Dire-Dawa University
📈 Analytical overview of Telegram channel Dire-Dawa University
Channel Dire-Dawa University (@dduniv) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 19 680 subscribers, ranking 10 050 in the Education category and 1 752 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 19 680 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 350 over the last 30 days and by 38 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 36.00%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.64% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 7 085 views. Within the first day, a publication typically gains 3 077 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 31.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“An Official Channel of Dire-Dawa University”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 September | +38 | |||
| 05 September | +13 | |||
| 04 September | +40 | |||
| 03 September | +7 | |||
| 02 September | +10 | |||
| 01 September | +31 |
| 2 | ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የከተማ አስተዳደሩን ምክር ቤት ስትራቴጂካዊ ፕላን ለማዘጋጀት የሚያስችል የምክክር መድረክ አካሄደ
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቀጣይ የስራ አቅጣጫውን የሚያመላክት ስትራቴጂካዊ ፕላን (strategic plan) ለማዘጋጀት የሚያስችለውን የመነሻ ሰነድ ይፋ አድርጓል። የሚዘጋጀውን ሰነድ አስመልክቶም ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን ምክክር ከዩኒቨርሲቲው ተወካዮች ጋር አካሂዷል፡፡
በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር፣ ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ፣ የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና መምህራን ተሳትፈዋል።
ይህ በእውቀትና በምርምር ላይ የተመሠረተ የስትራቴጂክ ፕላን ዝግጅት የምክር ቤቱን የአሰራር ዘይቤ በዘመናዊ መንገድ ለማዋቀር፣ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍና ተቋማዊ አቅምን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተመልክቷል።
የሰነድ ዝግጅቱን በስኬትና በታቀደለት የጥራት ደረጃ ለማጠናቀቅ ይቻል ዘንድ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና ከምክር ቤቱ የተውጣጡ ባለሙያዎችና አመራሮች የተካተቱበት አብይ ኮሚቴ እና ንኡስ ኮሚቴ ተቋቁመው ቀጥታ ወደ ተግባራዊ የስራ እንቅስቃሴ መግባታቸውም ተገልጿል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ባስተላለፉት መልዕክት፣ የስትራቴጂክ ፕላን ዝግጅት ስራው በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት መስፈርቶች መሰረት ተሰርቶ እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን እያደረገ ሲሆን ተቋማት በሚያቀርቡት ጥያቄ እና የትብብር ስራዎች ማዕቀፍ መሰረት መሰል ደጋፎችን መድረጉን እንደሚቀጥል ተመላክቷል፡፡ | 4 359 |
| 3 | የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለ200 ወጣቶች የሥራ ፈጠራና የአስተሳሰብ ለውጥ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በማኅበረሰብ ተሳትፎ ዳይሬክቶሬት አማካኝነት የሚያካሂደው የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፈቃደኝነት መርሃ ግብር አካል የሆነውን የወጣቶች አቅም ግንባታ ሥልጠና ዛሬ ማስጀመሩን አስታወቀ።
ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ 200 ወጣቶች የሚሳተፉበት ይህ ሥልጠና፤ በሥራ ፈጠራ (Entrepreneurship) እና በአስተሳሰብ ለውጥ (Mindset Change) ላይ ያተኮረ ነው። ሥልጠናው ወጣቶች የራሳቸውን እምቅ አቅም እንዲረዱ፣ የሥራ ፈጠራ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ፣ ግልጽ ግብ በማስቀመጥ በተግዳሮቶች ውስጥ አዳዲስ ዕድሎችን የመመልከት አዎንታዊ አስተሳሰብ እንዲገነቡ ለማስቻል ታስቦ እንደተዘጋጀ ተጠቁሟል፡፡
በሥልጠናው ወቅት ተሳታፊዎች በሥራ ፈጠራ መሠረታዊ እውቀቶች ላይ ከሚኖራቸው ግንዛቤ በተጨማሪ በራስ መተማመን፣ ተጠያቂነት፣ ችግር ፈቺነት፣ ጽናት እና የወደፊት ዕቅድ ዝግጅት ላይ ተግባራዊ ልምዶችን የሚያስጨብጡ ትምህርቶች ይሰጣቸዋል።
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በዚህ አቅም የመገንባት ተነሳሽነቱ፤ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ እንዲሰማሩና በአካባቢያቸው ሁለንተናዊ ልማት ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለራሳቸው እንዲሁም ለመጡበት ማኅበረሰብ ተጨማሪ እሴት እንዲፈጥሩ ለማስቻል በማሰብ ስልጠናውን እንዳዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ከፍተኛ ልምድ ባላቸው የዩኒቨርሲቲው ምሁራን አማካኝነት እነደሚሰጥ ተጠቁሟል፡፡ | 5 108 |
| 4 | #የስራ_ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተመለከቱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ህጋዊ ማስረጃዎቻችሁን ይዛችሁ ማስታወቂያው ላይ በተጠቀሱት አድርሻዎች በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን፡፡
ዝርዝር መስፈርት እና ተያያዥ መረጃዎችን ከታች ይመልከቱ!! | 5 994 |
| 5 | #Join_Dire_Dawa_University-where dreams become reality. | 5 591 |
| 6 | #Join_Dire_Dawa_University-where dreams become reality. | 1 |
| 7 | #Opportunity_to_Join_DDU
Dire Dawa University invites new private applicants who meet the higher education admission requirements announced by the Ministry of Education for the 2019 E.C. academic year to apply for Bachelor’s degree programs offered through Night and Weekend programs in various fields of study. | 6 536 |
| 8 | ማስታወቂያ፡ ነሐሴ 20 ቀን 2018ዓ/ም #ሁለተኛው_ክፍለ_ጊዜ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና #ከቀኑ_7_00_ሰዓት ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ተፈታኞች ስም ዝርዝር፣ የመፈተኛ ቦታ እና ተያያዥ መረጃዎችን ከዚህ በታች በተመለከተው ሰንጠረዥ ውስጥ እንድትመለከቱ እናሳስባለን፡፡ | 11 499 |
| 9 | No text... | 9 007 |
| 10 | ማስታወቂያ፡ ነሐሴ 20 ቀን 2018ዓ/ም #የመጀመሪያ_ክፍለ_ጊዜ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ተፈታኞች ስም ዝርዝር፣ የመፈተኛ ቦታ፣ ሰዓት እና ተያያዥ መረጃዎችን ከዚህ በታች በተመለከተው ሰንጠረዥ ውስጥ እንድትመለከቱ እናሳስባለን፡፡
የመጀመሪያው ክፍለ ጊዜ መፈተኛ ሰዓት፡ ከ ጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ | 7 428 |
| 11 | No text... | 6 641 |
| 12 | የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ መውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም የደስታ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ይመኛል።
ኢድ ሙባረክ
================
Yunivarsiitiin Dirree Dawaa hordoftoonni amantaa musliimaa marti keessan baga ayyaana Moowlidaa nagaan geessan yeroo jedhu, ayyaanichi kan nagaa, gammachuu fi jaalalaa akka isiniif ta'u ni hawwa.
Iid Mubaarak
================
Jaamacadda Diridhaba waxa ay dhammaan umadda muslimiinta ah ugu hambalyaynaysaa munaasabadda dhalashada Nabi Maxamed SCW (Mawliidka nabiga ) waxayna jaamacaddu rajaynaysa munasibad farxad iyo barwaqo ah uu ahato dhamaan bulsho waynta ku dhaqan magalada Diridhaba.
Ciid Mubaarak | 5 939 |
| 13 | በአርቲስት ኡስማዮ ሙሳ ህይወት ታሪክ ዙሪያ የተፃፈ መፅሐፍ ዛሬ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተመረቀ
የታዋቂውን አርቲስት ኡስማዮ ሙሳ የህይወት ታሪክ የሚያስቃኝ እና በአርቲስቱ የመጀመሪያ ልጅ አርቲስት ሳርቱ ኡስማዮ የተፃፈ መጽሐፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራር እና ጥሪ የተደረገላቸው ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ አርቲስት ኡስማዮ ለኦሮሞ የሙዚቃ እና ስነ ጥበብ እድገት ካበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ባልተናነሰ መልኩ ለህዝቦች እኩልነት፣ ነፃነት እና አንድነት ታሪክ የሚዘክረው አሻራ ያኖረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለህዝብ እኩለነት ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች እንዲታወሱ የሚያደርገውን ጥረት ያደነቁት ክቡር አቶ አብዲ፣ ታላላቅ የማህበረሰቡ መሪዎች እና ፋና ወጊ የነፃነት ታጋዮች እንዲታወሱ ፣ አበርክቷቸው ለትውልድ አንዲተላለፍ ታሪካቸው በመፅሐፍ መልክ ተሰንዶ ለአንባቢወ መድረስ አለበት ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም በበኩላቸው፣ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ለትውልድ የሚተላለፉ ታሪኮችን በመፅሐፍ መልክ አዘጋጅቶ የማቅረብ ልምድ ያልዳበረ መሆኑን ገልፀው በአርቲስት ኡስማዮ ታሪክ ዙሪያ የተዘጋጀው መፅሐፍ በብዙ መልኩ አስተማሪ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡ መፅሐፉ በአርቲስቱ ሴት ልጅ መዘጋጀቱ ሴት ፀሐፊያንን ከማበረታታት ባሻገር የህዝብ ታሪክ፣ ባህል እና ቋንቋ እድገት ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
የአርቲስት ኡስማዮ ሙሳ ልጅ እና የመፅሐፉ ፀሐፊ አርቲስት ሳርቱ ኡስማዮ በበኩሏ በመፅሐፉ መመረቅ የተሰማት ደስታ እና የወላጅ አባቷ በህይወት ኖሮ ይህንን የህዝብ ፍቅር ያለማየቱ | 6 948 |
| 14 | No text... | 6 244 |
| 15 | ለድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች በሙሉ
የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል። በመሆኑም የመፈተኛ ጣቢያችሁን ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ያደረጋችሁ ተፈታኞች በሙሉ የተመደባችሁበትን ቀን እና መፈተኛ ክፍል በዩኒቨሪስቲ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ ገጽ እንዲሁም ዋናው ግቢ መግቢያ በር ላይ የሚለጠፍ መሆኑንን እየገለጽን ባመለከታችሁበት ድህረ-ገፅ ወይም e-mail በኩል የሚላክላችሁን የመጠቀሚያ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) ይዛችሁ በዕለቱ በተመደባችሁበት ቀን እና ሰዓት እንድትገኙ እናሳስባለን።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት | 7 620 |
| 16 | የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ጋር በትብብር ለመስራት ተስማማ፦ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ነጻ የንግድ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል ያቋቁማል::
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን ውይይት ከንግድ ምክር ቤቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር አድርጓል፡፡ ሁለቱ ተቋማት በማማከር እና ስልጠና፣ በምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም የተለያዩ ኮንፍረንሶችን በትብብር ማዘጋጀት በሚችሉበት ጉዳይ ዙሪያ መክረዋል፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተማም አወል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎች ጋር በመቀራረበ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይነትም በተለይ አዲስ የቢዝነስ ሀሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪዎች እንዲሁም ስራ ነክ ጉዳዮች ላይ ነፃ የቢዝነስ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል እንደሚከፍት ይፋ አድርገዋል፡፡
የኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ዋና ፀኃፊ ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ በበኩላቸው ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ምርምሮችን የመስራት ልምድ እና እውቀት ያላቸው ምሁራን መገኛ መሆኑን ገልፀው ምክርቤቱ ይህንን አቅም ለመጠቀም ከትምህርት ተቋማቱ ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ዘርፍን የትኩረት አቅጣጫ በማድረግ እና የሰለጠነ የሰው ሃይል አብቅቶ ለስራ ከማቅረቡም በላይ የንግዱን ማህበረሰብ፣ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም አዳዲስ የቢዝነስ ሃሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን እና ተማሪዎችን የሚደግፉ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ በመድረከ ተመላክቷል፡፡ | 6 037 |
| 17 | #የስራ_ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተመለከቱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ህጋዊ ማስረጃዎቻችሁን ይዛችሁ ማስታወቂያው ላይ በተጠቀሱት አድርሻዎች በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን፡፡
ዝርዝር መስፈርት እና ተያያዥ መረጃዎችን ከታች ይመልከቱ!! | 6 155 |
| 18 | የሐዘን መግለጫ
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና ት/ርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር አና የአይን ስፔሻሊስት ሀኪም የነበሩት ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነሀሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በ ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል፡፡
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ | 8 297 |
| 19 | የውሃ ስርጭት እና ተደራሽነትን ማሻሻል የሚያስችል የስራ ውል ከአስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር ተደረገ
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የውሃ ስርጭት ችግር በቋሚነት መፍታት የሚያስችል የስራ ስምምነት ከድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር ተፈርሟል።
ዩኒቨርሲቲው የውሃ እጥረት ችግርን መቅረፍ የሚያስችሉ የከርሰ ምድር ውሃ ቢያስቆፍርም የስርጭት ክፍተት በመኖሩ ምክንያት በተማሪዎች መኖሪያ፣ በቢሮዎች እና የመምህራን መኖሪያ ቤቶች አካባቢ የውሃ ስርጭት እጥረት ተከስቷል። ከአስተዳደሩ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጥን ጋር የተደረገው ስምምነት ይህንኑ የውሃ ስርጭት ችግር በዘላቂነት የሚቀርፍ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ፕሮጀክት፣ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ እና በመምህራን መኖሪያ አካባቢዎች የሚስተዋለውን የአቅርቦት ችግር እንደሚያቃልል ተገልጿል።
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም እንደገለጹት ‘’የድሬዳዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ፕሮጀክቱን በወቅቱ በማጠናቀቅ በተቋም ደረጃ የሚስተዋለውን የውሃ ስርጭት ተግዳሮት ለማቃለል የተለመደ ድጋፉን እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አክለውም ባለስልጣኑ በቀጣይም ግቢውን የማስዋብ እና የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ረገድ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትብብር እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡።
የድሬዳዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ ሙሴ በበኩላቸው ‘’ዩኒቨርሲቲው በራሱ ጥረት እያከናወናቸው ያሉትን የልማት ስራዎችን አድንቀዋል። አቶ መሀመድ አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተጀመረውን የውሃ ስርጭት ፕሮጀክት ከተያዘለት ጊዜ ቀድሞ ለማጠናቀቅ ተገቢውን አመራር እንደሚሰጡ ገልጸዋል። | 8 174 |
| 20 | 📢𝐂𝐀𝐋𝐋 𝐅𝐎𝐑 𝐏𝐀𝐏𝐄𝐑𝐒 | 𝐇𝐚𝐫𝐥𝐚 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐚𝐥 𝐨𝐟 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐢𝐞𝐝 𝐒𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐞𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐌𝐚𝐭𝐞𝐫𝐢𝐚𝐥𝐬
We are cordially inviting researchers, scholars, and academics to submit their original research for publication in the upcoming issue!
🔹 Volume: 4, Issue 2
🔹 Accreditation: Nationally Accredited Journal in Ethiopia 🇪🇹
🔹 Scope: Applied Sciences, Materials Science, and Engineering
📩 Submit Your Manuscript Today!
For submission guidelines, editorial policies, and inquiries, please visit our website or contact the editorial team. | 7 178 |
