Fan's Pulpit
Open in Telegram
Fanuel Brhane:- This Channel Serve as a platform to study and discuss the word of God and how to live it in everyday life.
Show more213
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
November '23
November '230
in 0 channels
October '23
+222
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 27 November | 0 | |||
| 26 November | 0 | |||
| 25 November | 0 | |||
| 24 November | 0 | |||
| 23 November | 0 | |||
| 22 November | 0 | |||
| 21 November | 0 | |||
| 20 November | 0 | |||
| 19 November | 0 | |||
| 18 November | 0 | |||
| 17 November | 0 | |||
| 16 November | 0 | |||
| 15 November | 0 | |||
| 14 November | 0 | |||
| 13 November | 0 | |||
| 12 November | 0 | |||
| 11 November | 0 | |||
| 10 November | 0 | |||
| 09 November | 0 | |||
| 08 November | 0 | |||
| 07 November | 0 | |||
| 06 November | 0 | |||
| 05 November | 0 | |||
| 04 November | 0 | |||
| 03 November | 0 | |||
| 02 November | 0 | |||
| 01 November | 0 |
Channel Posts
ከጸጋ ሰማይ ሥር!
ግራ መጋባቴ፣ ልተውኽ መወሰኔ፣ ኮብላይነቴ አያደክምህም። ኹሉን ነገር ርግፍ ዐድርጌ ብተወውስ እያልኩ ሳውጠነጥን፣ ምን ዋጋ አለው! ርሱ ሲተወኝ አይደል! ብዬ የመተው ሐሳቤን እተወዋለሁ! ደግሞ እንዳሰብኩት ትመጣና አለሁ ትለኛለህ!
በጭጋግ ውስጥ ስራመድ በወለምታና ስብራት ተስፋ እንዳልቆርጥ እጆችህ በስሱ ሲዳስሱኝና ሲመሩኝ ይሰማኛል። የፈለኩትን ያኽል ብወራጭ አንድም ብለህ አትደነግጥም፣ እስኪደክመኝና እስካቆም ጠብቀህ በል ጉዞውን ቀጥል ትላለህ! እየተነጫነጭኩም እቀጥላለሁ። ለምን እንዲህ እንዳመረርክብኝ ግን የሚገባኝ ቆይቶ ነው።
ለኔው ነው! ውሱኑ ልጅህ አንተ ካየኸው መልካም ነገር እንዳልጎድል ነው፤ ሥርዐትህን እንድማር፣ አንተን እንድመስል ነው። ደካማና ተሰባሪ ሸክላ ላይ እንዲህ ዐይንህን ያጠናኸው ለምን ይሆን? ቃልህ ከአንድም ኹለቴ መልሱን ነግሮኛል፦ "የፀጋህ ክብር ይመሰገን ዘንድ" ፣ "የኀይልህ ታላቅነት" ከእኔ እንዳልሆነ ይታወቅ ዘንድ!
"አትተወኝም በቃ
አትረሳኝም በቃ
...አትተወኝም በቃ"
ግልባጭ:- ለደከማችኹ ኹሉ!
| 2 | No text... | 0 |
| 3 | “ለመንግሥተ ሰማይ ሕይወት ለመዘጋጀት ጊዜውና ዕድሉ ይኖራችሁ ዘንድ ይህ ሕይወት ተሰጥቷችኋል፤ ሞትም ቢሆን የእናንተ እንድታደርጉት የተሰጣችሁ ነው፡፡ ሞት ማለት ወደ አባታችሁ ቤት ሊወስዳችሁ የመጣ መልእክተኛ ነው፡፡ አሁን ያለው ነገር ኹሉ በመንገድ ጉዟችሁ ወቅት ለማገዝ ለእናንተ የተሰጠ ነው፤ በጉዞአችሁ መጨረሻ ላይም፣ ለዘላለም ደስ እንድትሰኙና ምሉዓን እንድትሆኑ ወደ ፊት የሚመጡትም ነገሮች ኹሉ የእናንተ ናቸው፡፡”
ማቲው ሄንሪ
(1ቆሮንቶስ 3:22-23) | 0 |
| 4 | No text... | 0 |
| 5 | Soon to be, R we ready? | 0 |
| 6 | No text... | 0 |
| 7 | No text... | 0 |
| 8 | "Religion is outside - in, but the gospel is inside - out"
Tim Keller | 0 |
| 9 | No text... | 0 |
| 10 | “በመከራዬ ቀን እግዚአብሔርን ፈለግኹት፤
እጆቼ በሌሊት በፊቱ ናቸው፥ አላረፍኹምም፥
ነፍሴም መጽናናትን አልቻለችም።
እግዚአብሔርን ዐሰብኹት፥ ደስ አለኝም፤” (መዝ. 77/2-3)
ሰው ሕይወቱን በገዛ እጁ የሚያጠፋው ለምን ይኾን? ከዚህ የመጨረሻ ዐጕል ውሳኔ ላይ የሚደርሰውስ፥ ያስጨነቀው ጕዳይ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ ምን ያኽል ቢከብደው ነው? ብለን መጠየቃችን አይቀርም። በአንጻሩ ደግሞ ብዙና እጅግ የሚያስጨንቅ ነገር ተሸክሞ፥ ወደዚህ ውሳኔ ከመድረስ ወይም ራስን በራስ ከማጥፋት ይልቅ፥ በዚህ ዓለም ላይ በማንኛውም አቅጣጫ ሊኾን ይችላል፥ የመጨረሻ በተባለ በማንኛውም የዝቅታ፣ የውርደትና የጕስቍልና ኑሮ ውስጥ ገብቶ ሕይወቱን በማቈየት፥ እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ፥ ‘ከሞቱት በላይ፥ ከቆሙት በታች’ ኾኖ የሚቀጥል ምስኪን ሰውን ስንመለከት፥ ጥያቄውን በተቃራኒው መንገድ ለማንሣት እንገደዳለን። ኢዮብም፥ “እነሆ፥ ቢገድለኝ ስንኳ ርሱን በትዕግሥት እጠባበቃለኹ፤ ነገር ግን መንገዴን በፊቱ አጸናለኹ።” (ኢዮ. 13፥15) ብሏል። አዎን፤ ኹለቱም የውሳኔ ጕዳይ ነው።
ሕይወታችን ከእግዚአብሔር የተሰጠችና ወደ እግዚአብሔር የምትመለስ (መክ. 12፥7) ናት፤ ወይም ራሱ ይወስዳታል እንጂ ባለቤቱም ኾነ ሌላው ሰው ሊያጠፋት አይገባም። ስለዚህ በማንኛውም ውጫዊም ኾነ ውሳጣዊ ጫናና ግፊት የተነሣ፥ ሰው ራሱን ወደ ማጥፋት ከባድ ውሳኔ ከመድረሱ በፊት፥ ዐቅሙን አሰባስቦ ወደ ተስፋ መቍረጥ የሚወስዱትን ጕዳዮች ለማቃለል መሞከርና መንገዶቹን ኹሉ መዝጋት አለበት። በተስፋዎች ኹሉ ላይ ተስፋ ቢቈርጥ እንኳ፥ አንድና ርሱ ብቻ ተስፋ በኾነው በእግዚአብሔር ግን ተስፋ መቍረጥ የለበትም።
በተጠቀሰው መዝሙር ውስጥ፥ ሳፋን በመከራው ቀን እግዚአብሔርን ያለ ዕረፍት ሲፈልግ፣ እጆቹ በሌሊት እንኳ ተዘርግተው በፊቱ እንደ ነበሩ፥ በዚህ ኹሉ ውስጥ ግን ነፍሱ መጽናናት እንዳልቻለች ተናግሯል። በመከራ ውስጥ እያለፈ ላለና ተስፋው ኹሉ ተሟጥጦ አንድ ተስፋ ብቻ፥ ርሱም እግዚአብሔር ለቀረው ሰው፥ ርሱኑ ተስፋ እያደረገ ለጊዜው መጽናናት አለመቻል ምንኛ ከባድ ነው! ይሀ ወደ ሌላ ከባድ ውሳኔ ሊያደርስ ይችላል። ነገር ግን ዘማሪው በቀረው አንድና አስተማማኝ ተስፋ፥ በእግዚአብሔር ተስፋ መቍረጥ አልፈለገም። ዳዊት “አኹንስ ተስፋዬ ማን ነው? እግዚአብሔር አይደለምን? ትዕግሥቴም ከአንተ ዘንድ ነው።” (መዝ. 39፥7) እንዳለው፥ ይህ ዘማሪ ተስፋ ያደረገው እግዚአብሔር በሰጠው ትዕግሥት እግዚአብሔርን የሙጥኝ ማለቱን ቀጠለ። ወደ መጽናናትና ከመከራው መውጣት የቻለው ታዲያ ተስፋውን እግዚአብሔርን ባሰበ ጊዜ ነው፤ “እግዚአብሔርን ዐሰብኹት፥ ደስ አለኝም፤” (መዝ. 77/2-3)።
ተስፋችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ተስፋ ሊያስቈርጥ በሚችል ችግር ውስጥ ብንገኝ፥ አንተን ዐስበን ተስፋችን እንዲቀጠልና እንድንጽናና፥ ደስም እንዲለን ርዳን!
አግዛቸው ተፈራ | 0 |
| 11 | የሐዘን ደግስ!
ምድሪቱ እያለፈችበት ያለችው የሰቆቃና የመከራ መጠን፣ የሰው ልጅ ጥበብ ሊፈታውና ሊያርመው ከሚችለው እያለፈ እየመጣ ነው፡፡ አመጣሁ የሚለውም መፍትሒ ለበለጠ ውስብስብና ውሉ ለማይታወቅ ችግር የሚዳርግ እየሆነ ነው፡፡ ሽንቊሩ በዝቷል፤ ጠጋኝ ነኝ ባዩም እንዲሁ፡፡ ሕመማችን ግን እያዋል እያደረ ባሰ እንጂ ጠገግ ሊል አልቻለም፡፡ የችግሩ መብዛት ብዙዎቻችንን ራስ ወዳድ አድርጎናል፡፡ ልንፈታው ለማንችለው ነገር መብሰልሰል ምን ለውጥ ያመጣል በሚል ወደ ራሳችን አተኵረናል፡፡ ታሪክ ወደ አንድ አቅጣጫ እየተጠቀለለ መንጐዱን ቀጥሏል፤ ልጓሙን ለመያዝ የሚውተረተረው የሰው ልጅ ከዐቅሙ በላይ ሆኖበታል፡፡ ነገ ነገሮች ይሻሻሉ ይሆን? አይመስለኝም! ከተሻሻሉም ለሚመጣው ሌላ ውስብስብ ችግር መደላድል ለመሆን ነው! ይህ ጨለምተኝነት ሊመስል ይችላል፤ ዳሩ ግን ታሪክ የሚያስተምረን ይህን ብቻ ነው፡፡
ሰማዩም ዝም ያለ ይመስላል! እንደ ፍጥርጥራችሁ ብሎን ይሆን? በተለይ በእግዚአብሔር እናምናለን፣ ርሱን እናውቀዋለን የምንል ሰዎች፣ ውሉ ለጠፋበት ዘመን የምንሰጠው ምላሽ ቅርብ-ጠለቅ ነው፡፡ በነገሩ ዙሪያ ከልባችን ዐስበንና ተጨንቀን እንዲሁም ጸልየን ሳይሆን፣ ለሚነዘንዘን ሕሊናችን ዕረፍት ስንል የማስታገሻ ሐሳቦችን እንውጣለን፡፡ ሕመሙ ግን ብዙ ሳይቆይ ያገረሻል፡፡ ምላሽ የመስጠቱ ጕዳይ ለእኛ ቢርቅ እንኳን፣ በፈራረሰች ምድር መካከል ቊጭ ብሎ ሰቆቃውን እንደተየበልን ኤርምያስ፣ ሐዘንን የመጋራት ዝንባሌ አናሳይም፡፡
መጽሐፉ “ከሚያዝኑት ጋራ እዘኑ” ያለንን ረስተን፣ ያዘኑትንና እኛን የፈጠረን አምላክ ለየቅ የሆነ እስኪመስል ድረስ ጮቤ እንረግጣን፡፡ የተወሰደብን ልብ አለ! የሆነ ቦታ ተወስዶ የተቆለፈበትና ቊልፉ ሩቅ የተወረወረበት ልብ ያለን እንመስላለን! ደንዝዘናል፡፡ ለመደሰት ብቻ ሳይሆን ለማዘን የሚያነቃን መንፈስ ያስፈልገን ይሆን? ነቢዩ አሞጽ ባገለገለበት ዘመን፣ ብዙኀኑ በአዘን ውስጥ ተከርችመው ሳለ፣ “ቀን የወጣላቸው” የተባሉት በዝሆን ጥርስ ባስጌጡት ቤቶቻቸው የወይን ጠጅ ይራጩ ነበር! በክረምትና በጋ ቤቶቻቸው ይንፈላሰሱ ነበር፡፡
በእግዚአብሔር ፊት ተሰብስበን ንስሓ የምንገባበትና፣ ወደ ቀልባችን የምንመለስበት፣ የምድሪቱን ሐዘን የምንካፈልበት የሐዘን ድግስ/ኮንሰርት ያስፈልገን ይሆን? | 0 |
| 12 | No text... | 0 |
| 13 | No text... | 0 |
| 14 | "ወንጌሉ፣ የእግዚአብሔር ቅድስናን የሚገልጥ ጨረር ሲሆን፣ ቁስልን እያጋለጠ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ፈውስንም የሚሰጥ ነው።"
ጎርደን ኬዲ | 0 |
| 15 | No text... | 0 |
| 16 | መስቀል ትምክሕታችን!
ታዋቂው የስነ-መለኮት ምሑር ጆን ስቶት “የክርስቶስ መስቀል” (The Cross of Christ) በሚለው መጽሐፋቸው፣ በምልክትነት የክርስትና ዕምነት ስለሚጠቀመው “መስቀል” ጥንታዊ እሳቤውን ያስቀምጣሉ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተሰቀለበት ዘመን፣ መስቀል የወንበዴዎች እና የወንጀለኞች መቀጣጫ በመሆኑ፣ አስቀያሚ እና እጅግ የተጠላ ነገር ነበር፡፡ ከክርስቶስ ሞት እና ትንሳዔ ጋር ተያይዞም በእርሱ በማመን እና ሕይወታቸውን በመስጠት የተከተሉት ሐዋርያት እና ደቀመዛሙርት ከነበረባቸው ከፍተኛ መከራ እና ስደት ጋር ተያይዞ፣ ዕምነታቸውን በቀጥታ የሚገልጽ ምልክት አይጠቀሙም ነበር፡፡ ስለሆነም “መስቀል” በመጀመርያዎቹ መቶ ዓመታት በምልክትነት አልዋለም ነበር፡፡
ከሮም ወጣ ብሎ በሚገኝው የካታኮምብ ዋሻ፣ ከወደረኞቻቸው እና ሊገድሏቸው ከሚፈልጉ ለማምለጥ ተደብቀው የነበሩት ክርስትያኖች፣ በዋሻው ግድገዳ ላይ ከሳሏቸው ምልክቶች ውስጥ ፒኮክ (ኢመዋቲነትን ለማመላከት)፣ ርግብ፣ የዘንባባ አክሊል፣ እና ዓሳ (በግሪክ ዓሳ ኢክተስ ሲሆን እያንዳንዱ ቃል የሚሸከመው ሀሳብ አለ፡-ICTHS Iesous Christos Theou Huios Soter ትርጉሙም፡- Jesus Christ, Son of God, Savior፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ አዳኝ የሚል ነው):: ጆን ስቶት አያይዘውም እስከ 6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ መስቀል በምልክትነት አለመዋሉን ይናገራሉ፡፡ ምንም እንኳን ክርስትያኖች ለረዥም ጊዜ በምልክትነት ባይጠቀሙትም፣ የእምነታቸው ማዕከል፣ የትምህክታቸው ሁሉ ምንጭ፣ የድነታቸውም ምሰሶ እንደሆነ በስብከታቸውም፣ በጽሑፎቻውም በዝማሬዎቻቸው ይገልጹ ነበር፡፡ እንዲያውም ጠርጢዮስ (Tertullian) በ200 ዓ.ም ላይ “ወደፊት ስንራመድ ሆነ ስንንቀሳቀስ፣ ስንወጣም ሆነ ስንገባ፣ ልብሳችንን ስንለብስ ሆነ ጫማችንን ስናጠልቅ፣ ገላችንን ስንታጠብ፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ስንቀመጥ ወይም መብራታችንን ስንለኩስ፣ ….በየትኛውም የቀን ተቀን እንቅስቃሴያችን፣ በግንባራችን ላይ የመስቀሉን ምልክት ልናመለክት ይገባል” ብሏል፡፡
ያኔ የሮም መንግስት ለሞት ፍርድ ታልፈው የተሰጡትን ወንጀሎኞች የሚቀጣበት “መስቀል” (በእኛ ዘመን እንደ ኤሌክትሪክ ወንበር ልትወስዱት ትችላላችሁ!) እንዴት የክርስትያኖች ትምክህት ሊሆን ቻለ? ራሳቸው አይሁዳውያን ኢየሱስ በዚህ መስቀል ተቸንክሮ አልላወስ ሲላቸው፣ “ምልክትን አሳየን” በማለት ተሳልቀውበታል፤ የጥበብ ቁንጮ ነን ብለው ለሚመፃደቁት ግሪኮች ደግሞ በመስቀል ላይ መሞት ከመዳን ጋር ተገናኝቶ መሰበኩ የልጅ ጨዋታ መስሏቸዋል፡፡ ይሕን አሰቃቂ የሞት መንገድ የመዳን መንገድ አድርገው ለሚሰብኩት ሐዋርያት ግን፣ መስቀሉ “ወንጌል፣ የምስራች” ነበር፡፡ ወንጌላቸውም፣ በሞቱ፣ የሰውን ልጅ ሞት ስለገደለው፣ ሕይወትን እና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን ስላመጣው፣ ሰላምንም ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገው፣ ሰላምንም ስለ ሰበከው ስለ ኢየሱስ ነው፡፡
ለሐዋርያው ጳውሎስ፣ ይሕ መስቀል፦ ለማዳን የሆነ የእግዚአብሔር ሀይል የተገለጠበት፣ በሕግ እና በነብያት የተሰጠው ተስፋ ፍፃሜን ያገኝበት፣ አሮጌው ስርዓት አልፎ አዲሱ የሕይወት ስርዓት ተመርቆ የተከፈተበት፣ የመቅደሱም መጋረጃ ለሁለት ተሰንጥቆ ወደ ቅደስተ ቅዱሳን ለመግባት ዕድል የተገኝበት፣ ኃጢያትም የተቀጣበት፣ የኃጢያት ይቅርታ የተሰጠበት፣ የሚቃወመን በትዕዛዛት የተፃፈው የዕዳ ፅሕፈት የተደመሰሰበት፣ የእግዚአብሔርም ፍቀር የተገለጠበት ነው፡፡ ምልክቱ የሚጠቁመን አንዳች በክብር የተሞላ እና ዘላለማዊ እውነት አለ፡፡ ምልክት ጠቋሚ ነው፣ ምልክቱ ጋር ደርሰን አንቆምም ወደሚጠቁመን እስካልደረስንም ልባችን ሊያርፍ አይገባውም፡፡ ዛሬ እና ነገ የሚከበረው የ “መስቀል” በዓል ጠቋሚ ሆኖ ቅዱሳን ሐዋርያት በቃላቸው ወደገለፁት እውነት ሊያደርሰን ይገባል፡፡ እንዲያው ታሪኩ እውነት ሆኖ፣ ኢየሱስ የተሰቀለበትን መስቀል ንግስት እሌኒ በጭስ ተመርታ እንዳገኝችው፣ እኛም በመንፈስቅዱስ ተመርተን የተሰቀለውን ኢየሱስን ማግኝት ይሁንልን፡፡ መስቀሉ በእግዚአብሔር እና በሰዎች መሀል የነበረውን ጠላትነት አጥፍቶ ሰላምን ያወረደ እንደሆነ አስበን ከሰዎች ሁሉ ጋር ሰላምን የምንፈልግበት፣ በሰላምም የምንኖርበት ይሁንልን፡፡
መስቀሉን ምክንያት አድርጋችሁ፣ ኢየሱስ በመስቀሉ ላይ ያደረገውን በማሰብ እና ለእርሱም ክብርና ውዳሴን በማምጣት ባዓሉን ለምታሳለፉ ሁሉ መልካም በዓል ይሁንላችሁ፡፡
(ዳግም ልጥፍ) | 0 |
| 17 | እኛን ያግኘን! | 0 |
| 18 | የመለወጥ ብቸኛ ተስፋችን የሰው ጥበብ ሳይሆን የእግዚአብሔር እጅ ነው! | 0 |
| 19 | መጽሐፈ ትርጓሜ ገላትያ በsoft copy ገዝተው ያንብቡ።
ዋጋ፦
200 ETB/ ከሐገር ውጪ ላሉ 10 USD
ቅድመ ኹኔታዎች ስላሉን ክፍያውን ከመፈጸሞ በፊት በውስጥ መስመር ያናግሩን።
@henok_esayas
ይህን መልዕክት ለሌሎች በማጋራት ከጎናችን ይቁሙ! | 0 |
| 20 | "...ስሰባር ስትጠግን
ዐለቀ ስል ስትጀምር
ምሥጋና ለጸጋህ ክብር...
እንደገና አቆምከኝ..." | 0 |
