en
Feedback
የኛ ግጥም 😍😄❤🥰🥺

የኛ ግጥም 😍😄❤🥰🥺

Open in Telegram

እንኳን ደና መጡ🙏 በዚህ ቻናል #ግጥሞች #ቀልዶች እንዲሁም ሀገርኛ ወጎችን አዝናኝ መረጃዎችን በለዛ እናገኛለን ለማንኛውም አስተያየት እንዲሁም ስራዎን ማቅረብ ከፈለጉ ወይም cross ከፈለጉ በዚህ ያናግሩኝ 👉 @berii34 እዚህ ለይ ደሞ👇 @ethiopianye👈join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ for any comment👉 @berii34

Show more
1 919
Subscribers
No data24 hours
+47 days
-1230 days
Posts Archive
አለቀለት ያሉት (በእውቀቱ ስዩም) ከጅረት አጠገብ ፥ቆሞ የኖረ ዛፍ መብረቅ ገነደሰው አሁን ድልድይ ሁኖ፥ ያሸጋግራል ሰው :: “አለቀለት”  ያሉት፤ ተልኮው መች አልቆ ቆሞ የጠቀመ፥ መላ አያጣም ወድቆ፤ @ethiopianye

ናፍቆቴ እናቴ አንቺ የኔ ኩራት እናቴ.... የፍቅር ማሰሮ እናቴ ልበልሽ የናፍቆት እሮሮ ትዝይለኛል ያኔ ጠረንሽ ሲገባ ባፍንጫየ ዘልቆ አሁን ይሸተኛል ከጎኔ እርቆ እናቴ ልበልሽ መጠሪያ ባይኖርሽ ናፍቆትሽ ይበቃል ከጉያሽ መዋሉ እኔን ይጎደኛል ፈገግታሽ መጉደሉ ትዝ ይለኛል ሳቅሽ ጭንቀት ተሸክሞ ሀዘን ተጫጭኖት ያላወኩት ነገር በሀሳብ አፍኖት ትዝ ይለኛል አይንሽ በስስት እያየኝ ሳይነቀል ላፍታ ሰቅሎ ሲክበኝ ከላዩ ከፍታ የኔ የኔ ብየ ዜማ አላወጣው ለምን እንዳትይኝ አንዴ ልበልሽ እኔ ወድሻለው አዚህ ተቀምጨ ሳቅሽን አሸታለው ጠረንሽ ልዩ ነው አስከዛሬ ስኖር ሁኘ በምድር ላይ ካንቺ የምትበልጥ አሎጣችም ፀሀይ እውነት ከምሬ ነው ጨረቃ ብትወጣ ብርሀን ብትሰጠኝ ከሳቅሽ አውጥታ መቸ ልትሰደኝ እኔ ወድሻለሁ እናፍቅሻለሁ እጠብቅሻለሁ ባካል ብንራራቅ ድምፅሽ ይሰማኛል ለሊት አስነስቶ በብርድ ያሞቀኛል ከምበላው ምግብ ከውሀ አብልጦ እንባሽን ማየቱ ይጥለኛል ቆርጦ ውበትሽ ልክ የለው ባይኖቸ የማይሽ አደለም አፍጥጨ በፎቶ ሳይቀረኝ አልጠግብሽ መጥጨ የኔ እናት ነሽ አንቺ ዝቅ አትበይ በርቺ ሀዘንሽን ተፋቺ ጠሎትሽን ደብቺ ከሳቄ ቀንሶ ለሳቅሽ ይገበር ከድሜየ ጨምሮ ለእድሜሽ ይጨመር ይጨመር ይጨመር አሁንም ይጨመር እግሬ መዳፍ ይሁን ባጭሩ ይቀንጨር ላንቺ ብቻ ልኑር እናቴ እናቴ ሁልጊዜ ልበልሽ እንባሽን ጠርጌ በሳቅ ላብስልሽ በልቤ አትሜ ዘወትር ላኑርሽ እናቴ እናቴ እሱ ይጠብቅሽ እናቴ❤❤❤❤ ✍🏾ሀሊድ

አግብተሻል ወይስ አላገባሽም አግብተሽ ከሆነም ደግ ካልሆነም ይጠቅምሻልና እነዚህን ሶስት ነጥቦች መቸም ቢሆን አትዘንጊያቸው፦ 1,ስለባልሽ ችግር መቼም ቢሆን ለባልሽ ቤተሰቦች አታማክሪ...ባብዛኛው እ
አግብተሻል ወይስ አላገባሽም አግብተሽ ከሆነም ደግ ካልሆነም ይጠቅምሻልና እነዚህን ሶስት ነጥቦች መቸም ቢሆን አትዘንጊያቸው1,ስለባልሽ ችግር መቼም ቢሆን ለባልሽ ቤተሰቦች አታማክሪ...ባብዛኛው እነሱ ከርሱ ጎን እንጂ ካንቺ ጎን አይቆሙም። 2,ባልሽ የሚረብሽሽ፣ የማያስደስትሽ፣ የሚበድልሽ ከሆነ ለቤተሰቦችሽ መቼም እንዳትነግሪያቸው...ምክንያቱም አንቺ ረስተሽው ህይወትሽን ስትቀጥይ እነሱ ይቅር አይሉትም። 3,የቤትሽን እና የትዳርሽን ጉዳይ በፍጡም ለሴት ጓደኛሽ አትንገሪ...አንቺ ትተሽው ስትሄጅ እርሷ እንደ ጤፍ ትዘራልሻለች Amharic_audio_book

እድሜ ይስጣት ለእሷ ሆኜ ቀርቻለሁ የህመም ጎተራ እረስቶኛል ዘመድ ከወጣሁ ቆየሁኝ ከሰውነት ተራ ያለማንገራገር ሞተች ቢሉኝ እንኳን ከንፍሮ ልዘግን እገባለሁ ድንኳን ስራዋን ለማያውቅ ነገሬ ቢመርም አርባዋን በልቼ... “ለአመቱ ያድርሰን!" ማለቴ አይቀርም በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያልተመሰረተ! ✍️ ሚኪ @ethiopianye

እንዴት ነው ነገሩ? #ኑረዲን_ኢሳ እንዴት ነው ነገሩ? ብንሄድ ብንሄድ ጎዳናው አያልቅም ፣ ሽቅብ ብናንጋጥጥ ጀንበር አትጠልቅም ፣ ጊዜ ቆሟል መሰል አይነቃነቅም ፣ ጋሪያችን ይሮጣል እኛ አንንፏቀቅም ። እንዴት ነው ነገሩ? ዒሻራ 📚 27 - 1 - 95 ዓ.ም

አንዱ ለአገሩ ፤ አንዱ ለ'ርስቱ ፤ አንዱ ለልጁ ፤ አንዱ ለሚስቱ ፤ ጥይት ወልውሎ ፤ ጎራዴ ስሎ ፤ በዱር በገደል ይከታከታል ፤ ሲሻው ይገድላል ፤ ሲሻው ይሞታል ። እኔ ግን ወዲህ . . . ወይ አ
አንዱ ለአገሩ ፤ አንዱ ለ'ርስቱ ፤ አንዱ ለልጁ ፤ አንዱ ለሚስቱ ፤ ጥይት ወልውሎ ፤ ጎራዴ ስሎ ፤ በዱር በገደል ይከታከታል ፤ ሲሻው ይገድላል ፤ ሲሻው ይሞታል ። እኔ ግን ወዲህ . . . ወይ አገር የለኝ ፤ ወይ ርስት የለኝ ፤ ወይ ልጅ አልወለድኩ ፤ ሚስት አላደለኝ ፤ ጎራዴ ሳልስል ፤ ጥይት ሳልገዛ ፤ በተኛሁበት ሀሳብ ገደለኝ ። #ቴውድሮስ_ካሳ

ሁለት ልጃገረዶች (©አዳም ረታ)
ከ'ከሰማይ የወረደ ፍርፍር '
ቅዳሜ ቅዳሜ ማታ በዙረቴ የማልደርስበት የከተማችን ክፍል የለም ። ሳምንት ወይ አስራ አምስት ቀን ሙሉ ከቤት ሳልወጣ እቆይና እመሽግና አንድ ቅዳሜ መርጬ ከወጣሁ ግን የምመለሰው ተበለሻሽቼ ነው ። በደንቤ ሳምንት ሁለት ሳምንት ሙሉ ከቤት አልወጣም ....... ከእሁድ እስከ ዓርብ ። ብዙ ጊዜ ቅዳሜ ግን ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ጀምሮ እግሮቼ የማያርፉበት የከተማዋ ክፍል የለም። ከፒያሳ በሜክሲኮ አደባባይ አድርጎ ቄራ። በፒያሳ በሐብተጊዮርጊስ ድልድይ አድርጎ በመርካቶ በሰባተኛ እስከ ልደታ። እንደ አውሬ ነው የሚያደርገኝ። በዚያን ዕለት የማውቀውን ማንንም ሰው መገናኘት አልፈልግም ። በሕይወቴ ወጥ ውስጥ ትንንሽ የእብደት ቅርንፉድ የልክስክስነት ኮረሪማ የባለጌነት ነጭ ሽንኩርት የደደብነት ጥቁር አዝሙድ ...... የመሳሰለ ልጭምርባት እፈልጋለሁ ። እነዚህ ቅመሞች ያሉበትን ሐጢያታዊ ማታና ምሽት ከሰዎች ጋር ልኖራት ግን አልፈልግም ። ይኽቺን አይነት እብደት ከሚያውቁት ሰው ጋር ሆነው ሲሰሯት ትቀጥናለች ። ትዕዝብት ፣ ትችት ፣ 'ይቅርብህ' 'ጥሩ አይደለም' 'ይደብራል' የተሰኙ ቃላቶችና የሚከስቱዋቸው ስሜቶች ይወረወሩብኛል ። በቂ ነፃነት የለውም ። ያቺ የእብደት ቀኔ የፍፁም ነፃነት ቀኔ ናት። አዲስአባ . . . የቅዳሜ አዲስአባ የእኔ ጦሮ ሜዳ ናት ። ፊታውራሪ እኔ ፣ ተራ ወታደሩ እኔ ። አዛዥ እኔ ነኝ ታዛዥ እኔ ። የግሌም ካርኒቫል ነው። @ethiopianye

መፍትሔ በር መስኮት ዘግተህ ፣ ቀዳዳዎች ደፍነህ ፣ የለኮስከው ሻማ "በራ !" ፣ "ጠፋ!" ካለ ፤ ጠርጥር ! ቤት ያፈራው ንፋስ ከጎጆህ እንዳለ ?
©በረከት በላይነህ
@ethiopianye

ወርቅ እና ዝምታ ዝምታ ወርቅ ነው የምትሉት ፈሊጥ ውዳሴ አላዋቂ ከሊቅ እስከ ደቂቅ አርምሞን ለማድቀቅ የምታቦኩት ሊጥ ኩፍ ብሎላቹ በአፋቹ ሰፌድ ተጋግሮ የወጣው የታል  እንጀራቹ    #ብሩህ @ethiopianye

ጥርሷ ሰዋሪ ሳቋ ነዳፊ ፤ ከንፈሯ ገዳይ ዐይኗ ገራፊ ፤   ፀጉሯ ሐመልማል ልብሷ ደመና ፤ ገላዋ አበባ ቃናዋ ናና ፤   ልክ እንደ ሰንደል ልክ እንደ ብርጉድ ፤ የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !   ከሰማይ በቀር የምድር አፈር የማይመጥናት ፤ ከመለዓክ በቀር በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤   ልጅማ ልጅ ናት !   ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤ የሚገድሉላት የሚሞቱላት ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤   ልጅማ ልጅ ናት !   ሲሻት በምድር ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤ ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤   እንኳን ለአዘቦት ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤ እንኳን በፀሐይ ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤ ልጅማ ልጅ ናት ! እንኳን ቁሞ ሃጅ ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤ እንኳን የሰው ዘር ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤ ከፍቅር በቀር ሌላ አይችላትም ፤ ከራሷ በቀር የቱም አበባ አይመጥናትም ፤ የምድር ዕንቁ ናት የምድር አበባ ፤ እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤ እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤ በዐይኖቿ ብቻ ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤ ለባህር ዛጎል ለሰማይ ኮኮብ ለምድር አደይ ናት ፤ እንኳንስ ቁሜ ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤   ልጅማ ልጅ ናት ከአንድ እኔ በቀር ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ። ቴዎድሮስ ካሳ @ethiopianye

በምን ይገለጻል፥ የትውልዴ አበሣ ከመንበርከክ ብዛት ፥ መራመድ የረሣ ያልፋል ተለጉሞ ያልፋል ተከርችሞ የጉልበቱን ኮቴ፥ ምድር ላይ አትሞ። #ብሩህ @ethiopianye

ቲማቲም ወርውሮ ትናንትና አንድ ሰው አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው ደነገጥኩ አይቼ ሲዠቀዠቅ ደሙ በጣሳ ውስጥ ነበር ለካስ ቲማቲሙ። #ብሩህ @ethiopianye

ካየኽኝ                     ብሩህ ዓለም ***** ላይሰናስል ሳዳውር፤ ላይጠረቃ ሳጋብስ፤ አለሁ እንዳጋሰስ። ላይከትም ከአቦል ጀምሬ፣ በረካ አልባ ቡን ሳንቃርር፣ የማይፈፀም ሩጫ ገጥሜ፣ በባእዳን ውርጭ ጠይሜ፣ ስኳትን ቅስሜን ቀልሜ “ቃል” ላይወጣኝ ተለጉሜ፣ “ኖሯል” ካሉ ፥ ይኸው አለሁ። የቅኔ ቆሌዬ በኖ፤ ዲዳነት ቋንቋዬ ሆኖ፤ ደስታ ጣእሙ ጠፍቶ፤ በአልጫ ኑሮ ተተክቶ፤ ከተማ ሳለሁ ድብርት፤ ከአሸን መሃል ብቸኝነት፤ ምን ትል ይሆን የኔ አባት! ያየህ እንደው ድንገት ተዚ እዛ ስቧከት።                 #ብሩህ @ethiopianye

እናቴ 🥰 . . . ቢጨላልም ንጋት ቀኗ፤ ሲደካክም ወገብ ጎኗ፤ ማጀት ቤቷ ቢጎድልባት፤ ስቃይ ችግር ቢደቁሳት፤ በሀዘን ጊዜ በደስታዋ፤ አይከደን ሁሌም ጥርስዋ፤ ብትከፋ ምን ቢያደማት፤ ፈገግታ ነዉ የሚቀድማት። ...................................... በዔደን ታደሰ @ediwub @topazionnn @topazionnn @ethiopianye

የታቦር ደብር                      ብሩህ ዓለም *** ክርስቶስን መኖር ሊታዘብ ተገኝ ያረገው ኤልያስ፣ #ያምላክን ፊት ጉጉት ሙሴንም ጎትቶ ጀርባውን ሊያሳየው አነቃው ከመንፈስ። ይህ ደብረ ታቦር ነው፣ ሊመሰክር ሲዋጅ አምላክ ሲል ልጄ ነው። ዘመናችን የት ነው መቼ ነው መንቂያችን፣ ሺ ታቦር አለፈ ነውራችን በሀላል እየለፈለፈ። #ብሩህ_ዓለም @ethiopianye