cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Life giving Gospel songs

LIFE GIVING GOSPEL SONGS # መንፈሳዊ ትምዕርቶች # ቆየት ያሉ እና አዲስ መዝሙራትን # መንፈሳዊ 𝗽𝗶𝗰𝘀 # ️መንፈሳዊ እና ወቅታዊ ጽሁፎችን በ @Thelifeofcrist For any info # @slaveofchrist7340 # @ragalt We can discuss in @Thelifeofchrist

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
182Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
👍 0
👎 0
Show all...
👍 0
👎 0
#አስቸኳይ_የፀሎት_ርዕስ። 🔵 በአዲስ አበባ ላይ ያነጣጠረ የጠሰፋት አዉሎ ነፋስ አየሁ። ከተማይቱ ላይ ድንገት የሚነሳ ረብሻና የሰዎች ግድያ አየሁ። ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ጊዜ እንደፃፍኩላችሁ አይነት በድንገት ግርግር ተነስቶ ብዙ ሰዎች እንዲገደሉነሠ ከተማይቷ እንዳትረጋጋ፣ ወጣቶች እንዲያልቁ ከአሜሪካ እስከ አዉሮፓ ድረስ ከዚያም እስከ ግብፅና ሱዳን ብሎም ከናይጄሪያ እስከ ኬንያና ጅቡቲ ድረስ የተዘረጋ የጥፋ ኔትወርክ አየሁ። በአዲስ አበባ ዙሪያና በከተማይቷ ዉስጥ የተመሸጉና እንዲጀምሩ ትዕዛዝ የሚጠብቁ ሰይፍ የታጠቁ ሰዉ የሚመስሉ ፊታቸዉ የማይታይ ነገር ግን ከተማይቷ ላይ የሚርመሰመሱ ጥላ የሚመስሉ ሰዎችን አየሁ። 🔵 እንደገና በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ከመሬቱ ዉስጥ እየፈነቀሉ የሚወጡ ብረት በብረት የለበሱ እባቦችን አየሁ። ቁጥራቸዉ የበዛ እየተርመሰመሱ በፍጥነት እየሮጡ ሰዎችን ሲነድፉ አየሁ። ሰዎችም በኃይል እየሮጡ ከሚናደፉት እባቦች ለማምለጥ ሲሞክሩ አየሁ ሰዎች ግን አያመልጡም ነበር። ይህን እያየሁ ሰማዩ ጭስ በሚመስል ደመና እየተሞላ ሲሄድም አይ ነበር። አድነን እያሉ ወደ እግዚአብሔር የሚጮሁትን ሰዎች እሰማ ነበር። ድንገት ድንገት ድንገት የሚነሳ አዉሎ ነፋስ አለ። እግዚአብሔርም ልባችሁን በማደንደንና ለመመለስ እንቢ ብትሉ ለመስማት የሚዘገንናችሁ ሞት ወደ ቤታችሁ ይገባል፣ ማንም ማንንም የማያድንበት ሰይፍ በምድሪቷ ይመዘዛል አለኝ። 🔵 የአዲስ አበባ ህዝብ ሆይ እንደ አንድ ሰዉ ልባችሁን መልሳችሁ ብትመለሱ እመለሳለሁ እንቢ ብላችሁ በአመፃችሁ ብትቀጥሉ ጠላት በሞት ምድራችሁ ላይ ይሰለጥናል። ከንቱ ጩኸት አትጩሁ ካልተመለሳችሁ ለጩኸታችሁ ጆሮዬ የራቀ ነዉ። 🔵 አዲስ አበባን ከብቦ የተቀመጠ የጥፋት እግር አይቻለሁ በፍጥነትም ወደ ከተማዋ ሲገባ አይቻለዉ። ለቁጥር የሚታክት ብዙ መሳሪያ እየተጫነ ወደ ከተማዋ ሲጓጓዝ አየሁ ይህ የሆነዉ በስዉር ነዉ። እኔ ያየሁት መሳሪያና የሚገድሉ እግሮች በፍፁም ያልተጠበቁ መሳሪያዎች ናቸዉ። ልክ በስጋዉ ጆሮዬ እንደምሰማዉ አይነት ድንገት ከአንድ አቅጣጫ ተኩስ ሲከፈትና ረፍት የሌለዉ ተኩስ ሲጮህ በመንፈሴ አደምጥ ነበር። በዚህን ቅፅበት ከዎች ሲሮጡ መኪኖች ሲቆሙ እንቅስቃሴ ሲቆምና የሰዎች ሬሳ መንገዶች ላይ ሲወድቅ አየሁ። ወንዱ ሴቱ እንደ ወላድ ሴት ሰዎች ሲያምጡና ሲጮሁ ሰማሁ፥ አረ እግዚአብሔር ሆይ ለዚህ ህዝብ ራራ እያለሰኩ አለቀስኩ ህዝቡ ንቆኛል በትዉልዱም መካከል የኃጢአትና የእንባ ፅዋ በፊቴ ሞልቷል ካልተመለሱ አልመለስም አለኝ። ግን ልብ በሉ ይሄ አዲሰሰ አበባ ላይ ይከራል እንጂ ክልል ከተሞችም ላይ አመፅ ይቀሰቀሳል። እናቶች አባቶችና ህፃናት ሲጮሁ መሬት ላይ ሲንከባለሉ አየሁ። ነገሩ እጅግ ከባድ ነዉ። አገልጋዮች ከቻላችሁ ለጊዜዉ ግርግሩን አቁሙና ህዝቡን ወደ ፀሎት አስገቡት። አሁን የሚመጣዉ ቤተክርስቲያኖችንም የሚያወድም እየመረጠ የሚገድል ሰይፍ ነዉ። 🔵 ነገሩ ተገልጦ ከተማችሁ በደም ከመጨማለቋ በፊት ፈጠኑ ፊቴን ፈልጉ አለኝ፤ አሁንም እንቢ ብትሉ ሞት በደጃችሁ ነዉ። በዚህ ሁሉ ግን ጥቂት ሰዎች ሲፀልዩ እመለከት ነበር። በቤቴ ፀሎት የለም ግርግርና ዝርፊያ ቤቴን ሞልቷል፣ አገልጋዮችም ልጆቼን ሰርቀዉኛል፣ እኔን የሚፈልግ የለም ቤተረ የወንበዴና የዘራፊዎች ዋሻ ሆኗል። በቤቴ ቃሌ ተንቋል፣ ፅድቅ ተጥሎ ኃጢአት ቤቴን አገማዉ አለኝ። ቤተክርስቲያን ሆይ ንቂ፥ ከእንቅልፍሸ ተነሺ። 🔵 የሚገርመዉ ደግሞ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ አዳነች አበቤ አስር የማይሞሉ ጥቂት ባለስልጣናት ላይ የተቀነባበረ የግድያ ሙከራ አየሁ። አሁን በፍፁም ልባችሁ የማትመለሱ ከሆነ ዘግናኝ ሞት ቤታችሁ ይገባል። እንደፈለጋችሁ አሁን የምትነሠገሩ በኃላ ማምለጫዉ ይጠፋችኃል፣ ዛሬ የምትቀልዱ ነገ ሰይፍ በአንገታችሁ ያልፋል። ደም ጠምቶት እያጋሳ ከተማይቷ ላይ የሚጮህ ዘንዶ አያለሁ ተዉ ግድ የላችሁም ተመለሱ ንስሃ ግቡ። 🔵 መልካም ለሊት። ሚያዚያ 18/08/2014ዓ.ም፤ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።” — 2ኛ ቆሮ 13፥14 #የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ 🔵 መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
Show all...
Show all...
👍 0
👎 0
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ከፍተኛ_የደም_እጥረት_ተከስቷል ! በብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት የደም ለጋሾች ዘርፍ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር ተመሥገን አበጀ ፦ " በአገሪቱ ያሉት የሁለቱ ትላልቅ ሃይማኖቶች ተከታዮች ፆም ላይ መሆናቸውን ተከትሎ በመላ አገሪቱ ከፍተኛ የደም እጥረት ተከስቷል። በአገሪቱ ያለውም የመጠባበቂያ ደም ክምችት ከ5 ቀናት የማይበልጥ ነው። በአገር ደረጃ ሲታይ ከፆም በፊት በዚህ ዓመት የነበረው የደም ክምችት አመርቂ የሆነበት ዓመት ነበር ብሎ መውሰድ ይቻላል። የዐቢይና ረመዷን አፁዋማት ከገቡ በኋላ የመደበኛ ደም ለጋሾችም ሆነ ሌሎች ለጋሾች ቁጥር አሽቆልቁሏል። ይህም የደም ክምችት ላይ ከፍተኛ እጥረት እንዲፈጠር አድርጓል። በተለይ እንደ ፕላትሌት የደም ተዋፅዖ እና ‘ኦ’ የደም ዓይነት ክምችቶች እጥረት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ፕላትሌት የሚባለው የደም ተዋፅዖ ለካንሰር ታማሚዎች እና የደም መፍሰስ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች የሚሰጥ የደም ዓይነት ነው፤ ክምችቱ ለአንድ ቀን ብቻ ሲሆን ‘ኦ' የተባለው የደም ዓይነትም በዛ ቢባል ለ2 ቀናት የሚሆን ክምችት ነው ያለው " ያንብቡ : https://telegra.ph/EPA-04-19-2 #EPA @tikvahethiopia
Show all...
Show all...
👍 0
👎 0
Show all...
👍 0
👎 0