ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
Open in Telegram
ይህ የታሪካዊ ፎቶዎች ኦፊሻል ቻናል ነው ታሪክን መዘከር ትልቅነት ነው ትውልድንም ያንፃል ‼️ Officeal channel 📡 》t.me/ @Tarikawi_potowech https://t.me/+3SO18mqWX_tiOWE0 #የጦር_ሜዳ_ውሎ https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ 👉 ለአስተያየትዎ @Eyoha_Bot
Show more735
Subscribers
+124 hours
-17 days
+3530 days
Posts Archive
ጎጃምና ጎንደር - 1964 ዓ.ም
Global Semester Archive:
http://geneastey.com/global/page4/page4.html
@Tarikawi_fotowech
ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን 1884 ዓ.ም ከራስ መኮንን ወልደሚካኤልና ከወ/ሮ የሺእመቤት ዓሊ ጋምቾ ከሐረር ከተማ
30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኤጀርሳ ጎሮ በተባለች ቦታ ልጅ ተፈሪ ተወለዱ፡፡
@tarikawi_fotowech
ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ክብር በኋይት ሀውስ የተዘጋጀ ግብዣ - ከ1955 እስከ 1959 ዓ.ም ድረስ የተነሱ ፎቶግራፎች
Related White House Pictures of Emperor Haile Selassie & US President Lyndon B. Johnson taken
between 1963 & 1967 G.C
Lyndon B. Johnson Presidential Library & Museum:
https://www.lbjlibrary.org
https://www.gettyimages.com
@tarikawi_fotowech
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️
የጎንደሩ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴ በወለጋው አምባሳደር አማኑኤል አብርሃም አይን፣
A 19th Century Victorian Gentleman, and Ethiopian Nationalist – Dr Charles Martin
“ትውልዱ ከዚህ አውራጃ ነው ከዚያ ሳይሉ፣ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ይሰጡት የነበረው ርዳታና ድጋፍ እንዲሁም ያሳዩ የነበረው የእውነተኛ ኢትዮጵያዊነት አርአያነት እስከ ዘመኔ መጨረሻ በልቤ ውስጥ ይኖራል”
አዛዥ ወርቅነህ የተወለዱት በ1857 ዓ.ም ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ነው፡፡ በ1860 ዓ.ም እንግሊዞች ከአጼ ቴዎድሮስ ጋር መቅደላ ላይ በተዋጉበት ጊዜ፣ ኮሎኔል ቻምበርሊን የተባለ የእንግሊዝ መኮንን የ3 አመቱን ልጅ ወርቅነህን ብቻቸውን በአምባው ላይ አግኝቶ ወደ ህንድ ወሰዳቸው፡፡ ኮሎኔሉ ብዙም ሳይቆይ በመሞቱ፣ ኮሎኔል ማርቲን የሚባል ጓደኛው
ወርቅነህን ወስዶ በት/ት አሳደጋቸው፣ ክርስትና አስነስቶም ቻርልስ ማርቲን አላቸው፡፡
አዛዥ ወርቅነህን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቅኳቸው የተፈሪ መኮንን ት/ቤትን በአዳሪነት ስቀላቀል በ1918 ዓ.ም ነው፡፡ በአዲስ አበባ ስራ የማግኘት ተስፋ እንደሌለኝ ከተረዳሁ በኋላ፣ የቀድሞ ት/ቤቴ የተፈሪ መኮንን አስተዳዳሪ ለነበሩትና በጊዜው የሐረርጌ ጨርጨር አውራጃ አበጋዝ ሆነው ሲያገለግሉ ለነበሩት አዛዥ ወርቅነህ በደብዳቤ ስራ እንዲሰጡኝ ለመጠየቅ ወሰንኩ፡፡
ጓደኛዬ የቄስ ባድማ ልጅ ጳውሎስ ከአባቱ የቴምብር መግዣ ሲያመጣ፣ እኔ ደግሞ በ2ታችን ስም በእንግሊዝኛ ደብዳቤ በመጻፍ ለአዛዥ ወርቅነህ ላኩላቸው፡፡ አዛዥ ወርቅነህ በቀድሞ ተማሪዎቻቸው መንገላታት አዝነው ለሁለታችንም ስራ ሊሰጡን ወስነው፣ በጨርጨር የንግድ ሹም የነበሩት ልጅ ክፍሌ ዳዲ ሁለታችንንም ከአዲስ አበባ ይዘው እንዲመጡ አዘዟቸው፡፡
ይሁን እንጂ ጓደኛዬ ጳውሎስን መልእክተኛው አአ ከመድረሳቸው በፊት ራስ ኃይሉ ተ/ኃይማኖት ለት/ት ወደ ቤይሩት ስለላኩት፣ እኔ ጥቅምት 21 ቀን 1924 ዓ.ም ከአአ በባቡር ተሳፍሬ በማግስቱ አሰበ ተፈሪ ገባሁና ጥቅምት 23 ቀን 1924 ዓ.ም ከአዛዥ
ወርቅነህ ጋር ተገናኘሁ፡፡ ከዚህ በኋላ አዛዥ ወርቅነህ ከቤታቸው ጀርባ አራት ክፍል ያሉት ት/ቤት በማሰራት እንዲሁም ዴስክ፣ ሰሌዳና ነጭ በሃ ድንጋይ/
ጠመኔ ከአአ አምጥተው በማሟላት ህዳር 21 ቀን 1924 ዓ.ም ት/ቤቱ ተከፈተ፡፡ ተማሪዎች እየበዙ ሲመጡ ሌሎች 7 አስተማሪዎች ተቀጠሩ፡፡ ሐኪም ወርቅነህ የመማሪያ መጽሀፍት፣ ደብተር፣ ወረቀት፣ እርሳስ፣ ቀለምና ብእር እንዲገዛ ያቀረብኩትን ጥያቄ በመቀበል እነዚሁ እቃዎች በቀጥታ ከለንደን እንዲመጡ በደብዳቤ አዘዙ፣ ገንዘቡንም በለንደን ከነበራቸው የባንክ ሂሳብ
እራሳቸው በግል በመክፈል የት/ሚኒስቴርን ቢሮክራሲ አስቀሩልኝ፡፡
በዚህ ሁኔታ ከአዛዥ ወርቅነህ ጋር እየኖርኩ በሳቸው ጸሃፊነት፣ በአስተማሪነትና በት/ቤት አስተዳዳሪነት ለ3 አመት ያህል ከሰራሁ በኋላ በ1927 ዓ.ም ወደ ውጭ አገር የሚያስኬድ እድል አገኘሁ፡፡ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ለመውረር በምትዘጋጅበት ጊዜ ቀዳማዊ
ኃይለ ሥላሴ ሐኪም ወርቅነህን በእንግሊዝ ባለሙሉ ስልጣን ሚኒስትር አድርገው ሾሟቸው፡፡ ብዙ ሰዎች በረዳትነት ይዘዋቸው እንዲሄዱ አዛዠ ወርቅነህን ቢጠይውቋቸውም፣ እሳቸው ግን የመረጥኩት ልጅ ስላለ አይሆንም ብለው መለሷቸው፡፡
ሰኔ 16 ቀን 1927 ዓ.ም በባቡር ተሳፍረን ወደ ጅቡቲ ሄድን፡፡ ከጅቡቲ በመርከብ በስዊስ ካናልና በፖርት ሳይድ አድርገን ሜዲትራንያንን እያቋረጥን እስከ ማርሴይ ወደብ ተጓዝን፡፡ በመጨረሻም በባቡር ከማርሴይ ወደ ፓሪስ፣ ከፓሪስ ወደ ሎንደን በመጓዝ ሰኔ 29 ቀን 1927 ኣ.ም ሎንዶን ከተማ ገባን፡፡ ሎንዶን ከመድረሳችን በፊትም ፓሪስ ላይ የኢትዮጵያውን ሚ/ር በጅሮንድ ተክለ ሐዋርያትን አገኘናቸው፡፡ እኔም ከ1927 -1931 ዓ.ም ድረስ በሎንዶን የኢትዮጵያ ሌጋሲዮን ጸሀፊ ሆኜ አገለገልኩ፡፡
ክቡር አዛዥ ወርቅነህ እሸቴ አገሬንና ወገኔን ለማገልገል እድል ካገኘሁበት ጊዜ ጀምሮ ለረጅም ዘመን ስራዬን እንደ ፋና እንድመራ የረዱኝ መሆኑን ይህንን ጽሁፍ ለሚነቡ ሁሉ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ ትውልዱ ከዚህ አውራጃ ነው ከዚያ እያሉ ሳይለያዩ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ይሰጡት የነበረው ርዳታና ድጋፍ እንዲሁም ያሳዩ የነበረውን የእውነተኛ ኢትዮጵያዊነት አርአያም እስከ ዘመኔ
መጨረሻ በልቤ ውስጥ ይኖራል፡፡
የሕይወቴ ታሪክ፣ አማኑኤል አብርሃም፣ አአዩ ፕሬስ፣ ገጽ 11-23 የፎቶ መግለጫ፣ የመጀመሪያውን ፎቶግራፍ ሐኪም ወርቅነህ የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት በነበረችው ህንድ በ1865 ዓ.ም እንደተነሱ ይታመናል፡፡ 2ኛውን ፎቶ ሐኪም ወርቅነህ በእንግለዝ የኢትዮጵያ ሚ/ር በነበሩበት ጊዜ በ1928/1929 ዓ.ም በሎንዶን የተነሱት
እንደሆነ ይታመናል፡፡ ተጨማሪ ማስታወሻ፣ ሐኪም ወርቅነህ ከ1875 ዓ.ም ጀምሮ ዘመናዊ የሕክምናና የሰርጀሪ ት/ት በመማር ከ135 አመት በፊት
የእንግሊዝ ኮሎኒ በነበሩት በርማና ህንድ የእንግሊዝን መንግስት ያገለገሉ፣ ከአድዋ ጦርነት ማግስት ጀምሮ በውስጣቸው ሆኖ ያሸነፋቸውን የኢትዮጵያ ናፍቆት በመጨረሻ ከምኒልክ ጋር በመገናኘት እውን ያደረጉ፣ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ድረስ
አገራቸውን ያገለገሉና እውነተኛ የአገር ፍቅር እንደነበራቸው ሌሎችም መስክረዋል፡፡
ከነዚህም አንዱ "Victorian Gentleman and Ethiopian Nationalist: The Life and Times of Hakim Wärqenäh, Dr Charles Martin" በሚል ርእስ በ Peter P. Garretson የተጻፈው በሀኪም ወርቅነህ የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው መጽሀፍ እንደሆነ በመግለጽ የበለጠ ለማወቅ የሚፈልጉ ሁሉ ይህንኑ እንዲያነቡ አንዳንዶች መክረዋል፡፡
@Tarikawi_fotowech
የጎንደሩ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴ በወለጋው አምባሳደር አማኑኤል አብርሃም አይን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@Tarikawi_fotowech
@Tarikawi_fotowech
Ethiopia back in the 1970s/1980s G.C
ኢትዮጵያ - 1970ዎቹ
The source World Bank Photo Library doesn't provide details of the photographs
Images possibly taken in 1975 or during the adult literacy campaign of the 1970s & 1980s in relation to the subjects of agriculture,
education, water supply and rural development
World Bank Photo Library/Ray Witlin Photographs:
http://secure.worldbank.org/photolibrary/
@Tarikawi_fotowech
ንጉሠ ነገሥት ግርማዊ ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ በሀገረ በኬንያ በነበራቸው የጉብኝት መርሀግብር በወቅቱ ከኬንያ ፕሬዝዳንት ጆሞ ኬንያታ ጋር እንዲሁም
የሁለቱም አገራት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት የሁለትዮሽ የድንበር ስምምነት ሲፈራረሙ ፤
ኬንያ - ሞምባሳ ስቴት ሃውስ ሠኔ/1962 ዓ.ም
@Tarikawi_fotowech
አጂፕ ነዳጅ ማደያና የልዑል መኮንን መታሰቢያ ቡና ቤት በባኮ '- መስከረም 1966 ዓ.ም
Eva Crane Trust Photographs/Ethiopia Gallery:
https://www.evacranetrust.org/gallery/ethiopia
@tarikawi_fotowech
አዲስ አበባ - 1968 ዓ.ም
Beautiful pictures you may have never seen before
Copyright: Nick Dewolf Foundation:
https://www.flickr.com/photos/dboo/albums/
@tarikawi_fotowech
የምስራቅ ጀርመን ሀኪሞች በጎንደር የጤና ሳይንስ ኮሌጅ - ከ1971 - 1976 ዓ.ም ድረስ
MDR ZEIT REISE/Plötzlich im Krieg: DDR-Ärzte für Äthiopien
https://www.mdr.de/zeitreise/ddr-aerzte-in-afrika-sozialistische-entwicklungshilfe-100.html
@tarikawi_fotowech
አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ - 1961/1962 ዓ.ም
Madelyn Duffey Ethiopia travel Photographs/Schodts Flicker Archive:
https://www.flickr.com/photos/schodts/albums/72057594055368414
@tarikawi_fotowech
እድለኛው ህፃን ሳሙኤል በላይ ፤
በ 1963 ዓ.ም አቶ በላይ የተባሉ ግለሰብ በአንድ ብር በልጃቸው ሳሙኤል ስም የቆረጡት 97ኛውን መደበኛ ሎተሪ ዕጣ ዕድል ቀንቷቸው በ 2ኛ ዕጣ 3000 ብር ዕድለኛ ሆኑ፡፡ ከታች በምስሉ ላይ የ 2 ዓመት ከ8 ወራት ዕድሜ ያለው ህፃን ሳሙኤል በላይ ከብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር የሽልማት ገንዘቡን (ሶስት ሺህ) ብር ሲረከብ ይታያል።
@tarikawi_fotowech
የሳውዲው ንጉስ ሳኡድ ቢን አብዱልአዚዝ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴን በሪያድ ናሲሪያ ቤተመንግስት
ተቀብለው ባነጋገሯቸው ወቅት ፤ (በ 1952 ዓ.ም)
@tarikawi_fotowech
King Sahle Selassie of Shewa in triumphal costume in/before 1845 G.C
The New York Public Library- Digital Collections
http://digitalcollections.nypl.org
ከግራ ወደ ቀኝ) በሀገረ አሜሪካ
👉 ሠዓሊ፣ ቀራፂ፣ የሥነጥበብ መምህር እስክንድር ቦጎሲያን
👉 ፀሐፌ ተውኔት፣ ባለቅኔ፣ የታሪክ ተመራማሪ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን
👉 ሠዓሊ እና ገጣሚት ከበደች ተክለአብ ፤
@tarikawi_fotowech
ኢትዮጵያ ከ86 አመት በፊት በ1923 ዓ.ም፡፡ ምስሎቹ ናሽናል ጂኦግራፊ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በአለ ሲመት ወደ ኢትዮጵያ በላከው ወኪሉ በሮበርት ሙር አማካኝነት
በአዲስ አበባ፣ በጎጃም/ጣና እና በትግራይ ካነሳቸው ፎቶግራፎች መካከል እንደሚሆኑ ይታመናል፡፡
Color Photographs of Life Magazine/Ethiopia:
www.vintag.es/2013/10/color-photos-of-ethiopia-1931.html
@tarikawi_fotowech
