የኛ ግጥም 😍😄❤🥰🥺
Open in Telegram
እንኳን ደና መጡ🙏 በዚህ ቻናል #ግጥሞች #ቀልዶች እንዲሁም ሀገርኛ ወጎችን አዝናኝ መረጃዎችን በለዛ እናገኛለን ለማንኛውም አስተያየት እንዲሁም ስራዎን ማቅረብ ከፈለጉ ወይም cross ከፈለጉ በዚህ ያናግሩኝ 👉 @berii34 እዚህ ለይ ደሞ👇 @ethiopianye👈join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ for any comment👉 @berii34
Show more1 919
Subscribers
No data24 hours
+47 days
-1230 days
Posts Archive
1 919
አለቀለት ያሉት
(በእውቀቱ ስዩም)
ከጅረት አጠገብ ፥ቆሞ የኖረ ዛፍ
መብረቅ ገነደሰው
አሁን ድልድይ ሁኖ፥ ያሸጋግራል ሰው ::
“አለቀለት” ያሉት፤ ተልኮው መች አልቆ
ቆሞ የጠቀመ፥ መላ አያጣም ወድቆ፤
@ethiopianye
1 919
Repost from የሳተር..🧘🏽♂
ናፍቆቴ
እናቴ አንቺ የኔ ኩራት
እናቴ....
የፍቅር ማሰሮ
እናቴ ልበልሽ የናፍቆት እሮሮ
ትዝይለኛል ያኔ
ጠረንሽ ሲገባ ባፍንጫየ ዘልቆ
አሁን ይሸተኛል ከጎኔ እርቆ
እናቴ ልበልሽ
መጠሪያ ባይኖርሽ
ናፍቆትሽ ይበቃል ከጉያሽ መዋሉ
እኔን ይጎደኛል ፈገግታሽ መጉደሉ
ትዝ ይለኛል ሳቅሽ
ጭንቀት ተሸክሞ ሀዘን ተጫጭኖት
ያላወኩት ነገር በሀሳብ አፍኖት
ትዝ ይለኛል አይንሽ
በስስት እያየኝ ሳይነቀል ላፍታ
ሰቅሎ ሲክበኝ ከላዩ ከፍታ
የኔ የኔ ብየ ዜማ አላወጣው
ለምን እንዳትይኝ
አንዴ ልበልሽ እኔ ወድሻለው
አዚህ ተቀምጨ ሳቅሽን አሸታለው
ጠረንሽ ልዩ ነው
አስከዛሬ ስኖር ሁኘ በምድር ላይ
ካንቺ የምትበልጥ አሎጣችም ፀሀይ
እውነት ከምሬ ነው
ጨረቃ ብትወጣ ብርሀን ብትሰጠኝ
ከሳቅሽ አውጥታ መቸ ልትሰደኝ
እኔ ወድሻለሁ
እናፍቅሻለሁ
እጠብቅሻለሁ
ባካል ብንራራቅ ድምፅሽ ይሰማኛል
ለሊት አስነስቶ በብርድ ያሞቀኛል
ከምበላው ምግብ ከውሀ አብልጦ
እንባሽን ማየቱ ይጥለኛል ቆርጦ
ውበትሽ ልክ የለው
ባይኖቸ የማይሽ አደለም አፍጥጨ
በፎቶ ሳይቀረኝ አልጠግብሽ መጥጨ
የኔ እናት ነሽ አንቺ
ዝቅ አትበይ በርቺ
ሀዘንሽን ተፋቺ
ጠሎትሽን ደብቺ
ከሳቄ ቀንሶ ለሳቅሽ ይገበር
ከድሜየ ጨምሮ ለእድሜሽ ይጨመር
ይጨመር ይጨመር አሁንም ይጨመር
እግሬ መዳፍ ይሁን ባጭሩ ይቀንጨር
ላንቺ ብቻ ልኑር
እናቴ እናቴ ሁልጊዜ ልበልሽ
እንባሽን ጠርጌ በሳቅ ላብስልሽ
በልቤ አትሜ ዘወትር ላኑርሽ
እናቴ እናቴ እሱ ይጠብቅሽ
እናቴ❤❤❤❤
✍🏾ሀሊድ
1 919
Repost from የሳተር..🧘🏽♂
አግብተሻል ወይስ አላገባሽም አግብተሽ ከሆነም ደግ ካልሆነም ይጠቅምሻልና እነዚህን ሶስት ነጥቦች መቸም ቢሆን አትዘንጊያቸው፦
1,ስለባልሽ ችግር መቼም ቢሆን ለባልሽ ቤተሰቦች አታማክሪ...ባብዛኛው እነሱ ከርሱ ጎን እንጂ ካንቺ ጎን አይቆሙም።
2,ባልሽ የሚረብሽሽ፣ የማያስደስትሽ፣ የሚበድልሽ ከሆነ ለቤተሰቦችሽ መቼም እንዳትነግሪያቸው...ምክንያቱም አንቺ ረስተሽው ህይወትሽን ስትቀጥይ እነሱ ይቅር አይሉትም።
3,የቤትሽን እና የትዳርሽን ጉዳይ በፍጡም ለሴት ጓደኛሽ አትንገሪ...አንቺ ትተሽው ስትሄጅ እርሷ እንደ ጤፍ ትዘራልሻለች
Amharic_audio_book1 919
እድሜ ይስጣት ለእሷ
ሆኜ ቀርቻለሁ የህመም ጎተራ
እረስቶኛል ዘመድ
ከወጣሁ ቆየሁኝ ከሰውነት ተራ
ያለማንገራገር ሞተች ቢሉኝ እንኳን
ከንፍሮ ልዘግን እገባለሁ ድንኳን
ስራዋን ለማያውቅ ነገሬ ቢመርም
አርባዋን በልቼ...
“ለአመቱ ያድርሰን!" ማለቴ አይቀርም
በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያልተመሰረተ!
✍️ ሚኪ
@ethiopianye
1 919
እንዴት ነው ነገሩ?
#ኑረዲን_ኢሳ
እንዴት ነው ነገሩ?
ብንሄድ ብንሄድ ጎዳናው አያልቅም ፣
ሽቅብ ብናንጋጥጥ ጀንበር አትጠልቅም ፣
ጊዜ ቆሟል መሰል አይነቃነቅም ፣
ጋሪያችን ይሮጣል እኛ አንንፏቀቅም ።
እንዴት ነው ነገሩ?
ዒሻራ 📚
27 - 1 - 95 ዓ.ም
1 919
አንዱ ለአገሩ ፤
አንዱ ለ'ርስቱ ፤
አንዱ ለልጁ ፤
አንዱ ለሚስቱ ፤
ጥይት ወልውሎ ፤ ጎራዴ ስሎ ፤
በዱር በገደል ይከታከታል ፤
ሲሻው ይገድላል ፤
ሲሻው ይሞታል ።
እኔ ግን ወዲህ . . .
ወይ አገር የለኝ ፤
ወይ ርስት የለኝ ፤
ወይ ልጅ አልወለድኩ ፤ ሚስት አላደለኝ ፤
ጎራዴ ሳልስል ፤ ጥይት ሳልገዛ ፤ በተኛሁበት ሀሳብ ገደለኝ ።
#ቴውድሮስ_ካሳ
1 919
ሁለት ልጃገረዶች
(©አዳም ረታ)
ከ'ከሰማይ የወረደ ፍርፍር 'ቅዳሜ ቅዳሜ ማታ በዙረቴ የማልደርስበት የከተማችን ክፍል የለም ። ሳምንት ወይ አስራ አምስት ቀን ሙሉ ከቤት ሳልወጣ እቆይና እመሽግና አንድ ቅዳሜ መርጬ ከወጣሁ ግን የምመለሰው ተበለሻሽቼ ነው ። በደንቤ ሳምንት ሁለት ሳምንት ሙሉ ከቤት አልወጣም ....... ከእሁድ እስከ ዓርብ ። ብዙ ጊዜ ቅዳሜ ግን ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ጀምሮ እግሮቼ የማያርፉበት የከተማዋ ክፍል የለም። ከፒያሳ በሜክሲኮ አደባባይ አድርጎ ቄራ። በፒያሳ በሐብተጊዮርጊስ ድልድይ አድርጎ በመርካቶ በሰባተኛ እስከ ልደታ። እንደ አውሬ ነው የሚያደርገኝ። በዚያን ዕለት የማውቀውን ማንንም ሰው መገናኘት አልፈልግም ። በሕይወቴ ወጥ ውስጥ ትንንሽ የእብደት ቅርንፉድ የልክስክስነት ኮረሪማ የባለጌነት ነጭ ሽንኩርት የደደብነት ጥቁር አዝሙድ ...... የመሳሰለ ልጭምርባት እፈልጋለሁ ። እነዚህ ቅመሞች ያሉበትን ሐጢያታዊ ማታና ምሽት ከሰዎች ጋር ልኖራት ግን አልፈልግም ። ይኽቺን አይነት እብደት ከሚያውቁት ሰው ጋር ሆነው ሲሰሯት ትቀጥናለች ። ትዕዝብት ፣ ትችት ፣ 'ይቅርብህ' 'ጥሩ አይደለም' 'ይደብራል' የተሰኙ ቃላቶችና የሚከስቱዋቸው ስሜቶች ይወረወሩብኛል ። በቂ ነፃነት የለውም ። ያቺ የእብደት ቀኔ የፍፁም ነፃነት ቀኔ ናት። አዲስአባ . . . የቅዳሜ አዲስአባ የእኔ ጦሮ ሜዳ ናት ። ፊታውራሪ እኔ ፣ ተራ ወታደሩ እኔ ። አዛዥ እኔ ነኝ ታዛዥ እኔ ። የግሌም ካርኒቫል ነው። @ethiopianye
1 919
መፍትሔ
በር መስኮት ዘግተህ ፣
ቀዳዳዎች ደፍነህ ፣
የለኮስከው ሻማ "በራ !" ፣ "ጠፋ!" ካለ ፤
ጠርጥር !
ቤት ያፈራው ንፋስ ከጎጆህ እንዳለ ?
©በረከት በላይነህ@ethiopianye
1 919
ወርቅ እና ዝምታ
ዝምታ ወርቅ ነው
የምትሉት ፈሊጥ
ውዳሴ አላዋቂ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ
አርምሞን ለማድቀቅ
የምታቦኩት ሊጥ
ኩፍ ብሎላቹ
በአፋቹ ሰፌድ
ተጋግሮ የወጣው
የታል እንጀራቹ
#ብሩህ
@ethiopianye
1 919
ጥርሷ ሰዋሪ
ሳቋ ነዳፊ ፤
ከንፈሯ ገዳይ
ዐይኗ ገራፊ ፤
ፀጉሯ ሐመልማል
ልብሷ ደመና ፤
ገላዋ አበባ
ቃናዋ ናና ፤
ልክ እንደ ሰንደል
ልክ እንደ ብርጉድ ፤
የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !
ከሰማይ በቀር
የምድር አፈር የማይመጥናት ፤
ከመለዓክ በቀር
በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት
አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤
የሚገድሉላት
የሚሞቱላት
ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ሲሻት በምድር
ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤
ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤
እንኳን ለአዘቦት
ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤
እንኳን በፀሐይ
ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
እንኳን ቁሞ ሃጅ
ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤
እንኳን የሰው ዘር
ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤
ከፍቅር በቀር
ሌላ አይችላትም ፤
ከራሷ በቀር
የቱም አበባ አይመጥናትም ፤
የምድር ዕንቁ ናት
የምድር አበባ ፤
እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤
እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤
በዐይኖቿ ብቻ
ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤
ለባህር ዛጎል
ለሰማይ ኮኮብ
ለምድር አደይ ናት ፤
እንኳንስ ቁሜ
ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት
ከአንድ እኔ በቀር
ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ።
ቴዎድሮስ ካሳ
@ethiopianye
1 919
በምን ይገለጻል፥
የትውልዴ አበሣ
ከመንበርከክ ብዛት ፥
መራመድ የረሣ
ያልፋል ተለጉሞ
ያልፋል ተከርችሞ
የጉልበቱን ኮቴ፥
ምድር ላይ አትሞ።
#ብሩህ
@ethiopianye
1 919
ቲማቲም ወርውሮ
ትናንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን
ግንባሩን ገመሰው
ደነገጥኩ አይቼ
ሲዠቀዠቅ ደሙ
በጣሳ ውስጥ ነበር
ለካስ ቲማቲሙ።
#ብሩህ
@ethiopianye
1 919
ካየኽኝ
ብሩህ ዓለም
*****
ላይሰናስል ሳዳውር፤
ላይጠረቃ ሳጋብስ፤
አለሁ እንዳጋሰስ።
ላይከትም ከአቦል ጀምሬ፣
በረካ አልባ ቡን ሳንቃርር፣
የማይፈፀም ሩጫ ገጥሜ፣
በባእዳን ውርጭ ጠይሜ፣
ስኳትን ቅስሜን ቀልሜ
“ቃል” ላይወጣኝ ተለጉሜ፣
“ኖሯል” ካሉ ፥ ይኸው አለሁ።
የቅኔ ቆሌዬ በኖ፤
ዲዳነት ቋንቋዬ ሆኖ፤
ደስታ ጣእሙ ጠፍቶ፤
በአልጫ ኑሮ ተተክቶ፤
ከተማ ሳለሁ ድብርት፤
ከአሸን መሃል ብቸኝነት፤
ምን ትል ይሆን የኔ አባት!
ያየህ እንደው ድንገት
ተዚ እዛ ስቧከት።
#ብሩህ
@ethiopianye
1 919
እናቴ 🥰
.
.
.
ቢጨላልም ንጋት ቀኗ፤
ሲደካክም ወገብ ጎኗ፤
ማጀት ቤቷ ቢጎድልባት፤
ስቃይ ችግር ቢደቁሳት፤
በሀዘን ጊዜ በደስታዋ፤
አይከደን ሁሌም ጥርስዋ፤
ብትከፋ ምን ቢያደማት፤
ፈገግታ ነዉ የሚቀድማት።
......................................
በዔደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn
@ethiopianye
1 919
የታቦር ደብር
ብሩህ ዓለም
***
ክርስቶስን መኖር
ሊታዘብ ተገኝ
ያረገው ኤልያስ፣
#ያምላክን ፊት ጉጉት
ሙሴንም ጎትቶ
ጀርባውን ሊያሳየው
አነቃው ከመንፈስ።
ይህ ደብረ ታቦር ነው፣
ሊመሰክር ሲዋጅ
አምላክ ሲል ልጄ ነው።
ዘመናችን የት ነው
መቼ ነው መንቂያችን፣
ሺ ታቦር አለፈ
ነውራችን በሀላል እየለፈለፈ።
#ብሩህ_ዓለም
@ethiopianye
