የመዝሙርና ኪነ ጥበባት ሚዲያ ክፍል
Open in Telegram
1 567
Subscribers
-224 hours
+27 days
+630 days
Posts Archive
ወንድማችን እንዲህ አለን!ዛሬ ጧት ከጓደኞቼ ጋር ቤተክርስቲያን ሂደን ስንመለስ ቁርስ እንብላ ብለን ወደ አንድ ካፌ አመራን። ከደረስንም በኋላ ምግብ አዘዝን ምግባችን እስኪደርስ አንዳንድ ወጎዎችን እያዎጋን እያለ ከመሀላችን አንድ ወንድማችን ነገ ግን መዝሙር እናጠናለን አይደል? አለን ። ማለት! የት ነው የምናጠናው ግቢ ጉባዔ እንደሁ ሁሉም ወደ ቤተሰብ እንደሄዱ አልተመለሱም ነው አንተ ያዘጋጀኸው ቦታ አለህ ? ብለን በጥያቄ ስንዘው ። እንዴ! አልሰማችሁም የመስቀል መዝሙር ጥናት እኮ በቴሌግራም ተጀምሯል ብሎ ክው አደረገን እላችኋለሁ! 👉ግን መቼ መቼ እና በየትኛው ግሩፕ ነው ? ብለን ስንጠይቀው በዚህ የፖሊ ግቢ ጉባዔ መዝሙር ጥናት በቴሌግራም በሚለው ነው ፧ እንዲያውም ነገ ሁለተኛ ቀን ነው ብሎ ነገረን ። ከዚያም ያዘዝነው ምግባችን ደረሰልን ምግባችንን ተመግበን ከጨረስን በሗላ ነገ ማታ የመስቀል መዝሙር ልናጠና ተነጋግረን "ሰላመ እግዚአብሔር አይለየህ ፣አይለየን " ተባብለን ተለያየን ። ⏰ሰዓት : - ምሽት 3:00 - 4:15 pm 📲ቦታ:- በOnline Telegram ላይ ኑ ምስጉን እግዚአብሔርን በአንድነት እናመስግን !!! ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
ሰዓታት ቀሩት!
⏰ሰዓት : - ምሽት 3:00 - 4:15 pm
📲ቦታ:- በOnline Telegram ላይ
መዝሙር ለማጥናት ተዘጋጅተናል እያላችሁ በኮሜንት ፃፉልን!!!────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
አይ መታደላችንሰላም ውድ የፖሊ ግቢ ጉባዔ አባላት እንዴት ናችሁ 👋 እነሆ ክረምቱ አልፎ መስከረም ሲመጣ አንድ ነገር ያጓጓናል እርሱም ጌታችን መድሀኒታችን እዮሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ ላይ የተሰቀለበት የመስቀል በዓል ነው ። እርሱንም ምክንያት በማድረግ እናት ግቢ ጉባዔ ለእናንተ በሚመች መልኩ በዓሉን ለማክበር ዝግጅቷን ከዛሬው እንዲሁ ትጀምራለች ።
እንዴት ?➥ለበዓሉ የሚሆኑ መዝሙሮችን በመምረጥ ➥ የመዝሙር ጥናቶችን በ Online በመጀመር እናታችን እንዲህ ከተዘጋጀች እኛ ደግሞ በተባለው ሰዓት እና ቦታ በመገኘት መዝሙሩን እናጥና ፣ እግዚአብሔርን እናመስግን !!! ⏰ሰዓት:- ማታ ከ3:00 እስከ 4:15 pm 📆ቀን:- ማክሰኞ እና እሁድ ከ 26 ጀምሮ ⛪️ቦታ :- በOnline ዜማ ክፍል Channel እርስዎ እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ፣ጓደኛዎን አይርሱ!!👬 ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
አይ መታደላችንሰላም ውድ የፖሊ ግቢ ጉባዔ አባላት እንዴት ናችሁ 👋 እነሆ ክረምቱ አልፎ መስከረም ሲመጣ አንድ ነገር ያጓጓናል እርሱም ጌታችን መድሀኒታችን እዮሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ ላይ የተሰቀለበት የመስቀል በዓል ነው ። እርሱንም ምክንያት በማድረግ እናት ግቢ ጉባዔ ለእናንተ በሚመች መልኩ በዓሉን ለማክበር ዝግጅቷን ከዛሬው እንዲሁ ትጀምራለች ።
እንዴት ?➥ለበዓሉ የሚሆኑ መዝሙሮችን በመምረጥ ➥ የመዝሙር ጥናቶችን በ Online በመጀመር እናታችን እንዲህ ከተዘጋጀች እኛ ደግሞ በተባለው ሰዓት እና ቦታ በመገኘት መዝሙሩን እናጥና ፣ እግዚአብሔርን እናመስግን !!! ⏰ሰዓት:- ማታ ከ3:00 እስከ 4:15 pm 📆ቀን:- ማክሰኞ እና እሁድ ከ 26 ጀምሮ ⛪️ቦታ :- በOnline ዜማ ክፍል Channel እርስዎ እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ፣ጓደኛዎን አይርሱ!!👬 ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
ማኅበረ ቅዱሳን ዜማና ኪነ ጥበባት ማእከል ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት ጋር በመተባበር "ዜማ ወጥበብ" የተሰኘ የስልክ መተግበሪያ አዘጋጀ
መተግበሪያው ማኅበሩ እስካሁን በተለያዩ የሕትመት ውጤቶች ለመላው ዓለም ምእመናን ሲያደርስ የነበረውን የመዝሙርና የኪነ ጥበባት ውጤቶችን በተሻለ ሁኔታ ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን ዜማና ኪነ ጥበባት ማእከል አባላቱን በማስተባበር በ2017 ዓ.ም ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት ጋር በመተባበር ሲሠራ ቆይቶ በመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአገልግሎት ውሏል።
ማእከሉ ይህን የስልክ መተግበሪያ (Mobile Application) በመላው ዓለም የሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን የማኅበሩ መዝሙራዊና ኪነ ጥበባዊ ሥራዎችን ማለትም የማኅበሩን የመዝሙር ጥራዞች፣ በተለያየ ጊዜያት የተዘጋጁ የመዝሙር ካሴቶች፣ የዜማ መሳሪያዎች መዝሙራት፣ የልዩ ልዩ ቋንቋ መዝሙራት፣ የኪነ ጥበብ ሥራዎችና የመዝሙራዊና ኪነ ጥበባዊ ግንዛቤ ማስጨበጫ ማሠልጠኛዎችን የያዘ ሲሆን ከዚህ ወር (መስከረም 2018 ዓ.ም) ጀምሮ ከፕላይ ሰቶር (Play store) ዜማ ወጥበብ ብሎ በመፈለግ ማውረድና መጠቀም ይቻላል።
ለማንኛውም ሐሳብና አስተያየት አፕሊኬሽኑ ላይ በተቀመጠው የአስተያየት መስጫ ወይም በተቀመጡት የኢሜይል አድራሻዎች ማድረስ ይቻላል።
አፕሊኬሽኑን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይችላሉ👇👇👇👇👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eotcmk.zemawetibebzmk
“ወዳጄ ሆይ፥ ተነሺ ውበቴ ሆይ፥ ነዪ”
— መኃልየ. 2፥10
🎊🎉 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የእርገቷ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን🎊🎉
“አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።”
— መዝሙር 132፥8
“ወዳጄ ሆይ፥ ተነሺ ውበቴ ሆይ፥ ነዪ”
— መኃልየ. 2፥10
🎊🎉 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የእርገቷ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን🎊🎉
“አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።”
— መዝሙር 132፥8
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
መስቀል ኃይልነ : መስቀል ጽንዕነ : መስቀል ቤዛነ : መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንዴት ናችሁ ውድ የፖሊ ግቢ ጉባኤ ዜማና ኪነ ጥበባት ክፍል አባላት
የክረምቱ ወቅት እንዴት እያለፈ ነው ?
የመስቀል በዓልን በጊቢ ጉባኤያችን ተገኝተን እንደምናከብር ስንታችሁ መረጃ ኑሯችሁ ይሆን 🤔 ?
በብርሃነ መስቀል የ ክረምቱ ጨለማ አልፎ የተባረከ አመት ከልዑል እግዚአብሔር ይቸረናል !!
እኛም ደግሞ ቸር እግዚአብሔርን
" በመስቀሉ ወበቃሉ አብርሃ ለኩሉ "እያልን እናመሰግነዋለን !! እኛም እንደ ግቢ ጉባኤያችን በደመቀ ሁኔታ በዓሉን እንድናከብር ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የመስቀል በዓል የቴሌ ግራም መዝሙር ጥናት ይኖረናል። በጥናቱ መሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች የሚገኘውን የቴሌ ግራም ግሩፕ በመቀላቀል የጥናት ቀናትን እንድትመርጡ ስንል እናሳስባለን!!! የመስቀል መዝሙር ጥናት ግሩፕ ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
መስቀል ኃይልነ : መስቀል ጽንዕነ : መስቀል ቤዛነ : መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንዴት ናችሁ ውድ የፖሊ ግቢ ጉባኤ ዜማና ኪነ ጥበባት ክፍል አባላት
የክረምቱ ወቅት እንዴት እያለፈ ነው ?
የመስቀል በዓልን በጊቢ ጉባኤያችን ተገኝተን እንደምናከብር ስንታችሁ መረጃ ኑሯችሁ ይሆን 🤔 ?
በብርሃነ መስቀል የ ክረምቱ ጨለማ አልፎ የተባረከ አመት ከልዑል እግዚአብሔር ይቸረናል !!
እኛም ደግሞ ቸር እግዚአብሔርን
" በመስቀሉ ወበቃሉ አብርሃ ለኩሉ "እያልን እናመሰግነዋለን !! እኛም እንደ ግቢ ጉባኤያችን በደመቀ ሁኔታ በዓሉን እንድናከብር ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የመስቀል በዓል የቴሌ ግራም መዝሙር ጥናት ይኖረናል። ስለዚህ ከታች በሚገኘው pole የሚመቻችሁን ቀን እንድታሳውቁን እናሳስባለን !!! ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
💥ደብረ ታቦር💥
"አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ"ማቴ ፲፯፥፬ እንኳን ለታላቁ በዓል ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ!! እነሆ የፖሊ ግቢ ጉባኤ ይህንን ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የደብረ ታቦር በዓል በታላቅ ድምቀት ያከብራል። ስለሆነም ሁላችሁ በግቢያችን እና ባህር ዳር አካባቢ ያላችሁ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በዓሉን አብረን በአንድነት እናክብር ስንል በክርስቶስ ፍቅር ጠርተናችኋል። "ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሁ" መዝ ፹፱፥፲፪ እርስዎ ሲመጡ ፣ ጓደኛዎን ኩሽ ይበሉት : በአንድነት በዓሉን እናክብር !!! ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
ለምን የአብነት ተማሪዎች የደብረታቦር ዕለት ይዘክራሉ ? 🤔
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፯ ከቁጥር ፩-፱ ያለው የእግዚአብሔር ቃል :-
ከስድስት ቀንም በኋላ ÷ ጌታችን ኢየሱስም ጴጥሮስን፣ ያዕቆብን እና ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረዥም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ፊቱም እንደ ፀሓይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እንሆም ሙሴና ኤልያስ ከርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ታዩዋቸው።
ጴጥሮስም መልሶ ጌታችን ኢየሱስን ጌታ ሆይ በዚህ መኾን ለእኛ መልካም ነው ብትወድስ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
እርሱም ገና ይህን ሲናገር እንሆ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው እንሆም ከደመናው ውስጥም ''በርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው ርሱን ስሙት'' የሚል ድምፅ መጣ።
ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር። ጌታችን ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና ተነሡ አትፍሩም አላቸው። ዐይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከጌታችን ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም። በማለት ይነግረናል።
ይህ ዕለት ከተሰዓቱ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን በዚህ ወቅት ለሐዋርያት የክርስቶስ የባህርይ ልጅነት ከባህርይ አባቱ ተገልጧልና፣ እንዲሁም የባህርይ አምላክነቱን በመግለጥ በልባቸው የነበረውን ጥርጣሬ አስወግዶላቸዋልና፣ በተጨማሪም ነገረ ሥጋዌውን እንዲሁም ምስጢረ ሥላሴን ገልጦላቸዋልና።
የአብነት ተማሪዎችም አቤቱ በዚህ ዘመን ላለን ሐዋርያትን በመምሰል አርድዕተ ሊቃውንት ለሆንን ለእኛም ትምህርታችንን ግለጥልን፣ የራቀውን አቅርብልን የቀረበውንም አራቅልን በማለት በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ የደብረታቦር ዕለት ዝክር ይዘክራሉ።
ይህ ዕለትም በፖሊ ግቢ ጉባዔ አብነት ተማሪዎች በደመቀ እና በአማረ መልኩ ይከበራል ።
ለበዓሉ ማዘጋጃ ድጋፍ ለምታደርጉ :-
ንግድ ባንክ :-
1000358173199
ተስፋሁን ገድፍ እሸቴ
እመሰ ረሳይኩኪ ቤተ ጉባዔ ለትርስዓኒ የማንየ ወይጥጋዕ ልሳንየ በጉርዔየ መዝ 136÷8ትርጉም:- የአብነት ቤተ ጉባዔ ሆይ ብረሳሽ ቀኘ ትርሳኝ፣ ባላስብሽም ጉረሮየ ከተናጋየ ትጣበቅ። እርስዎም ድጋፍ በማድረግ ፣ በዕለቱ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ ❗️ ⏰ሰዓት:- ምሽት 11:00 📆ቀን:- ነሃሴ 13/12/2018 ዓ.ም 🏛ቦታ:- አቡዬ ግቢ ጉባዔ አዳራሽ አዘጋጅ :- ፖሊ ግቢ ጉባዔ አብነት ተማሪዎች ────────── ✦ ────────── ፖሊግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ ጾም በሰላም አደረሳችሁ❕
ጾመ ፍልሰታ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅርና በረከት በሁላችንም ላይ የሚፈስስበት፤ በተለይም የሕጻናትን ልብ በቅዱስ ደስታና በየዋህነት የሚሞላ የተቀደሰ ወቅት ነው።
ሕጻናት በነጭ ነጠላ ተሸፋፍነው በጠዋት ወደ ቤተክርስቲያን ሲገሰግሱ፣ ታቦት ሰርተው በደስታ ሲዘምሩና ምጽዋት ሲካፈሉ ማየት የፍልሰታን በረከት ልዩ ያደርገዋል።
እግዚአብሔር አምላክ ጾሙን የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት ያድርግልን፤ የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን❕
++ ኪነጥበብ - መንፈሳዊ መነባንብ !!
(ርዕስ - ግቢ ጉባኤ ትዝ አለኝ)
የፍረሽ ቅበላው ትምህርት መጀመሪያው፡
የከረመው ግቢ አየሩን ስንቀስመው፡
ዌል ካም ሩጫው መልካም ግርግሩ፡
የልዩ ጉባኤው እሑድ መርሃ ግብሩ፡
. . . . . . . ትዝ አለኝ. . . . . . . . .
ነጭ ነጭ ለብሶ ማስታወሻ ይዞ ለጉባኤ መብረር፡
ቀኖናና ዶግማ ሥርዓት ለመማር፡
ደግሞ ተመልሰን ጭምጨማው ችከላው፡
አቤት ተማሪነት ስንቱን አሳለፍነው።
. . . . . . . ትዝ አለኝ. . . . . . . . .
የበዓል ዋዜማው ማኅሌት ቅዳሴው፡
በተማሪ ድባብ ተመስጠን ስንቆመው፡
መዝሙር ምስጋናውን በኅብረት ስናወርድ፡
የበዓል ድግሱን የፍቅሩን ማዕድ፡
ስንጎራረሰው ሁላችን አንድ በአንድ፡
. . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . . . .
መሮጥ ለአገልግሎት ማዘዝ መታዘዙ፡
ንስሐ አባትን ለማግኘት መፍጠኑ፡
ጭቅጭቅ ንትርክ ክርክሩ ቁጣው፡
ያ ሁሉ ለመልካም በኛ ዘንድ የሆነው፡
. . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . .
ለንግስ ተያይዞ ከተማ ማቋረጥ፡
በማታም በሌሊት ዝማሬውን ማቅለጥ፡
ቅዱሳት መካናት አይቶ ለመባረክ፡
ተራራ ቁልቁለት መውጣትና መውረድ በጉልበት
በእንብርክክ፡
መጓዝ በመኪና ወደ ፊት መገስገስ፡
የተቀደሰውን ነክቶ ለመቀደስ፡
. . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . . .
ሱባኤና የሰርክ ማኅበር ፀሎቱ፡
ደካማው በብርቱ ሲታገዝ ማየቱ፡
ኧረ እንዴት ደስ ይላል ያ ሁሉ ትጋቱ።
. . . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . .
የህይወት ውይይት በክፍል በክፍል፡
ዛሬ ምን አደረግህ አንችስ ምን አገኘሽ ስንል ስንባባል፡
በጠዋት በማታ ተቀሳቅሶ መሄድ ለህይወት መታገል፡
አቤት መጣፈጡ እንዴት ነፍስ ይገዛል፡
የአንዱን ሸክም ሌላው ሲሸከም ደስ ይላል።
. . . . . . . . ትዝ አለኝ. . . . . . . .
ከምሥራቅ ከምዕራብ ከሰሜን ከደቡብ፡
የመጣነው ሁሉ ለየራሳችን ግብ፡
መስርተን ተገኝተን ጠንካራ ቤተሰብ፡
በማትናወጠው በስላሴ ወደብ፡
ስንሄድ ስንመጣ ሲያየን ጎረቤቱ ይሉ ነበር አጀብ።
. . . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . . . .
ገናና ፋሲካ በዓሉ ሲመጣ፡
ሽር ጉድ ስንል ስንገባ ስንወጣ፡
አምናና ታች አምና እዚህ የነበረ ወንድማችን መጣ፡
ብለን በደስታ አቅላችን ስናጣ፡
ሲገኝ ፍሪዳውን ዳቦውን ሲታጣ፡
ለማቅረብ ስንኳትን በቀንና ሌሊት፡
ውሃውን ስንቀዳ ሊጡን ስናቦካ ሲያምርብን የዛንለት፡
እሳቱ ሲገርፈን ጭቃውም ሲነካን፡
ፍፁም ደስ ይለናል ከሌሎች ጋር ሆነን።
. . . . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . . .
የግንቦት ልደታ በእንግዶች ታጅበን፡
በጧፍ መብራት ደምቀን በዜማ ረስርሰን፡
ስናከብር ማርያምን እማሆይ ጋር ሆነን፡
. . . . . . . ትዝ አለኝ. . . . . . . .
አብሮን የቆየውን ቅድመ አባታችን ቅድመ አያታችን፡
ሲሄድ ሸኝተነው ስትሄድ ሸኝተናት በእንባችን ተራጭተን፡
እኛም ተቀብለን አዲሱን ቤተሰብ በደንብ አቋቁመን፡
ደግሞ ደረሰና እኛም ተሸኝተን ቃል ኪዳኑን ይዘን
መስቀሉን
አጥልቀን፡
ኢየሩሳሌም ሆይ፡ ግቢ ጉባኤ ሆይ አልረሳሽም ብለን፡
ዘምረን ተጫውተን የልብ የልባችን፡
ምከረኝ ምከሪኝ ምን ላድርግ እንግዲህ እንዲያ ተባብለን፡
. . . . . . . ትዝ አለኝ. . . . . . . . . .
ግቢውን አቋርጠን እስራኤልን መስለን፡
ከበሮ እየመታን ነጋሪት ጎስመን መለከቱን ነፍተን፡
ስንጓዝ በአንድ ላይ እግዚአብሔርን ይዘን ማደሪያውን
ይዘን፡
ባህረ ጥምቀቱ እንዴት ይረሳኛል፡
ጉባኤው ዝማሬው ልቤን ይንጠኛል።
. . . . . . . ትዝ አለኝ . . . . . .
ብቻ ሁሉም ነገር እዛ የነበረው፡
ትዝ አለኝ በድንገት ልቤን በረበረው፡
እናቴ ግቢ ጉባኤ በዚሁ እንደምን ነሽ?
ይችን ስዕለት ስሚኝ በለመደ ግብርሽ፡
ፍቅርሽ አነሳስቶ ያብረኝ ያክንፈኝ አንዴ ዳግም ልይሽ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን !!
ንዒ ሀቤነ
ንዒ ሀቤነ ኦ ድንግል
ምስለ ወልድኪ መድኃኒነ
ከመ ትባርኪ ላዕሌነ
ነይ ከአምላክሽ ጋር ከልጅሽ
ይቅር እንዲለን በምልጃሽ
ንዒ ድንግል(፪)ከልጅሽ ከአማኑኤል
አዝ = = = = = =
የሐና የኢያቄም መልካም ተክል
የሐዋርያት ስብከት የሰማዕታት አክሊል
ነይ ድንግል(፪)ነይልን ፈጥነሽ ድንግል
አዝ = = = = = =
አሕዛብ ነገሥታት ይገዙልሻል
የናቁሽም ሁሉ ይሰግዱልሻል
የእግዚአብሔር ከተማ (፪)ድንግል ሆይ ፅዮን ይሉሻል
አዝ = = = = = =
በጥልቅ ማዕበል ሳለን
በኃጢአት ወጥመድ ተይዘን
ድረሽልን(፪)ከልጅሽ አንቺ አማልጅን
💐🌹🌹🌹🌹ውድ የ2018 ዓ ም ተመራቂ እህት ወንድሞቼ እንኳን ለዚች በጉጉት ስትጠብቋትና ስትናፍቋት ለነበረችው ቀን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🌹🌹🌹🌹💐
🌹🌹🌹🌹🌹 🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹 🌹🌹
🌹🌹 እንኳን ደስ አላችሁ 🌹🌹
🌹🌹 🌹🌹
🌹🌹🌹🌹 🌹🌹🌹🌹🌹🌹
“ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።” — ዮሐንስ 1፥3✨ነገ እሁድ እንደሚታወቀው በቤተ ክርስቲያን ደግሞ ምርቃት ይኖረናል ፤ በዚህም ዕለት ስንዘጋጅ የነበረውን ወረብ ስለምናቀርብ መርሃ ግብሩ 2፡00 ስለሚጀመር እኛ ቀድመን አንድ ጊዜ ማየት ስላለብን በተባለው ሰዓት ወረቡን የምናውቅ በሙሉ እንድንገኝ ይሁን ።✨ ሰዓት፡ ጠዋት 1፡00 ቦታ፡ ፔዳ ቅድስት ሥላሴ አዳራሽ 👉ለበለጠ መረጃ በ0952757862 ይደውሉ ──────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ
