602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
602
እኔ : ሁሉን : በሚችል : ሰማይና : ምድርን : በፈጠረ
በእግዚአብሔር : አብ : አምናለው
ደግሞም : በአንድ : ልጁ : በመንፈስ : ቅዱስ : በተፀነሰ
ከድንግል : ማሪያም : በተወለደ
በጴንጤናዊው : በጲላጦስ : ዘመን : መከራን : በተቀበለ : በተሰቀለ
በሞተ : በተቀበረ : ወደ : ሲኦልም : በወረደ
በሦስተኛውም : ቀን : ከሙታን : በተነሳ
ወደ : ሰማይም : በወጣ
ሁሉንም : በሚችል : በእግዚአብሔር : አብ : ቀኝ በተቀመጠ
በሕያዋንና : በሙታን : ሊፈርድ
ከዚያም : በሚመለስ : በጌታችን : በኢየሱስ ክርስቶስ : አምናለው
ደግሞም : በመንፈስ : ቅዱስ
በአንዲት : ቅድስት : የሐዋሪያት : ቤተክርስቲያን በቅዱሳን : አንድነት : በሐጢያት : ስርየት
በስጋ : ትንሳኤ : በዘላለም : ሕይወት አምናለው !
602
እንኳን አንተ እግዚአብሔር ሆይ
የሰራሀቸው ሰማይ እና ምድር
በኔ አይምሮ አይለኩም ×2
👏👏👏👏👏👏👏👏
አንተማ ትልቅ ነህ ሰማይን የሰራህ
አንተማ ትልቅ ነህ ምድርን ያፀናህ
🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌
የቱ ነው እሩቅ ሰፈር እዚያ ሚባልለት
አባቴ አንተ ከቶ ማትደርስበት
የቱስ ነው ከአይንህ የተሰወረ
ወድቆ በሸለቆ ሳታየው የቀረ
አሸዋው በምድር ቢሆን እንደክምር
አንተ ግን ታውቃለህ ሁሉንም በቁጥር
ትልቅ ነህ ክበር
አንተማ ትልቅ ነህ ሰማይን የሰራህ
አንተማ ትልቅ ነህ ምድርን ያፀናህ
📚#share
602
1ኛ ዮሐንስ 1
¹ ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤
² ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤
³ እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን።
602
Repost from PROPHETIC REALM
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ
(በይዲድያ ብሬ)
ከ7 ዓመት በፊት የተጻፈ...ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው!! በጨለማ የነበሩ የጠበቁት ብርሃን፤ በሞት አገር የተሰደድን የናፈቅነው ሕይወት፤ ነቢያት በትንቢት ዳዊትም በመዝሙራት የተናገሩለት መሲሁ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ዮሐንስ በወንጌሉም በመልእክቱም ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መስክሯል። በወንጌሉ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የሚገልጡ ምስክርነቶችን እንደዋቢ አቅርቦአል፡፡ እነዚህም፦ 1.የዮሐንስ መጥምቅ ምስክርነት /ዮሐ 1:34/ 2.የናትናኤል ምስክርነት /ዮሐ 1:49/ 3.የጴጥሮስ ምስክርነት /ዮሐ 6:69/ 4.የማርታ ምስክርነት /ዮሐ 11:27/ 5.የራሱ የጌታ ንግግር /ዮሐ 10:36/ ሰው በአባቱ ስም ለምን ይጠራል? የእናትነት ጉዳይ በእርግዝና ግልጽ ስለሆነ ከጥርጣሬ ነፃ ነው፡፡ አባትነት ግን በእምነት እንደሆነ እናውቃለን። ኢየሱስ ከድንግል ማርያም እንደ ተወለደ አይሁድም ያምናሉ፡፡ትልቁ ችግራቸው ምንጩን አለማወቃቸው አባቱ እግዚአብሔር እንደ ሆነ አለማመናቸው ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ይህ ምንጩን የሚያሳይ ታላቅ ምስክርነት ነው። ከመዳናችን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ምስክርነት ነው። የሐዋርያው ጴጥሮስ ምስክርነት፡- "ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።" ማቴ.16:16። ይህ ምስክርነት የእውነት አምድና የቤተክርስቲያን መሰረት ነው፡፡ የጃንደረባው ምስክርነት፦ "ፊልጶስም።በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ።" ሐዋ. 8:37። ጃንደረባው የተጠመቀው ይህን በእምነት መስክሮ ነው። የዮሐንስ ወንጌል መጻፍ አላማ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ሰው ሁሉ አምኖ ሕይወት እንዲሆንለት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን የማመን ውጤት የዘላለም ሕይወት መሆኑን ዮሐንስ በመልእክቱም ሰበከ። "ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።" 1ኛ ዮሐንስ 5:12:: ➡️ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ !! መልካም ቀን !!
602
Repost from Rohobot
📔ርዕስ፦ የጸሎት ንቅናቄ
👤ጸሐፊ፦ዶ/ር ደስታ ላንጋኖ
📑የገጽ ብዛት፦201
_https://t.me/robhot
https://t.me/robhot
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
🎸⚜️🎺ኢየሱስ እንደቃሉ ይመጣል🎺
602
ስትወድ_ብዙ
#ራሔል_አለማየሁ
#Kingdom_Sound
#ᴀᴍᴀᴢɪɴɢ #Gospel #song
#ሼር_ይደረግ 🙏
⌚️25:48 ደቂቃ | 💾 18.16MB
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
#react አድርጉት
(🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 )
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
Facebook | Telegram | Youtube
| Instagram | Imo | X(Twitter) |
#Join_now #Join #channel
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
🎸🎺#ኢየሱስ እንደቃሉ ይመጣል🎺
