማረጋገጥ፣ የግሩፑን አደረጃጀት በማጠናቀቅ ወደ ተግባር ማሸጋገር ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል።
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በግሩፑ ስር የሚገኘውን አዲሰ ማሽንና መለዋወጫ ማምረቻ ኢንዱሰትሪንም ጉብኝተዋል። | 888 |
| 5 | No text... | 1 035 |
| 6 | No text... | 622 |
| 7 | No text... | 587 |
| 8 | https://drive.google.com/file/d/14yCkAie-n4rbI20dEI4p5SzmoKynwsPV/view?usp=sharing | 609 |
| 9 | No text... | 1 086 |
| 10 | No text... | 867 |
| 11 | ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም (ኢኢግ) የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ አመራር እና ሰራተኞች በብሔራዊ ጥቅም እና የጂኦስትራቴጂ ቁመና ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የግሩፑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ ሃገራዊ ጉዳይ ላይ አመራሩ እና ሰራተኛው ግንዛቤ እንዲፈጥር መደረጉ በሃገሪቱ ጉዳይ ላይ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡
ሃገራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲኖር ግሩፑ የራሱ ድርሻ እንዳለው አስታውሰው ግሩፑ በ2018 አ.ም ያቀደው እቅድ እንዲሳካ መላው አመራሩና ሰራተኛው ሚናውን ሊወጣ ይገባልም ብለዋል፡፡
ሰነዱን ያቀረቡት የግሩፑ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የሃብት አስተዳደር ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ኦላኒ Daniel Olani Mekonnen ብሔራዊ ጥቅም፣ ጂኦ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ለማስጠበቅ እየተሰሩ ስላሉ ስራዎች፤ የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ እና እየተወሰዱ ስላሉ መፍትሄዎች አብራርተዋል፡፡
በቴሌ ሚቲንግ የቀረበውን ገለጻ መሰረት በማድረግ በዋና መስሪያ ቤት እና በግሩፑ ስር የሚገኙት ሰባት ኢንዱስትሪዎች የሚገኙ ከ3 ሺህ በላይ የግሩፑ ሰራተኞች በ12 ማእከላት ተሳትፈውበታል፡፡
የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ለሀገሪቱ እና ለጂኦ ስትራቴጂ ጠቀሜታ መረጋገጥ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተሳታፊዎች አንስተዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ መንግስት የወደብ ጥያቄን አጀንዳ በማድረግ፤ ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ እንዲሁም አለም አቀፍ ህጎችን መሰረት በማድረግ ለተጠቃሚነታችን እየሰራ ያለውን ስራ በማድነቅ ፤የወደብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የበኩላችንን ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
የውስጥ ችግሮቻችንን በሰላም ለመፍታት እየተደረገ ያለውን ጥረት በማጠናከር ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር ይገባልም ተብሏል፡፡
ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተቀርጸው እየተሰራበት እንደሚገኝ ያነሱት ተሳታፊዎቹ ጥረቶችን በማጠናከር ሃገራዊ የኢኮኖሚ የበላይት እንዲረጋገጥ የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል፡፡ | 817 |
| 12 | ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም (ኢኢግ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ፓወር ኢኩፕመንት ማምረቻ ኢንዱስትሪ ስር የሚገኘውን የትራንስፎርመር ፋብሪካ ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ታጠቅ ትራንስፎርመር ማምረቻ ፋብሪካ የተለያየ አቅም ያላቸውን ትራንስፎርመሮችን በማምረት፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ እና የአመራረት ሂደቱን በሚመለከት ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
ከጉብኝቱ በተጓዳኝ ሚኒስትሩ ከግሩፑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ ጋር እና ከግሩፑ ከፍተኛ አመራሮች እና ከኢንዱስትሪው ሃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱም የትራንስፎርመር ፋብሪካው ለሃገሪቱን የሃይል መሰረተ ልማት ግንባታ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ተገልጿል፡፡
በዚሁ ውይይት ሚኒስትሩ የፋብሪካውን የማምረት አቅም ማሳደግ እንደሚገባ እና በዚህም ረገድ የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደሚደግፍ ገልጸዋል፡፡
ፋብሪካውን መደገፍ የሚያስፈልገው ሌሎች ፋብሪካዎች ሃይል እንዲያገኙ ስለሚያደርግ፤ ድርብ ጠቀሜታ ስላለው ጭምር ነውም ተብሏል፡፡
ፋብሪካው ከትራንስፎርመር ምርት በተጨማሪም የጥገና እንዲሁም ባለው ላቦራቶሪ ከውጭ ለሚገቡ የትራንስፎርመር ምርቶች የሙከራ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ | 1 089 |
| 13 | ጥቅምት 4/2018ዓ/ም (ኢኢግ) ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም ግምገማ ተጠናቀቀ።
ለሁለት ቀናት በተካሄደው ውይይት ላይ ኢንዱስትሪዎች እና የስራ ክፍሎች የእቅድ አፈጻጸማቸውን አቅርበው ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የግሩፑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት የግብአት አቅርቦት ስርአትን ማሻሻል ይገባል፡፡ያልተቆራረጠ ግብአትን በማረጋገጥ ኢንዱስትሪዎች በሁለት ፈረቃ ጭምር እንዲያመርቱ ሊደረግ ይገባል፡፡በጥሩ ይዞታ ላይ የሚገኙ የማምረቻ ፋሲሊቲዎችን ሙሉ በሙሉ ተጠቅሞ ምርት ማምረት እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡
የካይዘን እና የጥራት ስራ አመራር ስራዎችን ማጠናከር፤የፕላንት ዲዛይን ስራዎች ላይ ማተኮር ይገባል ተብሏል፡፡
በሀገር ውስጥ የሚገዙ ግብዓቶችን መጠቀም እንደሚገባ፣ የምርት ስብጥር እና ሎካላይዜሽን ላይ ትኩረት ማድረግ፣ እንዲሁም የሚመረቱ ምርቶች በጥራት፣በዋጋ እና በማቅረቢያ ጊዜ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በትኩረት ሊሰራ ይገባል፡፡
በመጀመሪው ሩብ አመት ያልተሳኩ ግቦችን በሁለተኛው ግማሽ አመት ላይ የማካካሻ ስራ ሊሰራበት እንደሚገባም አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡ | 783 |
| 14 | https://www.facebook.com/100063763910375/posts/pfbid02ws9yaE5TdU7a3eTnAsKDjKfBdMHhmFtcZTxpnaDCtt4mVsULyNYMMDBnmj3JJ2c1l/ | 1 |
| 15 | ጥቅምት 3/ 2018ዓ/ም (ኢኢግ) በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ።
18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ''ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ'' በሚል መሪ ቃል ነው የተከበረው፡፡
በግሩፑና በኢንዱስትሪዎች የተከበረው የሰንደቅ አላማ ቀን ብሄራዊ ህዝብ መዝሙር በመዘመር፣ እና በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። | 830 |
| 16 | መስከረም 30/2018 ዓ/ም (ኢኢግ)ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ እና ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱን የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ እና የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሄኖክ ከበደ ተፈራርመዋል፡፡
የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ በግሩፕ ስር ለሚገኙ በተለያዩ ዘርፍ ለተሰማሩ ሰባት ኢንዱስትሪዎች ግብአትቶች፣ የማሽኖች እድሳት እንዲሁም ኢንዱስትሪዎችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ከባንኩ የተለያዩ አገልግሎችን ለማግኘት እና በጋራ በመስራት የኢንዱስትሪዎች አቅም ለማሳደግ ስምምነቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሄኖክ ከበደ ከባንኩ ስትራቴጂክ ዕቅዶችን ውስጥ አንዱና ዋናው ጉዳይ ከትላልቅ ተቋማት ጋር አጋርነት በመፍጠር በጋራ መስራት መሆኑንን ገልፀዋል፡፡
በሁለቱ ተቋማት መካከል የተደረገው ስምምነት ወደ ተሻለ ዕድገት ለመሸጋገር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርና በባንኩ በኩል በስምምነቱ ላይ ያሉ ጉዳዮችን ከግብ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በስምምነቱ ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ | 762 |
| 17 | የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ማኔጅመንት በግሩፑ ስር ለሚገኙ እና በመላው ሃገራችን ለሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የደመራ እና የመስቀል በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል፡፡መልካም በአል!! | 1 130 |
| 18 | መስከረም 15/ 2018 ዓ.ም (ኢ.ኢ.ግ) በኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የምርምርና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዘርፍ ስር ከሚገኙ ከግብይትና ሽያጭ የስራ መሪዎችና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
ከዋና መ/ቤት እና ከኢንዱስትሪ የተገኙ የስራ መሪዎችና ባለሙያዎች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
በመድረኩም “ተቋሙ ከእኛ ምን ይጠብቃል? እኛ ከተቋሙ ምን እንጠብቃለን? የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫችን ምን መሆን አለበት?” የሚል የመወያያ ርዕስ እንደ መነሻ በግብይትና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት መምሪያ ኃላፊ በአቶ ታደሰ ጉርሙ ቀርቧል፡፡
የግሩፑ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የምርምርና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዘርፍ ኃላፊ አቡዱልፈታህ ሼህቡሂ (ዶ/ር) ተቋሙ እየተከተለ ያለውን የግብይት አሰራር ስርዓት ላይ እና የደንበኛ አያያዝ አቅጣጫዎች ላይ አጭር ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን የተለያዩ ተቋማትን ልምድና ተሞክሮዎች አካፍለዋል፡፡
በውይይቱ በዚህ በጀት ዓመት በዘርፉ የታቀዱ ግቦች ማሳካት በሚቻልበት መንገድ ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ተግዳሮቶችን በመለየት መፍትሄ ማምጣትና ተቋማዊ ውጤት ለማስመዝገብ ጥረት በሚደረግበት መንገድ ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የግሩፑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮ/ል ሸጋው ሙሉጌታ ባስተላለፉት መልዕክትና የስራ አቅጣጫ በዘርፉ የተሰማራ አመራርና ባለሙያ ተቋማዊ አመለካከት ሊያዳብር ይገባል፡፡
የግሩፑን ሃሳብ በተግባር ለመምራት ተቋሙ በመከተል ላይ ያለውን ስትራቴጂዎችና መመሪያዎችን ጠንቅቆ ማወቅ እና መተግበር እንደሚገባ ገልጸው የደንበኛ እርካታ እንዲረጋገጥ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ | 1 017 |
| 19 | መስከረም 15/ 2018 ዓ.ም (ኢ.ኢ.ግ) በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የኢንትርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ(ኢ.አር.ፒ) ስራ ላይ የቴክኒክ ስልጠና ላጠናቀቁ አመራር እና ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተ፡፡
ግሩፑ ኢ.አር.ፒ ለመተግበር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ሲስተሙን በማበልጸግ ሂደት አስተዋጽኦ እያበረከቱ ለሚገኙ ባለሙያዎች የቴክኒክ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የቴክኒካል ስልጠና እና የሲስተም ተጠቃሚ ስልጠና ለግሩፑ ባለሙያዎች ሰጥቷል፡፡
የቴክኒካል ስልጠና የወሰዱት 29 አመራር እና ሰራተኞች ሲሆኑ 825 አመራርና ባለሙያዎች ደግሞ የሲስተም ተጠቃሚ ስልጠና ወስደዋል፡፡ | 890 |
| 20 | No text... | 1 398 |
