en
Feedback
ብርሃን ይኹን💡

ብርሃን ይኹን💡

Open in Telegram

ብርሃን ይኹን መጽሐፍ ቅዱስን በተለያዩ መንገዶች በማድረስ ሰዎችን ኹሉ ክርስቶስን ወደ መምሰል ሕይወት እንዲጠጉ የሚያግዝ ክርስቲያናዊ አገልግሎት ነው። Facebook page link https://www.facebook.com/berhanyihunofficial/ Instagram link https://www.instagram.com/berhan_yihun/

Show more
1 074
Subscribers
+224 hours
+197 days
+2330 days
Posts Archive
photo content

photo content

ተነስቷል
ተነስቷል

ጌታ ቅርብ ነውና ጽድቅ በእምነት ይገኛል እንጂ የሰውን ልፋትና ጥረት አይጠይቅም። ስለዚህ ኢየሱስን ወደ ምድር ለማውረድ ወደ ሰማይ መውጣት አያስፈልግም። ጌታችን እርሱ ራሱ ሰው ሆኖ አስቀድሞ ወርዷል። እንደዚሁም ኢየሱስን ከሙታን ለማውጣት ወደ ጥልቅ መውረድ አያስፈልግም። ጌታችን አስቀድሞ በትንሣኤ ከጥልቁ ወጥቷል። ከሰዎች የሚጠበቀው፣ “ጌታን ከከፍታ ላይ ማን ያወርድልናል? ወይም ከሙታን ስፍራ ማለትም ከጥልቁ ማን ያወጣልናል?” የሚል ምክንያት መደርደር ሳይሆን፣ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብ አምኖ በአፍ መመስከር ነው (ቁ. 8-10)። የተሰቀለው ገጽ 197 ዻውሎስ ፈቃዱ

photo content

ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው

የዮሐ 1:14 ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ዘጸአት 33:18, 22-23 እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳ
+1
የዮሐ 1:14 ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ዘጸአት 33:18, 22-23 እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ። ክብሬም ባለፈ ጊዜ በሰንጣቃው ዓለት አኖርሃለሁ፥ እስካልፍ ድረስ እጄን በላይህ እጋርዳለሁ፤ እጄንም ፈቀቅ አደርጋለሁ፥ ጀርባዬንም ታያለህ፤ ፊቴ ግን አይታይም።

Repost from Fan's Pulpit
"የአምላኩ ፈቃድ ፈቃዱ ኾኖ በፍጹም ነፍሱ በጌታ ታምኖ በነገር ኹሉ ሕይወቱ ረክቶ ጻድቅ ይኖራል በቃሉ ጸንቶ (2)" ፓ/ር ተስፋዬ ጋቢሶ
"የአምላኩ ፈቃድ ፈቃዱ ኾኖ በፍጹም ነፍሱ በጌታ ታምኖ በነገር ኹሉ ሕይወቱ ረክቶ ጻድቅ ይኖራል በቃሉ ጸንቶ (2)" ፓ/ር ተስፋዬ ጋቢሶ

ቅዱስ አውግስጢኖስ “እርሱ የእኛን ዘላለማዊ ቁስል የፈወሰው በራሱ ላይ ያንን ሁሉ መከራ በታገሠበት ስፍራ ነው፤ እኛን ከዘላለም ሞት ያዳነን እርሱ በጊዜያዊ ሞት በሞተበት በዚያው መስቀል ላይ ነው”

Repost from Fan's Pulpit
"...በግል ጸሎታችን ውስጥ ጎልጎታን የሚያስታውስ ምስጋና ከጠፋ፣ በምንሰማው ስብከት ውስጥ የመስቀሉ ማዕከላዊነት ከቀረ፣ በጌታ ራት ወቅት የመስቀሉ ትዝታ እንደ አማራጭ ከታየ፣ የጎልጎታው ክስተት፣
"...በግል ጸሎታችን ውስጥ ጎልጎታን የሚያስታውስ ምስጋና ከጠፋ፣ በምንሰማው ስብከት ውስጥ የመስቀሉ ማዕከላዊነት ከቀረ፣ በጌታ ራት ወቅት የመስቀሉ ትዝታ እንደ አማራጭ ከታየ፣ የጎልጎታው ክስተት፣ በርሱም የተከናወነው አስደናቂ ነገር በጥቂቱም ቢሆን ከእይታችን ከተሰወረ፣ ያን ጊዜ የቅድስና ሕይወት ከእኛ መጥፋቱ አይቀሬ ይሆናል።" ስቱአርት ኦሊዮት "እነሆ ወንጌሉ: የሮሜ መልእክት ማብራሪያ በቀላል አቀራረብ፣ ትርጉም በፋኑኤል ብርሃነ (ዐዲስ ዐበባ፣ ጎስፕል ፎከስ ሚኒስትሪ፣ 2018 ዓ.ም) ገጽ 73 መጽሐፉ ሣር ቤቴ ኤግስት ሕንጻ 4ኛ ፎቅ ላይ ይገኛል።

“ቶማስም፣ “ጌታዬ፤ አምላኬም!” አለው። ኢየሱስም፣ “አንተ ስላየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብፁዓን ናቸው” አለው።”
“ቶማስም፣ “ጌታዬ፤ አምላኬም!” አለው። ኢየሱስም፣ “አንተ ስላየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብፁዓን ናቸው” አለው።”

እግዚአብሔር የፈጠረን በርሱ ብቻ ሊረካ የሚችል ጥማት በውስጣችን አኑሮ ነው። - ጆን ሊን

"You are constantly being molded either into the image of Christ or into the image of this world." — Jonny Ardavanis

Repost from Fan's Pulpit
"ሕጉ ወደ ወንጌሉ ሲወስደን፣ ወንጌሉ ደግሞ ሕጉን እንድንታዘዝ ነጻ ያወጣናል...ጆን ቡንያን በአንድ ወቅት እንዲህ ብሏል፣ ሕጉ 'ጆን ሩጥ! ሩጥ! ብሎ ያዝዛል፤ ነገር ግን የምሮጥበትን እጅም ኾነ እግር አይሰጥም። ወንጌሉ ግን የተሻለውን መልካም ዜና ያውጃል፤ ብረሩ ብሎ ክንፍንም ይሰጣል።" Gospel Centered Life ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ

photo content