Ethio telecom Family
Open in Telegram
6 046
Subscribers
-324 hours
-17 days
-2430 days
Posts Archive
6 045
የኤክስክዩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርዱ_ለስትራቴጂው_ሁለተኛ_ዓመት_ስኬት_የአገልግሎት_ጥራት_ማሻሻያ_አቅጣጫዎችን.pdf3.38 MB
6 045
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond
6 045
+6
ኩባንያችን የኢትዮጵያን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በግንባር ቀደምትነት እየመራ፣ ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ሁለንተናዊ እድገት የሚያደርገውን የማይተካ አገራዊ አስተዋፅኦ በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 73.5 ቢሊዮን ብር ታክስ ገቢ በማድረግ የሀገር ግንባታ ምሰሶነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ይህም ተቋማችን ያስገባቸውን አጠቃላይ የታክስ መጠን ወደ 244.5 ቢሊዮን ብር አድርሶታል። ኩባንያችን ከዚህ ቀደምም ለተከታታይ አምስት ዓመታት የሀገራችን ግንባር ቀደም የ"ፕላቲኒየም ግብር ከፋይና ልዩ" ሽልማት ባለቤት መሆኑ ይታወሳል።
ከቀዳሚ ግብር ከፋይነቱ በተጨማሪ፣ ተቋማችን ከውድ ደንበኞቹ ጋር በመተባበር 2.4 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ አደጋ ማገገሚያ ፈንድ በማሰባሰብ፣ በችግር ጊዜ ለወገን አለኝታነቱን በተግባር ዳግመኛ አስመስክሯል፤ ለ44,757 ዜጎች ቀጥተኛ የቋሚና የኮንትራት ሥራ ዕድል በመፍጠር ዜጎችን ኑሮ መደገፍ ችሏል።
ከዚህም ባለፈ ኩባንያችን 519,810 የምርትና አገልግሎት አከፋፋዮችንና የቴሌብር ወኪሎችን፣ 2,205 የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን፣ 1,213 የተጨማሪ እሴት አገልግሎት (VAS) አጋሮችን፣ 138 የፍራንቻይዝ አጋሮችን እና 693 ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማቀፍ ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ግዙፍ የኢኮኖሚ ሥነ-ምህዳር መገንባት ችሏል።
ኩባንያችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፈጠራን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር በማቀናጀት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ የማፋጠን፣ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የቀዳሚ ግብር ከፋይነት አገራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ለተጨማሪ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
6 045
+7
ቴሌብር የገንዘብ ዝውውርን ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ ለአካታችና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
በ"ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታልና ከዚያም ባሻገር 2028" ስትራቴጂ የመጀመሪያ ዓመት በሆነው በ2018 በጀት ዓመት፤ ቴሌብር 2.61 ቢሊዮን ግብይቶችን በማስተናገድ በጠንካራ የዕድገት ጉዞ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የግብይት የገንዘብ መጠኑንም 4.19 ትሪሊዮን ብር ማድረስ ተችሏል፡፡
በተጨማሪም 8.54 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት፣ አጠቃላይ የቴሌብር ደንበኞችን ቁጥር 60.6 ሚሊዮን በማድረስ የዕቅዳችንን 96.9% አሳክተናል።
ኩባንያችን ከዳሸን ባንክ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከሲንቄ ባንክ እና ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር በቴሌብር እያቀረበ በሚገኘው የማይክሮ ብድር፣ የማይክሮ ቁጠባ እና ኦቨር ድራፍት አገልግሎቶች ለ5.65 ሚሊዮን ደንበኞች 19.51 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት የሰጠ ሲሆን፣ 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ 18.75 ቢሊዮን ብር ቆጥበዋል፡፡
በአጠቃላይ ከ33 ባንኮች ጋር ከመተሳሰር ባለፈ፣ 410.7 ሺህ ወኪሎች እና 440.1 ሺህ ነጋዴዎች የቴሌብር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ይህም በዲጂታል ሥነ-ምህዳሩ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥሯል፡፡
የዲጂታል ግብይት ሥነ-ምህዳር ፈርቀዳጅ የሆነው ዘመን ገበያ (ኢ-ኮሜርስ) በበጀት ዓመቱ ከ2.4 ሚሊዮን በላይ ጉብኝቶችን መሳብ የቻለ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የተመዘገቡ ነጋዴዎች (Merchants) ቁጥር 739 ደርሷል፡፡ በዚህም ከ58.3 ሺህ በላይ ደንበኞች 72.1 ሺህ ግብይቶችን የፈጸሙ ሲሆን፣ በድምሩ ከ377.9 ሚሊዮን ብር በላይ የዕቃዎች ሽያጭ ተከናውኗል፡፡
በቴሌብር የስኬት ጉዞ አብሮነታችሁ ስላልተለየን ከልብ እናመሰግናለን!
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
6 045
ቴሌብር የገንዘብ ዝውውርን ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ ለአካታችና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
በ"ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታልና ከዚያም ባሻገር 2028" ስትራቴጂ የመጀመሪያ ዓመት በሆነው በ2018 በጀት ዓመት፤ ቴሌብር 2.61 ቢሊዮን ግብይቶችን በማስተናገድ በጠንካራ የዕድገት ጉዞ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የግብይት የገንዘብ መጠኑንም 4.19 ትሪሊዮን ብር ማድረስ ተችሏል፡፡
በተጨማሪም 8.54 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት፣ አጠቃላይ የቴሌብር ደንበኞችን ቁጥር 60.6 ሚሊዮን በማድረስ የዕቅዳችንን 96.9% አሳክተናል።
ኩባንያችን ከዳሸን ባንክ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከሲንቄ ባንክ እና ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር በቴሌብር እያቀረበ በሚገኘው የማይክሮ ብድር፣ የማይክሮ ቁጠባ እና ኦቨር ድራፍት አገልግሎቶች ለ5.65 ሚሊዮን ደንበኞች 19.51 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት የሰጠ ሲሆን፣ 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ 18.75 ቢሊዮን ብር ቆጥበዋል፡፡
በአጠቃላይ ከ33 ባንኮች ጋር ከመተሳሰር ባለፈ፣ 410.7 ሺህ ወኪሎች እና 440.1 ሺህ ነጋዴዎች የቴሌብር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ይህም በዲጂታል ሥነ-ምህዳሩ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥሯል፡፡
የዲጂታል ግብይት ሥነ-ምህዳር ፈርቀዳጅ የሆነው ዘመን ገበያ (ኢ-ኮሜርስ) በበጀት ዓመቱ ከ2.4 ሚሊዮን በላይ ጉብኝቶችን መሳብ የቻለ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የተመዘገቡ ነጋዴዎች (Merchants) ቁጥር 739 ደርሷል፡፡ በዚህም ከ58.3 ሺህ በላይ ደንበኞች 72.1 ሺህ ግብይቶችን የፈጸሙ ሲሆን፣ በድምሩ ከ377.9 ሚሊዮን ብር በላይ የዕቃዎች ሽያጭ ተከናውኗል፡፡
በቴሌብር የስኬት ጉዞ አብሮነታችሁ ስላልተለየን ከልብ እናመሰግናለን!
ለበለጠ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
6 045
+9
ኩባንያችን የ2018 በጀት ዓመት እና የቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታል እና ከዚያም ባሻገር 2028 ስትራቴጂ የመጀመሪያ ዓመት እቅዱን በላቀ ስኬት ማጠናቀቁን በታላቅ ደስታ እናበስራለን!
በበጀት ዓመቱ 264 ተጨማሪ ከተሞች የ4ጂ LTE አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የቻሉ ሲሆን፤ አጠቃላይ የ4ጂ ተጠቃሚ ከተሞች ቁጥር 1,200 ማድረስ ተችሏል፡፡ በሰባት ከተሞች የ5ጂ ተጨማሪ ማስፋፊያዎችን በማከናወን በአጠቃላይ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ከተሞችን ቁጥር ወደ 33 ከፍ ማድረግ ተችሏል፡፡
ኩባንያችን አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎቻችንን ቁጥር 90.12 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተያዘውን ግብ 101.7% በማሳካት ከአቅድ በላይ ስኬታማ አድርጎናል።
በተጨማሪም 475 አዳዲስ እና የተሻሻሉ ምርቶችና አገልግሎቶች ለግል ደንበኞች፣ ኢንተርፕራይዝ፣ ፊንቴክ፣ ዲጂታል ላይፍስታይል እንዲሁም በአለም አቀፍ የቢዝነስ ዘርፎች ላይ ለገበያ ማቅረብ ተችሏል፡፡
ዓመታዊ ገቢውን ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ33.2% ማሳደግ የቻለ ሲሆን፣ 215.82 ቢሊዮን ብር በማግኘትም የያዘውን ዕቅድ 99.7% ስኬታማ አድርጓል።
ለዚህ የገቢ ስኬት የዳታና ኢንተርኔት አገልግሎት በ31.1% እንዲሁም የሞባይል ድምፅ አገልግሎት በ23.5% ድርሻ ከፍተኛውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ ደንበኞቻችን፣ የሥራ አጋሮቻችንና ሚዲያዎች በስኬታችን ጉዞ አብሮነታችሁ ስላልተለየን ከልብ እናመሰግናለን!
ለተጨማሪ፡ https://bit.ly/45k6Gjw
6 045
· የኩባንያችን 2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀጥታ ስርጭት!
· የቀጥታ ስርጭቱን ለመከታተል:
https://web.facebook.com/ethiotelecom/live_videos
6 045
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ! #Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #LinkeInLearning #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond
6 045
+9
🏃♀️🏃♂️ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫ በሐረር በድምቀት ተካሔደ!!
መነሻና መድረሻውን ሐረር በር ላይ በማድረግ ፕሮፌሽናል አትሌቶችና ከአዲስ አባባ ተጓዥ ተሳታፊዎችን ያካተተ ልዩ የ10ኪ.ሜ ውድድር በወንዶችና በሴቶች ደስ በሚል ድባብ ተካሒዷል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ከ16 ዓመት በታች ታዳጊ አትሌቶች የተሳተፉበት የ1.5 ኪ.ሜ ውድድርና ከ11 ዓመት በታች ልጆች የተሳተፉበት የ1 ኪ.ሜ.ውድድር ሌላው የዕለቱ ድምቀት ነበር፡፡
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በስያሜና የቴክኖሎጂ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#EthiotelecomGreatHararRun #GreatEthiopianRun #Harar #telebirr #Ethiotelecom
6 045
+8
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ ከኢንስፐር (Inspur) እና ከሻንዶንግ ሃይ-ስፒድ (SDHS) ከፍተኛ አመራሮች ጋር ስትራቴጂያዊ ውይይት አካሄዱ
ውይይቱ በተቋማቱ መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር፤ የቀጣዩ ትውልድ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ከዘመናዊ መሠረተ ልማት ግንባታ ጋር ለማቀናጀት ያለመ ነው፡፡
ይህም የኩባንያችንን “ቀጣዩ አድማስ” ስትራቴጂ መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ የሀገራችንን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠንና ለመጪው ጊዜ ዝግጁ የሆነ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር ያስችላል፡፡
በውይይቱ የላቁ የኮምፒውቲንግ አቅሞች፣ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የዳታ ማዕከል መፍትሔዎችና የክላውድ ፕላትፎርሞችን በመዘርጋት ሀገራዊ የዲጂታል ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ የዲጂታል መተግበሪያዎችን በጋራ ለማልማት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በምርምር ለመሥራት እንዲሁም አህጉራዊ ተደራሽነትን በማስፋት ለዲጂታል አፍሪካ ግንባታ አስተዋፅዖ ለማበርከት ተወያይተዋል፡፡
የኢንስፐር እና የሻንዶንግ አመራሮች የኩባንያችንን አስደማሚ የትራንስፎርሜሽን ጉዞና የቴክኖሎጂ መሪነት በማድነቅ፤ በአፍሪካ ገበያ የሚታዩ ስትራቴጂያዊ ዕድሎችን በጋራ ለመጠቀም ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ገልጸዋል፡፡
ውይይቱ እነዚህን ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ወደ ተግባር የሚለውጥ የትግበራ ፍኖተ-ካርታ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲዘጋጅ በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን አቅጣጫ ተሰጥቶ ተጠናቅቋል፡፡
6 045
+8
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሁዋዌ ሰሜን አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሚስተር ሊ ሸን የኢንተርፕራይዞችንና የአነስተኛና መካከለኛ ቢዝነሶችን ዕድገት በዲጂታል ለማፋጠን የሚያስችል ውይይት አካሂደዋል።
ውይይቱ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር የንግድና የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው።
ይህም የኩባንያችንን “ቀጣዩ አድማስ” ስትራቴጂ መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ ለንግድ ተቋማትና ለማኅበረሰቡ ዘላቂ እሴት የሚፈጥር የተቀናጀ የዲጂታል መፍትሔዎችን በጋራ እውን ለማድረግ የሚያስችል ነው።
በውይይቱ ክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና ሳይበር ደህንነትን ከቴሌብር ጋር በማቀናጀት ለኢንተርፕራይዞች ምርታማነትንና ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ የዲጂታል የክፍያና የሥራ አመራር ሥርዓቶችን ለማቅረብ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በተጨማሪም በዲቫይስ ፋይናንስ አማራጮች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን ስማርት ስልኮችና የዲጂታል መሣሪያዎችን በሰፊው ተደራሽ በማድረግ የዲጂታል አካታችነትን ለማፋጠን ተወያይተዋል።
ሁዋዌ ኩባንያ ኢትዮ ቴሌኮም ወደ ቴክኖሎጂ ተቋም (TechCo) ለመለወጥ ለሚያደርገው ጉዞ ያለውን ድጋፍ አረጋግጦ፣ በቀጣይም ዲጂታል ፈጠራን ወደ አፍሪካ ገበያ ለማስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
ውይይቱ እነዚህን ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ወደ ተጨባጭ ተግባራት በመለወጥ ለኢንተርፕራይዞች አዳዲስ ዕድሎችን ለመፍጠር በሚያስችል ስምምነት ተጠናቋል።
6 045
Repost from Ethio telecom
+8
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሁዋዌ ሰሜን አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሚስተር ሊ ሸን የኢንተርፕራይዞችንና የአነስተኛና መካከለኛ ቢዝነሶችን ዕድገት በዲጂታል ለማፋጠን የሚያስችል ውይይት አካሂደዋል።
ውይይቱ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር የንግድና የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው።
ይህም የኩባንያችንን “ቀጣዩ አድማስ” ስትራቴጂ መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ ለንግድ ተቋማትና ለማኅበረሰቡ ዘላቂ እሴት የሚፈጥር የተቀናጀ የዲጂታል መፍትሔዎችን በጋራ እውን ለማድረግ የሚያስችል ነው።
በውይይቱ ክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና ሳይበር ደህንነትን ከቴሌብር ጋር በማቀናጀት ለኢንተርፕራይዞች ምርታማነትንና ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ የዲጂታል የክፍያና የሥራ አመራር ሥርዓቶችን ለማቅረብ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በተጨማሪም በዲቫይስ ፋይናንስ አማራጮች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን ስማርት ስልኮችና የዲጂታል መሣሪያዎችን በሰፊው ተደራሽ በማድረግ የዲጂታል አካታችነትን ለማፋጠን ተወያይተዋል።
ሁዋዌ ኩባንያ ኢትዮ ቴሌኮም ወደ ቴክኖሎጂ ተቋም (TechCo) ለመለወጥ ለሚያደርገው ጉዞ ያለውን ድጋፍ አረጋግጦ፣ በቀጣይም ዲጂታል ፈጠራን ወደ አፍሪካ ገበያ ለማስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
ውይይቱ እነዚህን ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ወደ ተጨባጭ ተግባራት በመለወጥ ለኢንተርፕራይዞች አዳዲስ ዕድሎችን ለመፍጠር በሚያስችል ስምምነት ተጠናቋል።
