en
Feedback
የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት

የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት

Open in Telegram

ይህ የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኦፊሻል የቴሌግራም ቻናል ሚዲያ ሲሆን የዞኑን ፓርቲ የተቋቋመለትን ተልዕኮ በብቃት ለማሳካት ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ የወረዳ፣የከተማና የዞን እንዲሁም የክልል፣ሀገር ብሎም የአለም አቀፍ ደረጃ ጭምር የሚያከናውናቸውን ማናቸውንም ተግባራት መረጃ ይሰራጭበታል!!.

Show more
364
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የጋራ የሆኑና የሚያስተሳስሩን የትላንት ታሪኮችን በመጠናከር የተሻለች ኢትዮጵያን እንገንባ!!. ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ!!.

ጥቅምት 18/2016 ዓ/ም፤ሀላባ ቁሊቶ፤በፓርቲው ግንባር ቀደም መሪነት የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በአደረጃጀት ለመፈጸምና የተጀመሩ የኢንሼቲቭ ሥራዎች ተጠናክረው ልቀጥሉ ይገባል - የተከበሩ አቶ መሀመድከማል ኑሪዬ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ፣ ቅ/ጽ/ቤቱ የ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል። በዚህ ወቅት መድረኩን የመሩት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ የተከበሩ አቶ መሀመድከማል ኑሪዬ በሩብ ዓመቱ በፓርቲ ግንባር ቀደም መሪነት ባተከናወኑት ተግባራት በየዘርፉ አንጸባራቂ ድሎች መመዝገባቸዉ ተገልጻዋል፡፡ በሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ግንባር ቀደም መሪነት በንቅናቄ የሚከናወኑ ሁሉንም የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በአደረጃጀት ለመፈጸም በአደረጃጀት ዘርፍ የተጀመሩ ኢንሼቲቭ ሥራዎች እንደ ዋነኛ ስልት ተወስደው በሁሉም የፓርቲው ግንባሮች በተደራጀ መልኩ ማስፋት እንዳለባቸው አስምረውበታል። በተለይም በዘርፉ ሞዴል የፓርቲ መሠረታዊ ድርጅቶችን፣ ህዋሳትንና አባላትን በብዛትና በጥራት በመፍራት የፓርቲው ማህበራዊ መሰረቶች ለማስፋት የተጀመሩ ኢንሼቲቭ ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል በሌሎችም ዘርፎች መደገም እንዳለባቸው አቶ መሀመድከማል በአጽንኦት ተናግሯል። ተግባራቱን በንቅናቄ በመፈፀም ሳይንጠባጠቡ በውጤታማነት እንዲከናወኑ በየደረጃዉ ያለው የፓርቲያችን መዋቅሮች በቅርብ ክትትልና ድጋፍ መምራት እንዳለባቸውም በመግለፅ። የፓርቲ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ ለተጀመረው ሁለንተናዊ ብልጽግናና ሀገር ግንባታ የማይተካ ሚና እንዳላው በመግለፅ በዞኑ በየደረጃው ዘርፉን በጠንካራ የሰው ኃይል፣ማቴሪያልና በአሠራር በማደራጀት የሚጠበቅበትን እንዲወጣ ልደረግ ይገባል ብሏል። ዘርፉ የፓርቲውን እሳቤዎች፣መርሆዎች፣እሴቶች እንዲሁም የተግባር ስኬቶች መሰረት በማድረግ በየደረጃው አፍራሽ ዘመቻዎችን ለመመከት እና አሁነዊ የትርክትና የመረጃ የበላይነት ለመያዝ የሚያስችል ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ በቀጣይነት መስራት እንደለበትም አቶ መሀመድከማል አሳስበዋል፡፡ በዞኑ በየደረጃው በንቅናቄ ለመፈጸም የለየናቸውን ተግባራት ከግብ እንዲደርሱና የህዝቡን ተጠቃሚነት በተጨባጭ እንዲያረጋግጡ በየደረጃው ያሉ የፓርቲ መዋቅሮች በፓርቲያዊ ዲስፕሊን መምራት እንዳለባቸውም ኃላፊው አሳስበዋል። በተለይም የፓርቲና የመንግስት አደረጃጀቶችን አደራጅቶ በማንቀሳቀስ ተቋማዊ አቅም በማጠናከር ለዘላቂ ለውጥ መሰራት እንደሚገባም እንዲሁ። ከዞን ማዕከል ፓርቲ ጽ/ቤት ጀምሮ የተደራጀው የፓርቲና የመንግሥት ኮማንድፖስቶች በየዘርፉ የታቀዱ የፓርቲና የመንግሥት ተግባራት በወሳኝ መልኩ እንዲሳኩ የተናበበና የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስርዓት በመዘርጋት የሚታይና የሚጨበጥ ለውጥ ለማስመዝገብ በጊዜ የለንም መንፈስ በቁርጠኝነት ልሠራ እንደሚገባም ኃላፊው አስገንዝበዋል። የዉይይት መድረኩ በተለይም በዞኑ በ2016 በጀት ዓመት የባለፉት ሶስት ወራት በፓርቲና መንግስት ተግባራትን በተናባበና በተቀናጃ መልኩ ከመምራትና ከማስፈጸም የነበሩ ዉስንነቶችንና የተገኙ ጥንካሬዎችን በዝርዝር ገምግሟል፡፡ በዞኑ የሚከናወኑ የፓርቲና መንግስት ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራትና በማስፈጻም የህዝቡን ተጠቃሚነት በተጨበጭ ለማረጋገጥ በቀጣይም አጽኖት ልሰጠዉ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡ በመድረኩ የየዘርፉ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጸጻም ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ዉይይትም የተደረገ ሲሆን የቀጣይ የሥራ አቅጣጫም ተቀምጧል። አንዳንድ የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከአፈጻጸም መድረኩ የተነሱ ጉድለቶችን ፈጥኖ በማረም፣ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ለህዝቡ ለጠንካራና ለዘላቂ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ሌተቀን በአንክሮ እንሠራለን ብለዋል። በጽ/ቤቱ የሚገኙ የፖለቲከና አቅም ግንባታ ዘርፍ፤የአደረጀጀት ዘርፍ፤የሲቪክ ተቋማትና ፖለቲከ ፓርቲዎች ዘርፍ፤የሀብት ልማት ዘርፍ፤የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች እንዲሁም የወጣቶች ሊግ እና ሴቶች ሊግ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሲል የሀላባ ብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ዘግቧል፣

ጥቅምት 18/2016 ዓ/ም፤ሀላባ ቁሊቶ፤ በሀላባ ዞን በ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በፓርቲ ግንባር ቀደም መሪነት ባተከናወኑት ተግባራት በየዘርፉ አንጸባራቂ ድሎች መመዝገባቸዉ ተገለጻ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በዛሬዉ ዕለት በጽ/ቤቱ ያሉ ዘርፎችን የ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጸጻም የሚገማግም መድረክም ተከሄዷል፡፡ በዞኑ የሚከናወኑ የፓርቲና መንግስት ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራትና በማስፈጻም የህዝቡን ተጠቃሚነት በተጨበጭ ለማረጋገጥ በቀጣይም አጽኖት ልሰጠዉ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡ መድረኩ በሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ በተከበሩ በአቶ መሀመድከማል ኑሪዬ የተመራ ሲሆን በጽ/ቤቱ የሚገኙ የፖለቲከና አቅም ግንባታ ዘርፍ፤የአደረጀጀት ዘርፍ፤የሲቪክ ተቋማትና ፖለቲከ ፓርቲዎች ዘርፍ፤የሀብት ልማት ዘርፍ፤የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች እንዲሁም የወጣቶች ሊግ እና ሴቶች ሊግ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን የየዘርፉ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጸጻም ሪፖርት አቅርበዉ ዉይይትም ተካሄዷል፡፡ በዚህ ወቅት በሩብ ዓመቱ በፓርቲ ግንባር ቀደም መሪነት ባተከናወኑት ተግባራት በየዘርፉ አንጸባራቂ ድሎች መመዝገባቸዉ ተገልጻዋል፡፡ የዉይይት መድረኩ በተለይም በዞኑ በ2016 በጀት ዓመት የባለፉት ሶስት ወራት በፓርቲና መንግስት ተግባራትን በተናባበና በተቀናጃ መልኩ ከመምራትና ከማስፈጸም የነበሩ ዉስንነቶችንና የተገኙ ጥንካሬዎችን በዝርዝር ገምግሟል፡፡ የፓርቲዉ ዘርፍ፤የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ

የደረሱ ሰብሎችን ፈጥኖ በመሰብሰብ ከአላስፈላጊ የምርት ብክነት መታደግ እንደሚገባ አቶ ሃጂ ኑርዬ የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳደሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አሳሰቡ ጥቅምት 18/2016 ዓ.ም ፣ሀላባ ቁሊቶ የደረሱ ሰብሎችን ፈጥኖ በመሰብሰብ ከአላስፈላጊ ብክነት መታደግ እንደሚገባ የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳደሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሃጂ ኑርዬ አሳሰቡ ወቅቱ አርሶአደሩ የለማውን ምርት የሚሰበሰብበት እንደመሆኑ መጠን ሁሉንም የቤተሰብ እና የአደረጃጀት አቅሞች አቀናጅቶ በመጠቀም በጊዜ የለንም መንፈስ በዘመቻ መልክ የደረሱ ሰብሎችን መሰብሰብ እንደሚገባ አሳስበዋል። የደረሱ ሰብሎች በተለይም በአሁኑ ሰዓት እየጣለ የሚገኘው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ አላስፈላጊ የምርት ብክነትን እንዳያስከትል አርሶ አደርን ጨምሮ ሁሉም ልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት በዞኑ የወጣቱን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ገለፀ ሊጉ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ አመት ዕቅድ አፈጻጸምም ሰሞኑን ገምግሟል። በዚህ ወቅት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት በድሩ ሎምቢሶ በዞኑ የወጣቱን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ጽ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በዞኑ በየደረጃው የሚገኙ ወጣቶችን ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ጽ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው ብለዋል። የመረጃው ምንጭ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት፣

በዞኑ የሚከናወኑ ሁሉም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የብልጽግና ፓርቲ እሳቤዎችን በላቀ ደረጃ የሚያሰርጹ መሆን እንዳላባቸው የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ገለፀ ጥቅምት 2016 የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ የዞን ማዕከል አጠቃለይ የፓርቲና መንግስት ተቋማት የሚዲያ ስራ እንቅስቃሴዎች ያሉበትን ደረጃ የሚገማግም የውይይት መድረክ ተካሄደዋል። የውይይት መድረኩ በተለይም በዞኑ በ2016 በጀት ዓመት የባለፉት ሶስት ወራት በፓርቲና መንግስት መስሪያ ቤቶች ሁሉንም የዲጅታል ሚዲያ አውታሮችን ተቋማዊ አድርጎ በተናባበና በተቀናጃ መልኩ ከመጠቀም አኳያ ያሉበትን በዝርዝር ተገምግመዋል። በዚህ ወቅት የዉይይት መድረኩን የመሩት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊዎች አቶ በድሩ ከድር በቀጣይ በዞኑ የሚከናወኑ ሁሉም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የብልጽግና ፓርቲ እሳቤዎችን በላቀ ደረጃ የሚያሰርጹ መሆን እንዳላባቸው ገልጸዋል። በተለይ ሁሉም የፓርቲና መንግስት ተቋማት የብልጽግና ኮሙኒኬሽን ስትራቴጂን ማዕቀፍን የተለበሰ የተቀናጃ የዲጅታል፤ የሚኒስትሪምና የህትመት ሚዲያዎችን አሟጠዉ በመጠቀም የተቋማቸዉን እና የዞኑን ብሎም የሀገርን መልካም ገጽታ ግንባታ አበክረዉ መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። አሁን የምንገኝበት ወቅት ዓለም በአንድ መንደር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተሳስራ በምትገኝበት በዚህ ዘመን ፣ፈተና የሆነውና የወል እውነታ እያጠለሻ የመጣው ሌላኛው ሐሰተኛ መረጃዎች ነባራዊ ሁኔታችንን የሚበክል ሆኖ መገኘቱን እና አሉታዊ ተጽዕኖ እያደረሱብን ነው ስሉም አቶ በድሩ ከድር ገልጸዋል። በሌላ መልኩ የማህበራዊ ሚዲያ ፕላት ፎርሞችን በመጠቀም እየተለቀቁ ባሉ ባልተጣሩ መረጃዎች ህዝብ፣ መንግስትና ፓርቲን ለመጉዳት የሚደረጉ አሉታዊ የተበከሉ መረጃዎች ስርጭት እንዲዳከም በየደረጃው ያለው ፎከል ፔርሴኖች የሚዲያ ተሳትፎውን ማሳደግ እንዳለበትም ጠቁመዋል። በቀጣይ ሁሉም የፓርቲዉ አመራርና አባላት በማህበራዊ ሚዲያዉ ከፌስቡክ ባለፈ የትዉተር፤ ትክቶክ፤ የዩቲዩብና ሌሎችንም አዳዲስ ፕላትፎርሞችን በመክፈትና በስፈት በመቀላቀል በተቋማቸዉ፤ በዞኑ፤ በክልሉ ብሎም በፌደራል ፓርቲ የሚላቀቁ የብልጽግና መልእክቶችን ላይክ፤ ሼር፤ ላይክ፤ ሼር፤ ገንቢ ኮማንት ከማድረግም ሌላ የፓርቲ እሳቤዎችን የሚመርዙ አሉታዊ ዘመቻዎችን በተቀናጃ መልኩ እንዲመክቱም አሳስበዋል። በየአከባቢው በተለያዩ ስሞች ተሰይመው የተፈበረኩ ሚዲያዎች የሚያሰራጩትን ሐሰተኛ መረጃዎች፣ አሉባልታዎችንና ጥቃቶችን ለመመከት ፎከል ፔርሴኖች የሚዲያ ተሳትፎ ይበልጥ ማሳደግ እንዳለበት አቶ በድሩ ከድር ገልጸዋል። ፎከል ፔርሴኖች የፓርቲውን እሳቤዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞችን በማስረፅ፣ በማስገንዘብና የአባላትን አቅም በመገንባት ላይ በማተኮር የታለመለትን ግብ ስኬት ለማረጋገጥ በየደረጃው ያለውን አደረጃጀት በማንቀሳቀስ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት መሠራት እንዳለበትም አሳስበዋል። ሚድያና ኮሚኒኬሽን ዘርፉ ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ረገድ የሚወጣውን ሚና አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። በዘርፉ በአፈጸጸም ወቅት የተስተዋሉ ዉስንነቶችን ፈጥኖ በማረም፤ የተገኙ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የተሳኩ ተሞክሮዎችን በማስፋት የፓርቲ እሳቤ ማእከል ያደረጉ የፓርቲና መንግስት ተግበራት ተዕመኒና ወቅታዊ መረጃ ለህዝቡ ተደራሽ ለማድረስ መሰራት እንደሚገባም በመድረኩ ተጠቁሟል፡፡ ከመድረኩ ላይ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ለተነሱ ሀሳብ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽ ማብራሪያ በመስጠት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በቀጣይ የውስጥ ኮሚውኒኬሽን ማጠናከር፤ አሉታዊ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎችን በተቀናጀ መንገድ መታገል፤ የማህበራዊ ሚዲያ ስራን ተቋማዊ ማድረግ፤ እና ሚዲያዉን ዲጅታላይዝ በማድረግ ማበልጻግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የጋረ መግባባት ላይ በማድረስ የዉይይት መድረኩ ተጠናቋል፡፡ በመድረኩ ላይ የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ምክትል ለላፊ አቶ ሰፊሮ ባሙድ ጨምሮ የዞን ማዕከል የፐብልክ ሰርቭስ ግንባር የህዋሳት የፖለቲከ ዘርፍ ሀላፊዎች፤ እንድሁም የፓርቲና መንግስት ተቋማት የማህበራዊ ሚዲያ የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ፎከል ፔርሴኖች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካለት ተገኝተዋል። # የዞኑ መ/ኮ/ጉ/መምሪያ

ጥቅምት 12/2016 ዓ.ም፣ሀላባ ቁሊቶ በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ሆነ በገጠሩ በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተማሪን የሚገድል ክትባት እየተሰጠ በሚል እየተነፈሰ በሚገኘው ሀሰተኛ ወሬ ማህበረሰቡ መረበሽ እንደሌለበት የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ የመምሪያው ኃላፊ አቶ አብደላ ሳይድ በዞኑ ስር በሚገኙት በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደርና በገጠሩ በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተማሪን የሚገድል ክትባት እየተሰጠ በሚል እየተነፈሰ በሚገኘው ሀሰተኛ ወሬ ሁን ተብሎ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማወክና ተማሪዎችን ለመረበሽ እንጂ በዞኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ የሚገኝ ምንም አይነት የህክምና ክትባት እንደሌለና ፈጽሞ መሰረተ ቢስ ወሬ መሆኑን አስታውቀዋል። ኃላፊው አክለውም የሚሰጥ የትኛውም አይነት ክትባት ከዞኑ ጤና መምሪያ ዕውቅና ውጪ እንደማይሆንና አሁን ላይ በትምህርት ቤት ደረጃ እየተሰጠ የሚገኝ ምንም አይነት ክትባት እንደሌላ ገልፀዋል። በመሆኑም በዞኑ የሚገኙ ሁሉም ተማሪዎች፣የተማሪ ወላጆችና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች እየተሰራጨ በሚገኘው በዚህ በሀሰተኛ መረጃ እንደይረበሹ በማሳሰብ ሁሉም ተማሪዎችን በመረጋጋት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ማድረግ እንዳለባቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፏል። የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ