የሳተር..🧘🏽♂
Open in Telegram
657
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-230 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
July '26
July '26
+2
in 0 channels
June '26
+7
in 0 channels
Get PRO
May '26
+7
in 0 channels
Get PRO
April '26
+5
in 0 channels
Get PRO
March '26
+10
in 0 channels
Get PRO
February '26
+8
in 0 channels
Get PRO
January '26
+13
in 1 channels
Get PRO
December '25
+10
in 0 channels
Get PRO
November '25
+80
in 0 channels
Get PRO
October '25
+240
in 10 channels
Get PRO
September '25
+114
in 5 channels
Get PRO
August '25
+136
in 3 channels
Get PRO
July '25
+155
in 9 channels
Get PRO
June '25
+250
in 0 channels
Get PRO
May '250
in 3 channels
Get PRO
April '25
+67
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 13 July | 0 | |||
| 12 July | +2 | |||
| 11 July | 0 | |||
| 10 July | 0 | |||
| 09 July | 0 | |||
| 08 July | 0 | |||
| 07 July | 0 | |||
| 06 July | 0 | |||
| 05 July | 0 | |||
| 04 July | 0 | |||
| 03 July | 0 | |||
| 02 July | 0 | |||
| 01 July | 0 |
Channel Posts
Track 16
👤 ቴዲ አፍሮ
🗣 መርከብ
መርከብ የመሀለቁ ጫፍ ባይሰራ
ረግቶ እንዳይቆም ሁሉ ከአንድ ስፍራ
ቃልሽ ሆነና ቦታው ማይገኝ
ተላላ አረገው ልቤን ሰው አማኝ
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
እ . . . እ. . .
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
መርከብ የመሀለቁ ጫፍ ባይሰራ
ረግቶ እንዳይቆም ሁሉ ከአንድ ስፍራ
ቃልሽ ሆነና ቦታው ማይገኝ
ተላላ አረገው ልቤን ሰው አማኝ
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
እ . . . እ. . .
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
.............ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ ምን አለ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ...... ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
🫶
| 2 | Track 16
👤 ቴዲ አፍሮ
🗣 መርከብ
መርከብ የመሀለቁ ጫፍ ባይሰራ
ረግቶ እንዳይቆም ሁሉ ከአንድ ስፍራ
ቃልሽ ሆነና ቦታው ማይገኝ
ተላላ አረገው ልቤን ሰው አማኝ
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
እ . . . እ. . .
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
መርከብ የመሀለቁ ጫፍ ባይሰራ
ረግቶ እንዳይቆም ሁሉ ከአንድ ስፍራ
ቃልሽ ሆነና ቦታው ማይገኝ
ተላላ አረገው ልቤን ሰው አማኝ
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ቦይ ብቀድለት
እምባዬ ፈሶም አይበቃው
ወፍ ጭጭጭ እስኪል
ቆሜ ነው ሌቱን ማነጋው
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
ከየት ልዋስ ያኔ ከየት ፅናት
ሲመሌዲዴ አላኖር ሲለኝ ስጋት
እ . . . እ. . .
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ምስኪኑ ልቤ ባንቺ ታምኖ
ባንቺ ታምኖ ሳይበቃው
ብለሻል አሉ ትቼዋለሁ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ ምን አለ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
ጆሮ
ጆሮ ምን አለ ማይሰማው
🫶 | 1 |
| 3 | ነፃ_ስሜቶች
ያልተገደበ ሀሳብ ገደብ ከሌለው የሰው እውቀት እየተመዘዘ ለናንተ ልሰጥ የከፈትኩት ቻናል ነው
አላማ አርጌ የተነሳውት ትንሽ_እንወቅ ነው
ብዙ ለመገንዘብ ትንንሽ እውቀቶችን ከየቦታው እየለቀምኩ ከራሴም የግል እውቀትና ከሌሎች ቦታ የቃረምኳቸውን ወደ ፅሑፍ በመለወጥ እያጋራው ነው
የምቶዱት ይሆናል ኑና ትንንሽ እውቀቶችን በጋራ በመሰብሰብ ለትልቅ መገለጥ እንድረስ
#ትንሽ_አውቃለው ለሚል ማንኛውም ሰው ቤትኛውም ዘርፍ ያለውን እውቀት እንዲያጋራ admin የምሰጥ ነኝ
ነፃ ስሜት መድረክ ትንሽ እንወቅ
https://t.me/Ewuket_bet | 182 |
| 4 | አንበሳው ተኛ እንጂ አልሞተም!
የልፋታችን ፍሬ 'ሩቅ ነው! ምኞታችን 'ሩቅ ቢሆን እንኳን በየጊዜው የሚቀያየር ግን ጥኑ ፍላጎት የጠናበት..... እድላቹህ ጠማማ ነው ተብለናል ወይም እውን እድላችን ጠማማ ነው። ይሁን ይጣመም። ልፋታችን ከምኞታችን ተጣምሮ ቤቱን እስኪሰራ መቼም አናቆምም። እመኑኝ የተጣመመውን እድላችን በልፋታችን ይቃናል። እመኑኝ ያ ቀን ይመጣል። ከፍ ብለን እንበራለን... እለፋለሁ ወጥሬ ያለኝን አቅም አፍስሼ እጣፈንታየን እንቀይረዋለሁ! እድል የሚባለው ተራ ነገር መሆኑን እናሳያለን! የተበላሸውን ዛሬያችንን አስተካክለን ነጋችን ላይ እንነግስበታለን.... ላባችን ተንጠባጥቦ፣ ሰውነታችን ዝሎ፣ ደምስራችን ተውጠርጥሮም ሆነ ደማችን ፈሶ ዝቅ ሊያረጉን ቆርጠው የተነሱትን በስኬታችን እናስደነግጣቸዋለን... ወደኋላ መቅረታችንን አይተው ጅሎች ሲያረጉን በራሳችን ጊዜ እንወነጨፋለን... እስከዛ ግን አቅማችንን እዩልኝ እያልን አናባክነውም። ጊዜው ሲደርስ እድላችንን እንሰብረዋለን... እመኑኝ ሂወት እስከመጨረሻው ለሰነፎች የምትነግራቸው የኛን ጥንካሬ ይሆናል። አይናችንን ጨፉነን አለምን እንስላታለን፤ እድላችንን የምንጥፈው እኛ እንሆናለን፦.... no more እድል forever ልፋታችን Finally, it will be revealed. | 498 |
| 5 | No text... | 288 |
| 6 | አዋጅ አዋጅ
የቻናል ባለቤቶች በሙሉ የቻናላቹህን ፕሮፋይል (logo) በማጥፋት ቻናላቹህን ከመሰረቅ አትርፉት....
አሉ ባልታ ብላቹህ አትለፉ... እኔ ተናግሬያለሁ🤥 | 72 |
| 7 | ሰላሞ ውድ የመፅሐፍ ወዳጆች..
"አቶ"እኔ.. የተሰኘ ልብ ወለድን፣ እውነተኛ ታሪክንና ሳይኮሎጂን(ፍልስፍናን) አጣምሮ የያዘ መፅሐፍ ፅፌ አጠናቅቄያለሁ!
ይህን መፅሐፍ ለአንባቢያን ለማብቃት የምትኮሩበትን ተሳትፍ እንድታደርጉ እጠይቃለሁ።
1ሺህ ሰዎች 50, 50 ብር ቢያዋጡ ለማሳተም የጎደለው ብር ስለሚሞላ.. የመፅሐፍ ፍቅር ያላችሁ ፍቅራችሁን ግለፁልን ስል በመፅሐፍት ክብር እጠይቃለሁ🙏🙏።
ልታወሩኝ ከፈለጋችሁ @Mr_lewi
የቻናሌ link @lewi_derest
Acc 1000514171328
Telebirr 0944240243 | 219 |
| 8 | ሰላሞ ውድ የመፅሐፍ ወዳጆች..
"አቶ"እኔ.. የተሰኘ ልብ ወለድን፣ እውነተኛ ታሪክንና ሳይኮሎጂን(ፍልስፍናን) አጣምሮ የያዘ መፅሐፍ ፅፌ አጠናቅቄያለሁ!
ይህን መፅሐፍ ለአንባቢያን ለማብቃት የምትኮሩበትን ተሳትፍ እንድታደርጉ እጠይቃለሁ።
1ሺህ ሰዎች 50, 50 ብር ቢያዋጡ ለማሳተም የጎደለው ብር ስለሚሞላ.. የመፅሐፍ ፍቅር ያላችሁ ፍቅራችሁን ግለፁልን ስል በመፅሐፍት ክብር እጠይቃለሁ🙏🙏።
ልታወሩኝ ከፈለጋችሁ @Mr_lewi
የቻናሌ link @lewi_derest
Acc 1000514171328
Telebirr 0944240243 | 1 |
| 9 | #ዜና_እረፍት
ተወዳጁ አርቲስት #ነፃነት_ወርቅነህ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።😔 | 305 |
| 10 | መግቢያ መውጫ
(ሀሊድ...)
በግማደ ግርጌው 'ስር ጥቡቅ ሁና ተሸምቅቃ
ተጠፍንጋ ተሰድራ ተኮማትራ ተጠንግራ እያየሀት
ለምን ሸሸህ ለምን ተውካት?
ተጠየቃ የኛ አዳም ስንትዜ ነው የገደልካት
አንድ አድነህ ሁለት ገለህ የሰደድካት
አስር ስመህ ሀያ ሰድበህ ያዋረድካት
ተጠየቃ ሁሉን አዳምጥ ግን አትፍረድ
ጠንቀቅ ብለህ በዝምታ እሩቅ ተጓዝ እንደ ሰደድ
እናም አዳ እንዲህ እያልክ ተማጸነኝ
ተሳስቸ አትበል።በድያለሁ አጥፍቻለሁ ከእዝነትህ አትንፈገኝ
በንፁህ ልብ፡በተፈጥሮ፣በጀንበሯ አለምልመኝ
ሰብሬያለሁ፣አፍርሻለሁ እንድጠግን እድል ስጠኝ
ባልሰጥህም በል ጠይቀኝ
ye_satter | 421 |
| 11 | ችኩሏ ቤዛ
(ሀሊድ......)
ቤዛ! ስስ ልብ አላት፣ከሰው ጋር መግባባት ትወዳለች፣ከሰውም ብዙ ትጠብቃለች... የምትጠብቀው የሰው 'ርሀብ ስላለባት ነው። በሰወች ዝቅ መደረግና ችላ መባል ሆድ ያስብሳታል። መጥፎ ባህሪዋ ደግሞ ችኩልነቷ ነው። ቤዛ ሲበዛ ችኩል ናት፣ብዙ ስህተቶችን በችኮላ ብትሰራም መጥፎውና ከባዱ ግን በእለተ ሀሙስ ቀን የተፈጠረው ክስተት ነበር።
እለተ ሀሙስ
በእለተ ሀሙስ አንድ አሜሪካ ውስጥ በምቾትና በተድላ የምትኖር የነ-ቤዛ ጓደኛ ዝምታዋን ከመስበሯ በተጨማሪ ስጦታ በቪትስ መኪና አጠራቅማ ላከች፣ ስጦታውን የያዘው መኪና ሰፈር ውስጥ ሁነኛ ቦታ ላይ ቁሟል። ቤዛ እና የቤዛ ጓደኞች በሙሉ በቅጥበታት መሀከል ቪትስ መኪናዋን እንደ ጉድ ከበዋት ቆሙ፣ መኪናዋን የሚሾፍራት ጠንበርበር ያለ ጠብደል ከውጭ ቁሞ በየተራ ስማቸውን በመጥራት ስጦታውን ያድላቸው ጀመር።
"ሜሮን! ሳባ! ኢክራም!..." የመኪናው ሹፌር ከያዘው ወረቀት ላይ የተነሸጠውን ስም እየጠራ በአብረቅራቂ ላፒስ የተሽሞነሞነውን ጥቅል ያድላቸው ጀመረ። በዚህ መሀል ቤዛ! ተራዋ አልደርስሽ አላት... ሌሎች ጓደኞቿ እየተጠሩ ስጦታቸውን ሲወስዱ ቤዛ ግን፦ "እህህ! ቆይ እኔ ከሁሎቹም በላይ ውድ ጓደኛዋ አልነበርኩምን? ታድያ ለኔ መጀመሪያ እንደመስጠት መጨረሻ!..." እያለች ማማረር ጀመረች፣ይህም አልሆነ፣ የስጦታ ጥቅሎች ሁለት ብቻ ቀሩ፣ ቤዛ ግን ስሟ አልተጠራም።
ወደ ሹፌሩ ጠጋ አለችና ከዝርዝሩ ላይ ስሟን አየችው... ደነገጠች! ጭራሹን ስሟ ከዝርዝሩ ላይ አልነበረም። 'ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለ እዳ አይቀበለውም...' ብላ ሹፌሩ ላይ አላቅራራችም። በጓደኛዋ ስራ እያፈረች መጨረሻ ላይ ሳትሰጥ ስትቀር ጓደኞቿ እንዳያሸማቅቋት በመስጋት ቦታውን ለቃ ተፈተለከች... ቤቷ ገብታ እሪ፣ እንቧ አለች፣ በዚህ ስሜት ውስጦ ሁና ለጓደኛው እንዳዘነቺባትና፡ እንደጠላቻት፣ የለለ ነገር እየፈጠረች የለለ ጥላቻዋን የሚገልጥ መልዕክት በስልኳ ላከችላት፣
አይ ችኩሏ ቤዛ! የስጦታ ጥቅሎች ላይ አይኗን ስታተራምስ የስጦታ ጥቅሎችን የያዘውን ቪትስ መኪና ዘነጋችው፡ ያ! ግርማ ሞገስ ያለው መኪና ለችኩሏ ቤዛ ታዞ ነበረ። ሹፌሩ ጥቅሎችን አራግፎ ከጨረሰ በኋላ መኪናውን ለቤዛ አስረክባታለሁ በሚል እሳቤ ቅድሚያ አልሰጣትም።,መጨረሻ ላይ ግን የስጦታ ጥቅሎችን አራግፎ መኪናውን ሊያስረክባት ቤዛን ብሎ ያማተረው አይኑ አላያት አለ።,ለአለቃው ደውሎ ቤቷ ሂዶ ሊሰጣት መሆኑን ሲነግራት ይህቺ አሜሪካዊ በቤዛ የችኮላ ንግግር ቆስላ ነበርና ዝም ብሎ እንዲመለስ አዘዘችው። በሂወት ውስጥ ክብርን የሚጋፋ ትዕግስን ሊኖረን ይገባል። ቤዛ ይህ መሳሪያ አልነበራትም።አይ ችኩሏ ቤዛ!
ye_satter | 376 |
| 12 | በጣም ይቅርታ ቤተሰብ🙏❤
(come back)
በአንዳንድ ፐርሰናል ጉዳዮች ምክንያት ለተከታታይ ቀናት ተሰውሬ ቆይቻለሁ.... ከይቅርታ ጋር ዛሬ እየተመለስኩ ተከታታይ ፁሁፋችንን እንደድሮው እንድንኮመኩም የድሮውን ተነሳሽነታቹህን እጠብቃለሁ....
መልካም ምሽት ቤተሰብ❤❤❤ | 317 |
| 13 | #ማን አየ?
#ክፍል_አስራ_ሁለት
ድብልቅልቁ ቢወጣም ሰላም ያየናል
"ምነው ፍቅሬ! ፎቶውን ከዚህ ቀደም አይተኸዋል?..."
"አይ አላየሁትም!..."
"ፊትህ ለምን ተቀየረ? ምን የሚያስደነግጥህ ነገር ተፈጠረና ፊትህን ትጥለዋለህ?..."
"ምን ያህል የእንባ ዶፎችን ምን ያህል መቀመቅና ሲቃ እንደሰጠሽ አውቃለሁ! ፊቱን ሳየው ደነገጥኩ! ይህ ሰው በህልሜ ይመጣል። መልዐክ ይመስለኝ ነበረ። እንደሱ መሆን ተመኝቸ ነበረ። ሁለ ነገሩ ይስበኝ ነበረ። ታድያ አንቺ ላይ ምን እንዳረገ ባላውቅ ኑሮ አሁንም ከፈጣሪ በላይ ሁኖ ይታየኝ ነበረ። ፎቶውን ሳይ እናም እጁ ላይ የስብራትሽ ነጠብጣብ ታትሞ ሳይ ህልሜ ተገለባብጦ የዋጠኝ መሰለኝ!...."
"እህ ታድያ በአካል አግኝተኸው ታውቃለህን?..."
"ኸረ በፍጡም! በአካል ባገኘውማ ይሄኔ ገድየው ወይ ገድሎኝ ከሁለት አንዳችን ፖሊስ ጣብያ እንማቅቅ ነበረ።..."
"ታድያ በህልም አለም አገኘኸው አደል? መቼ ገደልከው? መቼ ታሰርክ?..."
"የህልሜ ጌታ እኔ አደለሁም። መታሰሩን ከሆነ ሁሌም የፍቅርሽ እስረኛ ነኝ!..."አላትና ቢንያም እቅፍቅፍ አርጎ የፈጠረውን ቤት በክንዶቹ ቆለፈው። በዚሁ ቤት ውስጥ የሚሰማው ብቸኛው ነገር ዝምታ ነው። ሊሊ በሆዷ የያዘችው ህጻን ልጅ ቢንቀሳቀስም ድምጡ ክላሲካል እስኪፈጥር ድረስ!
ወራቶች ይሄዳሉ ግን ይህ ክንድ መቼም አይከፈትም። በክፍተቶች መሀል ሁሌም መቆለፍ አለ። ጠዋት ላይ የሚስረገረገው ሽንቁር ለስላሳዋን የፅሀይ ሞገድ ለማሳለፍ ብቻ ነው። ሁለት ልቦች አሉ እንዳሉ! ባለመኖራቸው ውስጥ መኖርን ይፈጥራሉ።
በመኖራቸው ውስጥ አለመኖርን ይፈራሉ። ሁሌም ግን መኖራቸው ይደበዝዛል። ይህ ሁላ ጊዜ ግን ከንቱ ይሆን ነበረ እነዛ ሁለት ልቦች በደብዛዛ ጭላንጭል ውስጥ እየተራመዱ ብርሀንን ማሰስ ባይችሉበት ኑሮ!
ያች ዱቃ አመድ የሆነችት ፎቶ ማን አየን ብዙ ነገሮች አስተማረችው። በውስጡ ያለውን ፍርሀት ተጠቅሞ የጥንቃቄ መረቦችን መዘርጋት ጀመረ። ወደ በሀርዳር መንደር አቅዶት የነበረውን ጉዞ ሰረዘ። አቶ ምስክር የተባለውን ገለፍተኛ የሰው ዘር እንደ ንስር ያድነው ጀመረ።
ቤቱ ዙሪያውን በጥበቃወች ተከበበ... ያንዳንዳንዷ የሳር ጫፍና ስር ጉልታ እስክትታይ ድረስ የተወጠነ ግዙፍ ካሜራ በቤቱ ዙርያ አስተከለ። ቢሮውም አልቀረም። ብዙ ጥንቃቄወችን አረገ። የሱ እቅድ ግን የሚስቱን ደህንነት መጠበቅ ብቻ ሳይሆን አቶ ተሰማን ማግኘት ነበረ።
ወና ፍለጋ ነበረ። ቀናቶች ሂደው ወራቶች አለፉ... አቶ ምስክር ብሎ ራሱን በመላእክ ስም ያስተዋወቀው አቶ ተሰማ ግን እስካሁን ዳናው አልተገኘም።
"አቶ ተሰማ ስኬቴን እንድጠላው አርጎኛል! እስከዛሬ በራሴ አቅም እዚህ ደረጃ ላይ የደረስኩ ይመስለኝ ነበረ። ነገር ግን አቶ ተሰማ እጁን አስገብቶበታል። በሊሊ ስምኮ ከዚህም የባሰ ብዙ መሬት እና ተቆጥሮ የማያልቅ ሀብት አለ። የኔ ሀብት በዚህ አይነት ኢምንት ነው። ግን አንጠቀመውም! ምክንያቱም የአቶ ተሰማ እጅ ነክቶታል። የኔ ሀብትም ባዳየ ነው።
አቶ ተሰማ ቁራሽ ባይሰጠኝ ኑሮ እዚህ አልደርስም ነበረ። ምንም አቅም የለኝም። ይህን ለሊሊ ብነግራት ዛሬውኑ ጎዳና በወጣች!..." ማንአየ በንዴት ጠረንጴዛውን በአንድጁ ነተረው። ሰብለ ከፊቱ ተቀምጣ በዝምታ ታዳምጠዋለች...
"ይህ ትክክል አደለም። ለፍተህ እና ላብህን አፍሰህ የሰራኸው ኑሮ ነው። በማይሆን ሀሳብ ራስህን አታስጨንቅ ቢኒየ!..."አለችው ሰብለ ከተቀመጠችበት እየተነሳች፣ወንበር አስጠግታ አጠገቡ ተቀመጠችና ትክሻውን እየዳበሰች ልታረጋጋው መሞከሯን ቀጠለች
ተቃቅፈው ባለበት ሰሀትም የቢንያም ውስጥ አመጥ በአመጥ ሁኖ ነበረ። ራሱን ማጥናናት የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ እየሰመጠ ነበረ። ከአንደበቱ የሚወጣው ቃል ተመሳሳይ ነው።
" ላገኘው ይገባል! በዙ ነገሮችን ላወራርድ ይገባኛል። በሊሊ ላይ ላረገው ነገርም ልጠይቀው ይገባል።..."
"አትገለውም አደል?...." ሰብለ ጠየቀቺው
"እኛ ኑረን እየተሰቃየን አደል! አሱ ቀድሞ ሙቷል። በራሱ ጊዜ ይሙት እንጂ እጄን አላስገባም።..."
"ሁለት ወር ጠበቅከው ግን አልመጣም። እሱ የሚመጣው ያኔ ነው የሚመጣበት ምክንያት ሲኖረው! አዲሁ ይመጣል ብሎ መጠበቅ ዘበት ነው።..."አለችው ሰብለ እጆቹን በሁለት እጆቿ ጥብቅ አርጋ እየያዘች
"ታድያ ምን እናርግ? ሰብሊ..."
"የሚመጣበት ምክንያት እንስጠው።..."እጆቹን ለቀቅ አርጋ ተነስታ እየተንጎራደደች"እስከዛሬ እንዳየሁት ከሆነ ወዳንተ የሚመጣበት ምክንያት ከራሱ አደለም። ሲመቸው ወይም ደስ ሲለው አደለም። የሆነ አደጋ ሲገጥምህ! ሊሊ ስትታመም ወይም የሆነ እርዳታ ሲያስፈልግህ በዚህ ወቅት ነው የሚገኝ! ማረግ ያለብንም ይህንኑ ነው።..."
ቢንያም በሰብለ ሀሳብ እየተደነቀ ከመቀመጫው ብድግ አለና"በሚገባ! ለማጣራት እንኳን ጊዜ የማያባክንበትን እየተንቀለቀለ የሚመጣበትን ምክንያት እሰጠዋለሁ!..."
"በላ ቢኒየ! ይመጣል ሳይሆን ለምን ይመጣል ማለታችን ብዙ ቁልፍ ነገሮችን ይፈታልናል። እና ምን ልታደርግ ነው?..."
"ለዚህ ቁልፍ የምትሆነኝ ሊሊ ናት! ዛሬ መረቤን እዘረጋለሁ.... በይ ተነሽ የምንሰራቸው ወሳኝ ስራወች አሉን!..."እጅ ለእጅ ተያይዘው በፍጥነት የቢሮውን በር አልፈው ሄዱ፡ሁኔታቸውን ማጤን የጀመረችው ገነት ጥላቸው እስኪሰወር ድረስ ትከታተላቸው ነበረ። እጇን አገጯ ላይ ጣል አርጋ በጉድ እየታዘበቻቸው ተመልሳ ወደ ማንአየ ቢሮ ገባችና ማን አየ መቀመጫ ላይ ተዘርራ ወደ ታች እየተንዠረገገች ማኪያቶ መጎንጨቷን ቀጠለች....
ይቀጥላል....
📎ሀሊድ | 501 |
| 14 | https://t.me/+r79M-j20Jt00MGVk | 123 |
| 15 | #ማን አየ?
#ክፍል_አስራ_አንድ
በዳይ የጤና መድን የሚቀበለው ከሞት ነው።
ማለዳ! ፀሀይዋ ሞቅ ሳትል እንደወረደ የሚንተገተገውን የሰማይ ንሪት እየሰነጠቀች ነጩን አዙሪት ነፃ ታወጣው ይመስል አስሬ እየተሽከረከረች ታሽኮረምመዋለች! ነጩ ግሽልጥ በተራው እየደመቀ በሄደ ቁጥር ፀሀይ ከተፈጥሮ ህግ እያፈነገጠች መሽኮርመም ትጀምራለች... ብቸኛው አማራጯ መጠንከር ቢሆንም ጊዜዋ አልደረሰምና ቁልቁል እየተብረከረከች የማዕዱን ጠርዝ ታስውበዋለች....
በረንዳ ላይ ግርማ ሞገስ የተላበሱ ቤተሰቦች ተሰይመዋል። የፀዋት ፀሀይ ልዩ ግርማ ሞገስ እየለገሰቻቸው በፈገግታ አከናንባቸዋለች.... ማን አየ በእንዲህ አይነት ሁኔታ ቁርስ ሲመገብ የመጀመሪያው ነው። ሰብለም ሆነች ሊሊ የመጀመሪያዋ ነው። ከቶ እንዲህ አይነት ቁርስ መቸ ተመግበው ያውቁና? ቢያውቁም እንኳን ይሄ የመጀመሪያቸው መሆኖ የማይፋቅ ሀቅ ነው።
"ውድ ቤተሰቦቸ!..."አለ ማን አየ በርግጥ ጠረንጴዛው ላይ ያሉት ሚስቱ እና ሰብለ፣ ሹፌሩ አሹ፣ የቤት ሰራተኛዋ የውብ ዳር... ቢሆኑም ቤተሰቦቸ ሲል ሁሉንም በእኩል መጥራቱ ነው።
"ይሄን እጅግ ውብ የሆነ ቁርስ ይበልጥ ውብ የሚያረግ ነገር ልነግራቹህ ነው! ከዚያ በፊት ግን...."ብሎ ቀጠለ ማን አየ!
"ተዋ! እንዲህ ያለ ማንጠልጠል አይሆንልኝም! መጀመሪያ መጥፎውን ዜና ቀጥለህ ጥሩውን ንገረን ቢያንስ! በላ...."አለው አሹ
"በቅድሚያ! በቅርቡ ወደ ባህር ዳር እንደምሄድ ልነግራቹህ እወዳለሁ!...."
"ምን አልክ ፍቅሬ!..."አለችው ሚስቱ
አሹም ቀበል አርጎ"ምን ትሰራለህ?...."
ሰብለ ብቻ ነው የገባት፣ ማን አየ ሚስቱን ጠቀስ አርጎ ዝም አስባላት፣ ወደ አሹ ዞር አለና" ድሮ የጀመርኳቸው ያልጨረስኳቸው ስራወች አሉኝ! ስድስተኛ ቅርንጫፍ ባህር ዳር ውስጥ ላቋቁም አስቤያለሁ!..."
"የስራ ጉዳይ ከሆነማ ማን ያስቆምሀል! ባይሆን ጣና ሀይቅን ለመጀመሪያ ጊዜ የመጎብኘት እድል አገኘሁ!..."አለው አሹ! በጥልቅ መሻት ውስጥ ሁኖ... አሹና ማን አየ የተገናኙት ከስምንት አመት በፊት ነበረ። በወቅቱ ማን አየ ከሚስቱ ጋር በኮረኮንች መንገድ ወክ እያረጉ ነበረ። በዚህ ቅጥበት ከየት መጡ ሳይባል የሰፈር አውደልዳይ ጨንጓራወች አስቁመው ሊዘርፏቸው ይረባረቡ ጀመር።
አንዱ ጠብደል ማን አየን በክንዱ ጠግሮ ሲቀጠቅጠው ነበረ አሹ እንደ መልአክ መጥቶ ያዳናቸው። አሹ በራሱ አስር ሰው ነው። ብርቱ ነው። ፊቱ ግን የጨዋ ነው። ንግግሩም የጭዋ ነው። ይህ የሚሆየው ግን ጭዋ ሁነህ ስትቀርበው ነው። አሹ ጋር እሳት መሆን ማለት በሰደድ እሳት መዋጥ ማለት ነው።
ያኔ ማን አየ ጋር ተመሰጋግነው ተለያዩ፣ከወራት በኋላ እራሱ አሹ ማን አየ ድርጅት ውስጥ ስራ ሊያመለክት ጎራ አለ። ማን አየም በክብር ተቀብሎ የመኪናውን ቁልፍ ሰጠው፣ ቀስ በቀስ የቤቱን በር ከፈተለት... አሹ በብቸኝነት መኖሩን እየረሳ አዲሱን ኑሮ ይወደው ጀመረ። ማን አየ ሌላ ሹፌር ሊቀጥር አስቦ ነበረ። ቢሆንም አሹ ቦታ መልቀቅ አልፈለገም። ከማን አየ ጋር እጅግ ስር የሰደደ ቁርኝት ፈጥረዋል። ለሱ የተሻለ ነገሩ የማን አየ ሹፌር እና በሄደበት መሄድ ነው።ይሄ ነው አሹ!
"አይ አንተ አትሄድም አሹ!..."አለው ማን አየ ኮስተር ባለ ድምፅ፣ አሹ ሊከራከረው መፈለጉን ሲያይ" ምን መሰለህ አሹ! ጣናን በሌላ ግዜ እቅድ አውጥተን አስጎበኝሀለው! አሁን አይሆንም! ቤቱን ለማን ትቼ እሄዳለሁ? ሚስቴን እና ልጄን ካንተ ውጭ ካንተ ውጭ ለማን ትቼ እሄዳለሁ?..."
"እንዴ የምን ልጅ ነው?..."አለ አሹ በንግግሩ ተደንቆ
"ሁለተኛው የምስራች ምን ይመስልሀል? አባት ልሆን ነው? ቆንጆ ሴት ልጅ ሊኖረኝ ነው?..."አለው ማን አየ: አሹ በደስታ ማን አየን ተነስቶ ጨበጠውና ሊከራከረው ቢፈልግም ሚስቱ ሳትከራከረው እኔ ስከራከር....ሊቆይ ወሰነ
ሁሉም በደስታ እንኳን ደስ አላቹህ አሏቸውና ቁርሲቸውን በጣፋጭ ንግግር መሀል እየተመገቡ ቅዩ...ተመግበው ሊጨርሱ አካባቢ ላይ ኪሮስ ማን አየን ጠቀሰችውና ተነጥለው ክፍላቸው ገቡ...
"ምነው ፍቅሬ! እዚህ ጥለኸኝ ልትሄድ ነው?..."አለችው ኮስተር ብላ
"አዎ! ልጃችንን ይዘሻልኮ! እንዲሁም ዶክተሩ እያንዳንዱ እንቅስቃሴሽ አደጋ እንዳለው ነግሮኛል። ነገ የህክምና ቡድን ይመጣል! ይሄን ዊልቸር አትጠቀሚም! እንቅስቃሴም አታረጊም። ልጃችን አስኪወጣ ድረስ በልዩ ቡድን እንክብካቤ ውስጥ ትገቢያለሽ...."
"ይሄ ሁላ ለምን?..."
"ለልጃችን! ለእህትሽ ነዋ! ለሴሪ ስትይ ሁሉንም ነገር ትወጪዋለሽ! ሁሉም ከባድ ሊመስል ይችላል ግን አንቺ ፍቃደኛ ሁነሽ የምትጠኚ ከሆነ እናት ትሆኛለሽ..."አላትና ግንባሩን በአንድ ጣቱ እያከከ" ታውቂያለሽ መሄድ አለብኝ! እናቴን በአካል አላገኘኋትም። ልስማት አልታደልኩም። መቃብሯን ቢያንስ ልሳመው!..."
"እሺ ፍቅሬ! ምን ያህል ቀን ትቆያለህ?...."
"ቢበዛ አስራ አምስት ቀን! እና ደግሞ ሰብለም አብራኝ ትሄዳለች.... በብዙ ነገሮች ታስፈልገኛለች!"
"ፍቅሬ ግን አባትህን አታገኘውማ! አደራ ንዴትህ እንደኔ አይነት ስራ እንድትሰራ እንደማያረግህ!..."አለችውና የቢንያምን አይን ትክ ብላ ታየው ጀመረች፣ ቢንያም ክፉኛ ደንግጧል። ግራ በተጋባ አዙሪት ውስጥ ተነክሮ አጉል እየዋኘ ይመስላል።አይኑ ዲስኩ ላይ ተከፈሰቶ ከተተወው የፎቶ አልበም ላይ ተተክሏል። አይኑ ጭፍን ግልጥ እያለ በማመንና ባለማመን ግራ መጋባት ውስጥ እየተገላበጠ ይከስላል።
"ይሄ ሰውየ ማን ነው? ፍቅሬ ይሄ ሰው ማነው? ከፎቶ አልበማችን ውስጥ ምን ይሰራል?..."
"ይሄ አባቴ ነው! አቶ ተሰማ ይባላል። ደግሞ የፎቶ አልበማችን ውስጥ ምን ይሰራል! አይ የውብ ዳር ለብቻው መሬት ላይ ወድቆ ነበረ። አንስታ የትዝታችን ማህደር ውስጥ ከተተችው! ለነገሩ ሂወታችን ውስጥስ ገብቶ የለ። ያሳፍራል..."አለችና አንዱን ፎቶ መዛ ከአልበሙ አወጣቸው፣ ቢንያም መንጥቆ ተቀበላትና ትክ ብሎ እያየው ድርቅ መታው። ፎቶው ላይ የሚያየውን አስጠያፊ ቅጥበት አምርሮ ረገመው! የሚኖረውን ኑሮ፡ ቤቱን.. ቢሮውን.. መኪናውን... አብልጦ ረገማቸው።
"ቆይ ላቃጥለው!..."ሊሊ ፎቶውን እሳት ቀንጭባ ዱቅ አመድ አረገችው። የቢንያም ሰውነትም አብሮ እየነደደ ነበረ።በውስጡ ብዙ ያሰላስላል።'ወይኔ ቢንያም! ይሄ ሽማግሌ ተጫወተብኝ! እንዴት ይሆናል? አቶ ምስክር! ይሄ ቀጣፊ ማለትም አቶ ተሰማ ነው? በሂወት አለ አልሞተም ማለት ነው? እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ?..."እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ... ሀሳቦችን ሲክብና ዝቅ ሲያረግ ሊሊ በአግራሞት ትመለከተው ነበር።
ይቀጥላል...
📎ሀሊድ | 440 |
| 16 | መቸም ከማልረሳቸው የትምሮ የክፍላችን ግድግዳ ላይ የተጻፉ ጥቅሶች መሀል ጥቂቶቹን እንመልከት...
1, መቆላት እንኳን ላንቺ ለቡናም አልጠቀማት...አስወገጣት እንጂ
2, ትምህርት ውጭ ሀገር ቢሄድ ኑሮ ጅቡቲ ድረስ እሸኘው ነበር
3, ህጣን ልጅ ነው ብየ ጡቴን ባንተርሰው... ሁለት እግሬን ከፍቶ አንጀቴን አራሰው
4, መንግስትና ጡት እንደቆሙ አይቀሩም
5, ቅርብ ወራጅ ከሆንሽ የኋላ በር ላይ ምን ትሰሪያለሽ?
6, አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ!
7, ዳቦሽ ደረቅ ነበር ለጥርስ የከረረ
ህዝቤ ግን ጨረሰው ሻይ እየነከረ
8, ሰው በቃኝ ቢል ኑሮና ጤና ይበቃው ነበር!
9, ከገጠር መጥቶ እኔን የሸወደኝ ጫት ብቻ ነው።
10, ከምታዝጋት ቸኮሌት ግዛላት!
11, ከሰጠሽ ስጪኝ ባሰጪኝ ይቀራል።
እቃሽ አይወረስ አብሮሽ ይቀበራል።
12, ያለወት ቀሪ ሂሳብ እንኳን ጥቅል አገልግሎት ጥቅል ጎመን አይገዛም። እባክወ ጠቅልለው የሚለውን ዘፈን ይክፈቱና ጥቅልል ብለው ይተኙ!
13, ዘረ ለገበሬ ነው።
14, በፍቅር መያዝህ አትዘን! በሚኒሻ መያዝ አለና...
15, እናቷ አራዳ የገባቸው ናቸው።
አባቷ አራዳ ሀገር ያወቃቸው...
እና ምን ያረጋል ፋራ ናት ልጃቸው!
16, ቀና ብለህ ተማር! ዝቅ ብለህ ቅዳ!
17, *... ማለት ዝንብ ያላየው ቁስል ነው።
Just ለትዝታ... እኔ ጋር ከማስቀረው ላጋራቹህ ብየ ነው። የኔ ሀሳቦች አደሉም በሌላ አተርጉሙብኝ... የቱ እስገራቹህ? የቱ አበሻቀጣቹህ?
@ye_sater | 1 505 |
| 17 | #ማን አየ
#ክፍል_አስር
ተገማሽ ባለ ወይን- ክፍል አንድ
"እርግጠኛ ነህ ዶክተር!...."
"በሚገባ!...."
"እና አባት ልሆን ነው?..."
"ጥሩ አባት እንደምትሆን አልጠራጠርም ኢንጅነር ማን አየ!..."አለው ዶክተር ፊቱን ቀየስ እያረገ ወደ ኪሮስ ትኩረቱን አንዣበበና"እንኳን ደስ አለሽ እናት ልትሆኚ ነው።..."አላት
"ይገርማል! እናቴን እንደማያት አርጋ የምታየኝ ልጅ ልትኖረኝ ነው?..."
"አዎ! በተለየ መልኩ አርዐያ እንደምታረግሽ ፍጡም አልጠራጠርም...."
"እኔም አልጠራጠርም! አርዐያ የሚሆን ምን ነገር ላረግላት እችላለሁ? ምን የማወርሳት ነገር አለኝ? እጣየን?..."በአንድ ጣቶቿ ዘመናዊውን የተቀመጠችበት ዊልቸር እያሽከረከረች ክፍሉን ለቃ ወጣች፣ ምንም አይነት ደስታም ሆነ መከፋት አይታይባትም።
ማን አየ የምስራቹን ሲሰማ ራሱን መቋቋም አቅቶት ነበረ። በደስታ ሰክሮ ነበረ። ነገር ግን የማናየ ገጥታ ኪሮስ ላይ አንዱም አልታየም። ሴት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ስትጠንስ የሚታይባት የስሜት አይነት ኪሮስ ላይ ኢምንት አልታየም።
ውስጧ ግን በፍርሀት ይክለፈለፍ ነበረ። ትንሿ እህቷ ትዝ ትላት ጀመረ።ጠረኗ፣ ፈገግታዋ፣ ስታለቅስ ከሁሉም በላይ ደግሞ ' እህቴ አድኚኝ!..."ብላ ስትማጠናት... ድጋሚ ደጋግሞ እየመጣ ሲያንቀጠቅጣት ማን አየ ሰተት ብሎ መጦ ትክሻዋን ጨብጦ ያዛት...
"ውዴ! በሰላም ነው! ጥለሺኝ መሄድሽ ምንን በማስመልከት ነው?..."
"ደስ ብሎሀል? አባት መሆን ምን ያህል ደስታን ይሰጥሀል?..."
"የእናቴ ልጅ የመሆንን ያህል ደስታ ይሰጠኛል። በተለይ ሴት ልጅ ካገኘሁ እናቴን ያገኘሁ ያህል ደስ ይለኛል..."
"ይህኮ ለኔ የማይሆን ነገር ነው። እናት መሆን አልፈልግም። ምንም አይነት ደስታ አይታየኝም። ብችል አሁኑኑ አሶርደው ነበረ ግን..."
"ምን አልሽ ፍቅሬ! ለምን እንዲህ ትያለሽ?..."
"ህጻን ልጅ ባየሁ ቁጥር እህቴ ትዝ ትለኛለች! አዛ ኮንቲነር ውስጥ ሬሳዋ ወድቆ በደም ተሸፋፍና ያየሁበት ቅጥበት ያመኛል። አስበውስኪ ልጅ ወልጄ ማቀፍ ሳልችል ስቀር! ሰልንከባከባት ስቀር! ለሷም መጥፎ እናት መሆን አልፈልግም። እናትነት ለኔ አይሆንም።....''
"እና እናሶርዳት እያልሺኝ ነው..."ፊቱ እየገረጣ እንባ ተናንቆታል
"ድጋሚ ልጠይቅህ! አባት መሆንህ ምን አይነት ደስታን ይሰጥሀል።...."
"ብዙ ደስታ! ከፈቅራት ሴት ልጅ ማግኘት ማለት የፍቅራችን ፍሬ ናት! ወሲብ አደለም ጣፋጩ ፍሬ! ለጅ ነው። ቆንጆ ሴት ልጅ!...."
"ቆንጆ ባትሆንስ! አንደኔ መራመድ ባትችልስ? ምን ይሰማታል?...."
"አንቺ መራመድ አችይም! መልሺልኝ እስኪ! ተጠይፌሽ ወይም ዝቅ አርጌሽ አውቃለሁን? አንቺ መራመድ ባለመቻልሽ ምን ተሰማሽ?..."
"ይሄኮ ነው ልዩ ነገርህ! ጨራሽ ተጠይፈኸኝም ሆነ ዝቅ አርገኸኝ አታውቅም። መራመድ ባለመቻሌ ህልሞቸ ተንደዋል። ግን መራመድ ብችል ኑሮ ይህን ማንነትህን ማግኘቴን እጠራጠራለሁ...''
"እመኚኝ ልጃችን የዚህ አለም አስጠሊታዋ ሴት ብትሆንም አልጠየፋትም። እንቁ አርጌ አሳድጋታለሁ.... ቆንጆም ሆነች አስጠሊታ የሚፈጥረው ልዩነት የለም። ብቻ ትምጣልኝ! ብቻ ውለጂልኝ...."
"እመነኝ ቆንጆ ሴት ልጅ እሰጥሀለው! ይሄ ለኔ ምንም አይነት ደስታ፣ ምንም አይነት የእናትነት ፍላጎት ባይኖረኝም ሙሉ እድሜህን ለሰጠኸኝ አንተ ስል አደርገዋለሁ! እንዲህ ስትፈግግ ያየውህኮ ከረጂም ጊዜ ቀፊት ነው። እና ይህን ደስታህን የምነፍግህ ይመስልሀል? እስካሁን ለደስታየ ኑረሀል። እና እኔ ለምን ደስታህን አላከብርም?..."
ጥምጥም አርጎ አቀፋትና ለቀቅ አርጎ ከንፈሮቿን በወፍራሙ ነደፋት፣ ተመልሶ ተቀመጠና ትክዝ አለ። ማን አየ ከልቡ ደስ ቢለውም አላማው እየተዛባ መምጣቱን ሲያይ በውስጡ ኢጭ አለ። ማናየኮ ለልጅ ብዙ ፍላጎት አልነበረውም። የፈለገው የሚስቱን ደስታ ብቻ ነበረ። ከሊሊ ደስታ ጋር አባትነቱ ሲነጣጠር ኢምንት ነው የሚሆንበት...
"ሊሊ!..."አላት ቢንያም ኮስተር ብሎ
"ጠራኸኝ ፍቅሬ!...."
"ይህ የኔ ብቻ ደስታ እንዲሆን አልፈልግም። እስከዛሬ ከልቤ ያልሳቅኩት አንቺ ደስተኛ ስላልነበርሽ ነው። እናም ልጅ ቢኖረን እንኳን አንቺ ደስተኛ ካልሆንሽ... ያኔ ስማችንን ስንቀይር የተመኘነውን ሂወት ካልኖርነው ምንም አይነት እርካታ አይኖረኝም...."
"ብችል ደስ ይለኝ ነበረ ፍቅሬ!...."
"ብቻ ፍቃደኛ ሁኚ እንጂ ትችያለሽ! የሆነው እንዲህ ነው! ድጋሚ በእህትሽ ናፍቆት አትደሚም። ምክንያቱም በሆድሽ ይዘሻታል። ከወራት በኋላ ትወልጃታለሽ! አሁን ሆድሽ ውስጥ የእህትሽን ነፍስ ዝሪባት! እንባወችሽን ለግልጊባት...
እኔም የእናቴን ነፍስ ናፍቆት በሙሉ ያልተወለደችው ልጃችን ላይ እዘራለሁ.... አናም ከወራት በኋላ የምትወልጂው ልጃችንን ብቻ አደለም። እህትሽን እና እናቴን ነው። ያኔ ናፍቆታችንን በፈገግታዋ እናያለን... ስሟን ሴሪ እንላታለን! ፈጣሪ አዲስ ሂወት ለእህትሽ እንደሰጣት ቁጠሪው! ለእህትሽ ልታረጊው ያቀድሽውን ለሷ አርጊላት...
ያኔ ደስታዋን ታያለሽ! በፈገግታዋ እንጥናናለን! በጩኸቷ ቤታችን ይደምቃል። ውብ የሆነ መናፈሻችን ውስጥ ሶስታችን ተቀምጠን ፊልም እናያለን! አልጋችን ሶስት ስንሆን የተለየ ዳና ይኖረዋል። ብቻ ምን አለፋሽ!...."
"ሴሪ! እሀቴ ሴሪ! ታውቃለህ ድሮ እናትና አባታችን ከሞቱ በኋላ እህቴ ተኝታ ሳያት ምናለ ልጄ ብትሆኚ እላት ነበረ። የእናት ፍቅርን ከምትናፍቅ ምናለ እናቷ በሆንኩ ብየ እተክዝ ነበረ። አሁን ደግሞ ልጄ ልትሆን ነው? ደጋሚ እንደተወለደች እቆጥረዋለሁ! ሀሌም አጠገቧ እሆናለሁ! እንከባከባታለሁ! የተመኘነውን ሂወት እንኖረዋለን... መቸም ከአጠገቧ አልለይም።...."ሊሊ ባንዴ ፊቷ ሲቀየር የቢንያም ልብም ሸፈተ... ድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያያት የነበረችው ሊሊ መስላ ታየችው... ገን ያ ጊዜ ለሱ መቼም የማይደገም ነበረ። በሂወቱ ካሉት የትዝታ ከተማወች መሀል መዲናዋ ያ ጊዜ ነው።
"ውይይይ የኔ ማር! ይህን አንቺ ነሽ የተናገርሺው? ደግሞ እንደድሮው መሳቅም ትችይበታለሽ! እስከዛሬ ሸውደሺኝ ኑረሻል። ድጋሚ ይሄ ፈገግታሽ ከፊትሽ ተለይቶ ማየት አልፈልግም። የሆንሽ አሲዳም ነገር!...."አላት ቢንያም። ለመጀመሪያ ገዜ ከአመታት በኋላ ሲኮራረፉ፣ ሲተራረቡ ሲደባደቡ ቆይተው አመሻሽ ግድም ላይ እንደ ወጣትነት ዘመናቸው ሊሊ ዊልቸሯ ላይ ቢንያም ደግሞ እየገፋት ወደ ቤታቸው ጉዞ ጀመሩ። እንደድሮዋቸው ሲታዩ ብርቅ ቢመስሉም አሁን ደግሞ የብርሀን ነፀብራቅ ይታይባቸዋል። ጀንበር ባናታቸው ላይ ስታዘቀዝቅ አብራቸው እየተጓዘች ትመስላለች... አቤት ማዳላት! ቢንያምና ሊሊ አሁንም የድሮወቹ ናቸው። የተቀየረው ሂወታቸው ነው።.......................
ይቀጥላል....
✍🏾ሀሊድ | 401 |
| 18 | #ማን አየ?
#ክፍል_ዘጠኝ
ከወር በስተጀርባ የተደበቀው ጮሌ...
.....ያች ቀን ከሰብለ ቤት ውስጥ የተፈጠረው ክስተት በሁለት ሰወች አመለካከት ውስጥ ንፋስ የዘራ ይመስላል። ማን አየና ሰብለ አያወሩም። የስራ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ጭራሽ አብረው አይቀመጡም። መተቃቀፍ የሚባለው ነገር በአንዲት ለሊት ክስተት ብቻ ሌላ አመለካከት ተዘራበትን ገመዱ ተበጠሰ....
ይህ ጉዳይ ሰብለን እያሳሰባት ነው። እንደድሮዋቸው እንዲሆኑ ብትፈልግም ክስተቱ በሷ ስሜታዊነት የተፈጠረ መሆኑን ተገን በማረግ ሙሉ ጥፋቱን ራሷ ላይ ዱላዋለች... በዚህም የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማታልና ማን አየን ማናገር ቀርቶ ለሰከንዶች አፍጣ ለማየትም ወኔዋ ይከዳታል።
ታድያ አንድ ቀን የተወሰኑ ሰነዶችን ይዛ ወደ ማን አየ ቢሮ ስትገባ ማን አየ ተነስቶ ባልጠበቀችበት ቅጥበት ከንፈሮቿ ላይ ተጠመጠመ... የናቱን ጡት እንደሚጠባ ህጻን ልጅ መጠመጣት፣ መልሶ ለቀቃት... አይን ለአይን ተፋጠው ቀሩ...
"ለምን ሳምከኝ?..."ብላ ጠየቀችው
"የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማሽ ነዋ! ባለፈው በተፈጠረው ነገር ምክንያት በመሀላችን ንፋስ እየገባ ነው። የጥፋተኝነት ስሜት እየተሰማሽ ወይም አንቺው ስለጀመርሽው የመዋረድ የክብረ ቢስነት ስሜት እየተሰማሽም ሊሆን ይችላል።..."
"እና..."
"እናማ እይው እኔም ሳምኩሽ! እኔም ፈጣጣ ነኝ! እኔም ጥፋተኛ ክብረ ቢስ ነኝ! ከምሬ ነው! የተፈጠረው ነገር ምንም ይሁን ኢግኖር እናርገው! ያችን የምታጥናናኝን እህት ላጣት አልፈልግም።...."
"ግን የሚቻል አልመሰለኝም። የሆነ የተቆረጠ አይነት ስሜት ይሰማኛል።...."
"ደግሜ ልሳምሽ እንዴ...."ከልቡ ሳቀ
ተከትላው እየሳቀች..."ያች የማታዋ ሰብለ እኔን አትወክልም። ያች ሌላ ሴት ናት! ግን ገላኝ የሄደች ይመስለኛል።....."አለችና ፊቷን ለወጥ አርጋ"እኔምልህ! ሊሊ እንዴት ናት! እስከዛሬኮ አማቼን አላስተዋወቅከኝም! በጣም ታዘብኩህ!....."
"ባይገርምሽ ስላንቺ ነግሬያታለሁ! ብዙ ብዙ ነገር...ምን እንዳለቺኝ ታውቂያለሽ!..."
"እሺ ምን አለች?..."
" 'ፍቅሬ እስካሁን ለምን አልነገርከኝም? ደግሞ ብቻዋን ያውም ተከራይታ ነው የምትኖረው! እዚህ ትልቅ ቤት ያለ ሰው ጢሻ ለብሶ እየኖረ ለምን አታመጣትም?...' እናም ቤታችን ላንቺ ክፍት ነው። በመሀላችን የተፈጠረውን መስተጓጎል ላቃና ብየ እንጂ ከታዘዝኩ ቆይቻለሁ..."
ማን አየና ሰብለ ወሬያቸውን ሳያቋርጡ ቀጥታ ወደ ትልቁ መኖሪያ ቤት አቀኑ.... ሰብለ መንግስተ ሰማያት የደረሰች መሰላት... በሩን አልፋ ወደ ውስጥ ስትገባ እቃዋ በሙሉ ተዘጋጅቶ፣ ክፍሏ ውብ ሁኖ ጠበቃት... ከሊሊ ጋር ለመግባባት ጊዜ አልወሰደባትም።
ጥሩ ተግባብተው እየፈገጉ ሳለ ሊሊ ዊልጀሯን እጅ ማሰደገፊያው ላይ ባለው ማንቀሳቀሻ ተገንጥላ መናፈሻው ላይ ደረሰች... በጀርባ ያሉትን የተከመሩ ዛፎች እያየች ትክዝ ብላ ቀረች... ሰብለ ግን ክው ነበረ ያለችው። በሚያስደንቅ ሁኔታ እየፈገጉ ሊቋረጥ በማይችል ንግግር ተጠምደው ባለበት ሰሀት ዝም ብላ ጥላት ስትሄድ እንዴት አትደንግጥ? የፍርሀት ስሜትም አድሮባታል።
ሊሊ እንደዚህ ናት! ደስታም ሆነ ሌላ ጥሩ የሚባል ነገር ላይ ፍላጎት ታጣለች... ውስጧ ያለው ፍላጎት ማጣት የናረ ነው። መኖርም ሆነ መሞት፣ መሳቅም ሆነ ማልቀስ... ብዙ ነገሮችን በቸልታ ማለፍ አይሳናትም። ለሷ ትክክለኛው ቦታ ወይ የባሏ እቅፍ ነው። ወይ ደግሞ ከራሷ ጋር ብቻ የምታረገው የዝምታ ንውጠት ነው። ይህ ዝምታዋ ሀያል ነው። አንዴ ዝም ካለች ሳምንትም ልትቆይ ትችላለች.... በራሷ ጊዜ ካልሆነ በቀር ዝምታዋ አይሰበርም። ሲላት ደግሞ ትጮሀለች እቃ ትፈጃለች... እንደ እብድ ያረጋታል።
ማን አየ ሰብለን ቤታቸው ካደረሳት በኋላ አንድ ስልክ ተደወለለት፣ መልዐክ የጠራው ይመስል ጥድፍ ጥድፍ እያለ ወደ ተቀጠረበት ቦታ አመራ...አንድ በዛፎች እና በአዕዋፋት የተከበበ ቦታ ሲደርስ ቆም አለ።ከፊት እየቃኘ ሳለ " ኢንጅነር ማንአየ!..." የሚል ድምፅ ከኋላ አቃጨለበት....
ወደ ኋላ ዞረ... ረዘም ያለ... ጠቁር ጃኬት ጥቁር ሱፍ ላይ የደረበ... ሸበቶ ፂማም። ድርድር ጥርስ እና የሚስብ ሀይል ያለው ሸምገል ያለ ሰውየ... በተለይ ለማን አየ ከመልአክ አይተናነስም።
"አቶ ምስክር! እንዴት ተገኘህ ባክህ! መቸስ ተፈልገህ አትገኝም። እንደ ጥላ ነህ! ብትታይም ከትጨበጥም!..."አለው ማን አየ ከልብ በሆነ ሙሉ ፈገግታ እጁን ዘርግቶ አቀፈው....
አቶ ምስክር አቶ ምስክር ብቻ ነው። ማን አየ የሚያውቀው አቶ ምስክርነቱን ብቻ ነው። ታድያ ለምን እንዲህ ቦታ ሰጠው ብትሉኝ የማንአየ የስኬት ቁልፍ የሆነው አቶ ምስክር ነውና... ማን አየ ወየ ኢንጅነር ማማ ተጉዞ ስኬት ላይ ከመውጣቱ በፊት ምስክር ነገሮችን ጎዝጉዞለታል።
ሊሊና ቢንያም አዲስ አበባ በባዶ ኪሳቸው ሲደርሱ የተወሰኑ ቀናትን በርሀብ ተሞርሙረው የጎዳና ሂወትን ተንተርሰው ፍዳ እየበሉ ነበረ። ታድያ ቢንያም ከሊሊ ተነጥሎ ምግብ ፍለጋ ሲሰማራ ምስክርን ያገኘዋል። አቶ ምስክርም ለቢንያም አስራ አምስት ሺ ብር ሰጠው... ቢንያም በዚህች ለወር የማትበቃ ብር ተጉዞ ኢንጅነር ማን አየን ሊሆን ችሏል።
ታድያ የምስክር ውለታ አላበቃም። በአንድ ወቅት የማን አየ ድርጅት ከሰረ፣በብድሮች አዘቅት ውስጥ ሁኖ ድርጅቱ ለጫረታ ሊወጣ ተወሰነ... እናም በዚህች ቅጥበት አቶ ምስክር ማን አየን መንገድ ዳር ኩርምት ብሎ ያገኘዋል።ቀርቦ አዋይቶ በስተመጨረሻም በብድር መልክ ብዙ መቶ ሚሊየኖችን አቅርቦለት አድራሻውን ሳይነግረው ይሰወራል።ማን አየ ድርጅቱን ካስተካከለ፣ እዳውን ከፍሎ ካገገመ በኋላ ሰውየውን ቢፈልገውም ሊያገኘው አልቻለም።
"ምነዋ! ምነው! ሳልተኛ ህልም ማየት ጀመርኩሳ..."አለ ማን አየ ምስክርን አፍጦ እያየ...
"ህልም አደለም ወዳጀ! እውን ነው..."
"ህልም ማለት አንተው አደለህምን? መላ ኢትዮጵያ ውስጥ ያላስፈለኩህ ቦታ ይኖር ይሆን? አይ አይኖርም።...."
"ኢትዮጵያ ውስጥ ተቀምጠህ እንዴት ኢትዮጵያን ትፈልጋለህ ወዳጀ? ስለመጣህ ደስ ብሎኛል!...."ተቀምጠው እልፍ ሰሀታትን ሲያወጉ ከቆዩ በኋላ ምስክር ብድግ ብሎ"ወዳጀ ስላየውህ ደስ ብሎኛል። ካንተ ጋር መሆን ወጣትነቴን ያስታውሰኛል። በድጋሚ እንደማገኝህ ትልቅ ተስፋ አለኝ!...."
"ምነዋ ወዳጄ! ቢያንስ ብድሬን ከፍየህ እንድትሄድ እለምንሀለው!...."
"የገንዘብን መንፈስ ቀስቅሰህ ይህን ጨዋታ አንዲያቆሽሸው አታርግ! የለኝ ገንዘብ ይበቃኛል። ምን ልጆች የሉኝ አላወርሳቸው! ሰግብግብ ባለ ስልጣን ከሚበላው እሱ ይሁን! ሰፈልግ እጠይቅህ የለ!...."ተመልሶ ሰላም አለውና ተሰናብቶት ድጋሚ በመንገዶች መሀል ተሰወረ።
ማን አየ እስኪሰወር ድረስ ሽማግሌውን ፍንትው አርጎ እያየው ነበረ።ልክ እንደተሰወረ የተለመደ ጥያቄው ጭንቅላቱን ይኮሰምነው ጀመረ።"ይህ ሰውየ ግን ማነው? እንዴት የራሱ ሰው እንደሆንኩ ሁሉ በየኔ ነህ ስሜት ሊያየኝ ቻለ?............."
ይቀጥላል......
✍🏾ሀሊድ | 364 |
| 19 | No text... | 281 |
| 20 | #ማን አየ?
#ክፈል_ስምንት
ስልካችን power off ቢሆንም ቻርጅ ያደርጋል
ቆየት-የት - መሸት- ሸት ሲል ማን አየን ያነቀፈው ደዌ ከልቶ እየተረጋጋ ይመስላል።...ሰብለ የለበሰችውን ስስ ሌዘር ጃኬት አውልቃ ጣል አረገችለ እየበረደው ላለ ሰው ብርድ ልብስ ምን ይፈይድለታል?... ምንም መንቀጥቀጡን አቁሞ ትክዝ ባለ አስተያየት አንዴ ሰማዩን አንዴ መሬቱን ያያል።...'አንቺ መሬት እናቴን በቁሟ ተሸክመሽ ስታሳክኪያት ኖርሽ! አሁን ደግሞ ስጋዋን እየበላሽ ነው። የትኛዋን ልጅሽን ድረሽ ይሆን የእናቴን ስጋ ለመስዋትነት ያበቃሽ፣ የቀጠፍሽ! ሰርጉ በምስር አይሆንም ነበር? ምስሩም ስጋውም አጠገብሽ አለ።...."ይላል በውስጡ
"ታላቁ ሰማይ! እስከዛሬ ድረስ ስነቅፍህ ኑሬያለሁ! ካንተ ይልቅ የመሬቱን መና አስቀድሜያለሁ፣ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ እንደማልፈልግህ ይሰማኝ ነበረ። ዛሬ ግን እናቴን ይዘሀል። ውድ ሁነሀል። መንግስተ ሰማያት እራሱ ውድ የሚሆንብኝ እናቴ ስትኖርበት ነው። እናቴ እውስጥ ካለች የፈለገው መጥፎ ብሆን የመግባት መብት አለኝ... መጥሀፉ አንድን እናት ከልጇ ነጥላቹህ አታርቁ፣ መብቷን አትንፈጊ ይላልና...ደግሞ እኔ የገነት ፍቅር ኑሮኝ አይምሰላቹህ፣ እናቴ ስላለች ነው። ካላመናቹህ እናቴን ገሀነም አስገቧትና ገሀነምን ከመንግስተ ሰማያት እኩል አርጌ አሳያቹሀለው። ግን ሰማይ ሁሌም ትናፍቀኛለህ....."
ኢንጅነር ማንአየ እንዲህ ባለ የሀሳብ ነውጥ ራሱን ሲንጥ ቆየና የሆነ ሀሳብ አፉን ከፍቶ አክታውን የለቀቀበት ይመስል ወደ ሰብለ ዞር አለና ግንባሩን በመሀል ጣቱ ጫር ጫር እያረገ፦
"እኔምልሽ!..."አላት
"ወየ ቢኒ!..."
"ደብዳቤ ጥፌ አልነበረ? አንድ ለሰብለ አንድ ለእናቴ ስጪልኝ ብየ ሰጥቸሽ ነበረኮ!...."
"አወ! ግን በወቅቱ ለሰብለና ለሊድያ ብቻ ጥፈህ ለኔ ስላልጣፍክ ቀንቼ... ወረቀቱን አቃጥየዋለሁ። በጣም ይቅርታ! መጥፋትህን ሲነግሩኝ እነሱን ቻው ብለህ ዝም ስትለኝ ያለ መፈለግ ስሜት ተሰማኝ...."አለችው በውስጧ የመቀለድ ስሜት እየተጠናወታት... እንጂማ ደብዳቤውን እንደሰጣት ወስዳ የቤታቸው ጠረንጼዛ ላይ ነበረ ያስቀመጠችው። ልብሷን ቀይራ ስትመለስ ደብዳቤውን በቦታው ላይ አጣችው፣"የት ተሰወረ? እሺ ማን በላው ይባላል?..."ስትል ነበረ።
"ማን እንደወሰደው አላወቅሽም?...እናቴኮ...."መናገሩን ገታ አረገ "(እናቴኮ ደብዳቤውን ብታነበው ደህና ትሆን ነበረ። ትረጋጋ ነበረ)"" ሊል የፈለገው ይህን ነበረ። የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማት ሲል አልነገራትም።
"በጣም ይቅርታ! አንተ ግን ምን እየተሰማህ ነው?..."
"የሚሰማኝን አጠይቂኝ! እኔን የሚሰማኝ ነዳጅ እንደሆንኩ እና ዙሪያየን በእሳት እንደተከበብኩ ነው። እሳቱ ቃስ በቃስ እየተጠጋኝ ግን አልነድም። ፍርሀት ብቻ ይለቅብኛል።..."
"አይዞህ! በማንኛውም ሰሀት አጠገብህ እሆናለሁ..."
"የእናቴን መቃብር ማየት ይኖርብኛል። በቅርቡ ታሳይኛለሽ በቅርቡ!....."
"ምን! አኔ ግን አልችልም። ድጋሚ ወደ ባህርዳር መመለስ አልፈልግም።..."
"ለኔ ስትይ ታደርጊዋለሽ...."በንግግራቸው መሀከል ላይ አልታወቃቸውም እንጂ አጠገብ ለአጠገብ መሆናቸው ቀርቶ ሰውነታቸው ተገጣጥሟል።የሚያወሩት አፍ ለአፍ ነው።ሰብለ ይታወቃታል። በትንፋሹ ስበብ ሰውነቷ ስስ ሁኗል። ፍም ሁናለች፣ ሰውነቷ ይንዘረዘራል። ፍጡም ግላለች፣ለመጨረሻ ጊዜ ወሲብ ያረገችው ከሁለት አመት በፊት ነበረ።ዛሬ በአንድ ቀን ተደማምሮ ሲነሳባት ልውስውስ ዝንፍፍ አለች፣
ከቢንያም ጋር ስሜታዊ ግንኙነት አትፈልግም። አንድ እንደ ወንድሟ ስታየው... ሁለትም ቢሆን ለሊሊ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ታውቃለች፣... ቢሆንም ሰውነቷን ከቢንያም እጅ ማላቀቅ አልቻለችም። ሁሌ እንደምታቅፈው የዛሬው ቢለይም ዛሬ ግን የቢኒ ፊት እቀፉኝ እቀፉኝ እያለ እያየች ከግለቱ ለመሸሽ ድፍርት አነሳት...
"እሺ ቢኒየ! አብሬህ እሄዳለሁ!..."አለችውና ለመነሳት እየሞከረች..."አንዴ ውሀ ይዤልህ ልምጣ!..."አለችው
"አይ አያስፈልገኝም! እስኪ ፀጉሬን ዳብሺኝ እንደ እናቴ!..."አላትና ዝቅ ብሉ ጭኖቿን ተንተርሶ ገደም አለ።ሰብለ ግን እየተንተከተከች ነው። ወደ ጭኗ ዝቅ ሲል አናቱ ጡቶቿን ቀርጨፍ አርጎ ነበረ። ቢንያም ጭኖቿን ቢንተራስም ጉልበቷን በእጁ ይዳብሳት ነበረ።
በስተመጨረሻም ሰብለ ነሆለለች፣ በዚህ ሁኔታዋ አንድ የመንደር እብድ ቢያገኛት እንኳን ለምና ጭኖቿን እንደምትከፍትለት አያጠራጥርም። ሰብለ ራሷን አደለችም። ሰብለ አሁን የወሲብ ስሜቱን ከግለቷ ጋር ሁናለች፣የቢንያምን ፀጉር መዳበስ ካቆመች ፀሀይ ምሳዋን እና እራቷን የበላች ይመስላል።አንዴ ጀርባውን አንዴ ደረቱን ብትዳብሰውም እሱ አይሰማትም።
"ቢኒ ራብከኝ!..."አለችው ለጥ ያለ እንቅልፍ ወስዶታል። ይህ ግን የሚገታት አደለም። አንከባላ ብርድ ልብስ ውስጥ አስገባችው። በቅድሚያ ሸሚዙን... ሱሪውን... ፓንቱን... ቢንያም በእንቅልፍ ልቡ እርቃኑን ሆነ፣ ሰብለ ሰብልየ ተከመረችበት.... አንዴት አትበሉኝ ስልካችን power off መሆኑ ቻርጀር ከማረግ አይገድበውምና
ማን አየ በእንቅልፍ ልቡ ቢሆንም አእምሮው ጤሰ፣ ከባድ ግለት ተሰማው... የወሲብ የማይመስል ግለት ሰውነቱን አንዘረዘረው... ከወሲብ በላይ የሆነ ንውጠት ከእንቅልፍ ልቡ አባነነው... የሰብለ ትንፈሽ ፋታ አልሰጠውም። ወድያው ተሸነፈ፣ ታላቁ ህንጻ ሰሪ ብረት ተብሎ የተነገረለት ጀግና ዛሬ ተሸነፈ... ከንፈሮቿ ስር ሲቀረቀር ኤርታሌ ውስጥ ተነክሮ የሚዋኝ መሰለው... ከፀበል የማይተናነሰው ላቧ አገላብጦ ሲያርሰው ከሀጥያቶቹ ነፃ የሆነ መሰለው። የሰብለ ግን ከሁሉም የከፋ ነበረ። አንድ አንድ እያለች የሁለት አመቱን ሙሉ ስምቷን የምታሯሩጥ ይመስላል።ሰውነቷና ሰውነቱ አንድ አይነት ዜማ ዘመሩ፡ ቤቱ ወሲብ ወሲብ መተሻሸት መተሻሸት ሸተተ... በበር ሲያልፍ ሲያገድም ሽታው ውል ባለበት ሰው ሳይቀር የተደበቀ የወሲብ ግለትን ይፈነቅላል።
ይቀጥላል....
✍🏾ሀሊድ
Copy/past እያረጋቹህ ሌላ ቻናል ላይ የምትለቁ ወገንታት አድቡ! በትክክለኛው መንገድ forward እና share እያረጋቹህ ብቻ ተጠቀሙ። አንብባቹህ ከወደዳቹህት like ማረግ በነፃ ነው🥇 | 493 |
