602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
602
ፀሐይ አሽቆልቁላ በምዕራብ ስትጠልቅ፤
ለምሽት ተረኛ ለጨረቃ ስትለቅ፤
ጐኔን ላሳርፈው ከቀኑ ድካሜ፤
ስተኛ እንቅልፌ ሲያደርሰኝ በህልሜ፤
ህልሜ ቅዥእት ሆኖ ጨለማው በርትቶ፤
እጥፍ ሲሆን ሌቱ ሲረዝም ምሽቱ፤
አቤቱ ወደአንተ ድምጼን አሰማለሁ፤
ፈጥነህ እንደትመጣ እለምንሃለሁ፤
የሚረዳኝ የለምና ከጐኔ አትራቅ፤
የሚያግዘኝ የለምና ከጐኔ አትራቅ፤
የሚረዳኝ - (ሩት አመረ)
org-እየሩሳሌም ነጊያ
#share_ይደረግ 🙏
⌚️22:33 ደቂቃ | 💾 24.49𝙢𝙗
#react አድርጉት (👍🥰❤😍🔥 )
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
Facebook | Telegram | Youtube
| Instagram | Tiktok | X(Twitter) |
sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯
🎸⸻ 🔹 ለክብር ነው 🔹⸻🎺
602
ወዳጆቼ ማዕበሉ እጅግ ከባድ ቢሆንም መውጫ የሌለው ሚመስል ቢያስፈራም ንፋሱም የሚቆም ባይመስልም ወጀቡ ቢበዛም ያላቹበት condition ልክ እንደ ማዕበሉ ቢበረታም አያጠፋቹም ወጀብም ማዕበሉም የመጠው ንፋስም ፀጥ ረጭ ይላል ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ እግዚአብሔር አለ አትጠራጠሩ በብዙ እንቀጥላለን🙏
602
ሉቃስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ እንዲህም አለ፦ አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት።
¹² ከእነርሱም ታናሹ አባቱን፦ አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው።
¹³ ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፥ ከዚያም እያባከነ ገንዘቡን በተነ።
¹⁴ ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ፥ እርሱም ይጨነቅ ጀመር።
¹⁵ ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ፥ እርሱም እሪያ ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው።
¹⁶ እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር፥ የሚሰጠውም አልነበረም።
¹⁷ ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ፦ እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ።
¹⁸ ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥
¹⁹ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ።
²⁰ ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው።
²¹ ልጁም፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው።
²² አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ፦ ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት፥ ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ፤
²³ የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፥ እንብላም ደስም ይበለን፤
²⁴ ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር።
²⁵ ታላቁ ልጁ በእርሻ ነበረ፤ መጥቶም ወደ ቤት በቀረበ ጊዜ የመሰንቆና የዘፈን ድምፅ ሰማ፤
²⁶ ከብላቴናዎችም አንዱን ጠርቶ፦ ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ።
²⁷ እርሱም፦ ወንድምህ መጥቶአልና በደኅና ስላገኘው አባትህ የሰባውን ፊሪዳ አረደለት አለው።
²⁸ ተቈጣም ሊገባም አልወደደም፤ አባቱም ወጥቶ ለመነው።
²⁹ እርሱ ግን መልሶ አባቱን፦ እነሆ፥ ይህን ያህል ዓመት እንደ ባሪያ ተገዝቼልሃለሁ ከትእዛዝህም ከቶ አልተላለፍሁም፤ ለእኔም ከወዳጆቼ ጋር ደስ እንዲለኝ አንድ ጥቦት ስንኳ አልሰጠኸኝም፤
³⁰ ነገር ግን ገንዘብህን ከጋለሞቶች ጋር በልቶ ይህ ልጅህ በመጣ ጊዜ፥ የሰባውን ፊሪዳ አረድህለት አለው።
³¹ እርሱ ግን፦ ልጄ ሆይ፥ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፥ ለእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው፤
³² ዳሩ ግን ይህ ወንድምህ ሞቶ ነበረ ሕያው ስለ ሆነ ጠፍቶም ነበር ስለ ተገኘ ደስ እንዲለን ፍሥሐም እንድናደርግ ይገባናል አለው።
602
👁ስለ ፀሎት ትንሽ ትርጉም በአጭሩ 👁
👉ፀሎት የእሳትን ኃይል አጥፍቷል፤ 👉የአንበሶች አፍ ተዘግቷል፤
👉አመጽን ፀጥ አሰኝቷል፤
👉ጦርነት አቁሟል፤
👉አጋንንትን አስወጥቷል፤
👉የሞትን ሰንሰለቶች ሰባብሮአል፤ 👉👉የመንግስተ ሰማይን ደጆች ከፍቷል፤ 👉የእግዚአብሔርን መንግስት አስፋፍቷል፤
👉ከተሞችን ከጥፋት እንዲዲኑ አድርጓል፤
👉ፀሐይና ጨረቃም በቦታቸው እንዲቆሙ አድርጓል።
መጽሐፍ ስናገር፦“ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።”
— ያዕቆብ 5፥16
ስለዚህ ፀሎት እንዲሚገባ ያልተጠቀምነው ትልቁ ሀብትና ተቆፍሮ ተቆፍሮ የማያልቅ ማዕድን ነው ያልኩት።
602
ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ሰው ሆነ?
1,,,,, ሰውን ለማዳን (ድነት)
ሰው በኃጢአት ተለይቶ ነበር፤ የሰውን ቦታ የሚወክል ፍጹም ሰው ያስፈልግ ነበር።
ክርስቶስ ሰው ሆኖ ሞትን ተቀብሎ ኃጢአታችንን ከፍ አደረገ።
“የሰው ልጅ ሊያድን እንጂ ሊጠፋ አልመጣም (ሉቃስ 19፥10)
2,,,, እግዚአብሔርን ለመግለጥ
እግዚአብሔር ማን እንደሆነ በትክክል እንድንያውቅ፣ በሰው መልክ ተገለጠ።
“ቃልም ሥጋ ሆነ” (ዮሐንስ 1፥14)
3,,,, መካከለኛ (Mediator) ለመሆን
ክርስቶስ ሙሉ አምላክ ሆኖ እንዲሁም ሙሉ ሰው ሆነ፤ ስለዚህ በአምላክና በሰው መካከል አገናኝ ሆነ።
“አንድ አምላክ፥ አንድም መካከለኛ… ኢየሱስ ክርስቶስ” (1 ጢሞቴዎስ 2፥5)
4,,,, ለሰዎች ምሳሌ ለመሆን
እንዴት መኖር፣ መውደድ፣ መታዘዝ እንዳለብን በሕይወቱ አሳየን።
“እኔ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁ” (ዮሐንስ 13፥15)
5,,,ሰቃያችንን ለመካፈል
ረሃብ፣ ሕመም፣ ሀዘን ምን እንደሆነ ራሱ አሳየ፤ ስለዚህ የሚራራ መድኃኒት ነው።
“በሁሉ እንደኛ ተፈተነ” (ዕብራውያን 4፥15)
ባጭሩ 🙌
👉 ክርስቶስ ሰው ሆነ ሰውን ለማዳን፣ እግዚአብሔርን ለመግለጥ፣ መካከለኛ ለመሆን እና ፍቅሩን በተግባር ለማሳየት
ክርስቶስ ፍቅሩን በዚህ ልክ ካሳየ 🙏 ለሙስሊም ዎገኖቻችን ጥያቄ አለኝ አላህ የምትሉት ለሰው ልጅ ፍቅር ምን አሳየ ???
I want an answer, everyone participate 🙏
602
Repost from የእግዚአብሄርን ፈቀድ መድረግ MINISTRY
ሥላሴ(TRINITY)
ሥላሴ ምን ማለት ነው?
“ሥላሴ” የሚለው ቃል ከግዕዝ ቋንቋ የመጣ ሲሆን፣
ከ“ሠለሰ” የሚለው ግስ ይወጣል፤ ትርጓሜውም “ሦስት አደረገ” ማለት ነው።
[“ሠለሰ” → “ሦስት አደረገ”]
በእንግሊዝኛ ቋንቋ ደግሞ Trinity የሚለው ቃል፣
ከ Tri (ሶስት) እና Unity (አንድነት) የተጣመረ ሲሆን፣
“ሶስትነትን በአንድነት” ይገልጻል።
ሥላሴ የሚለው ቃል፦ የአምላክን አንድነት እና በአካል ሶስትነት ለማብራራት የምንጠቀምበት ሥነ-መለኮታዊ (ቴክኒካል) ቃል ነው።“ሥላሴ” የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ በቃል በቃል አልተጻፈም። ይህ ነገር ትምህርተ ሥላሴን ለመቃወም በሚነሱ አካላት በተደጋጋሚ የሚቀርብ ጥያቄ ነው። እነሱም፦ “ሥላሴ የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ የለም፤ እግዚአብሔርም ‘ሶስት ነኝ’ አላለም” ይላሉ። ነገር ግን ይህ ጥያቄ የመጽሐፍ ቅዱስን ጠቅላላ አውድና አተረጓጎም ያላማከለ የተሳሳተ ጥያቄ ነው። ምክንያቱም፣ የእምነት ዶክትሪኖች (Dogma/Doctrine) በአንድ ቃል ብቻ ሳይሆን፣ ከመላው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የሚወጣ ድምዳሜ ላይ ይመሠረታሉ። መጽሐፍ ቅዱስ በጠቅላላው አውድ፦ 👉 እግዚአብሔር አንድ አምላክ መሆኑን 👉 በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ሶስት አካላት መገለጡን በግልፅ ያስተምራል።
“ሥላሴ” የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ በቃል በቃል ባይገኝም፣ 👉 ሀሳቡን የሚገልጽ ትምህርት ግን በግልፅ ይገኛል።
602
.........አውርዱኝ በቃ
ማይገባኝ ሳለሁ መዝሙር ቀርቶ መኖር
የቁጣል ሳለሁ በሞቴ የምኖር
ምህረቱን አብዝቶ ቀጥሎልኝ እድሜ
ዘመን ካመጣልኝ እንዳመልከው ቆሜ
ፀጋን አድሎ እንድገልጠው ብርሃንን
በሰው ዘንድ ታውቄ ሳገኝ መድረክን
መዝሙሬ ደምቆ ጉባኤው ካልተፅናና
ከዳንኪራ አይለይም ካልታየ ህልውና
ቃልን ስተረትር ስደበድበው መስባኩን
አሜን በል እዛጋ እርገጥ መሬት እያልኩኝ
ከአሪያም ካልመጣ የክብርህ ደመና
አወይይይ ከንቱ ወሬ ንግግር ሆኗልና
ልብሴ ከላይ አምሮ ከረቫትና ሸሚዙ
መንፈስ ከሌለበት ብዙ ነው መዘዙ
አጋንንት ማስጮህ ድዉይ መፈወሱ
በትንቢት መገለጥ አዳራሽ ማመሱ
ካልታየ በፍሬ ትንቢት አካል ለብሶ😭😭
መንፈስህ ሳይነካው ሰው ከሄደ ተመልሶ😭😭
ፍቅርን ሰብኬ ስጡ አምጡ እያልኩ አስራትና በኩራት😭😭
እኔ ግን ካቃተኝ መኖር ስብከቴን በእውነት😭😭
ካላደርኩ ዘምሬ በኑሮዬ ጓዳ😭😭
ፍቅርን ሰብኬ ፍቅር እኔን ከከዳ😭😭
አውርዱኝ በቃ ከምስባኩ በገሀድ
ጌታዬ ይክበርበት በእውነትና መንገድ
ለምኔ ስብከቱ ዝማሬ ጋጋታ
መች ይጨበጨብልኝ ሳይከብርልኝ ጌታ
Prophet Apostle የወርሺፕ ዘማሪ
መሆን አልፈልግም የከንቱ አዝማሪ
ይገለጥ በፍሬ አካል ይልበስ ነብሳት ይዳኑ
ወንጌል በፅድቅ ይሰበክ ገሀነማይ ባዶ ይሁኑ
ሞት መውጊያው ይሰበር ይገለጥ መንፈሱ
ያዘነ ተፅናንቶ በቃልህ ድነው ይመለሱ
ይባረኩ ስዘምር ተስፋ ይሰንቅ ቀናቸው
ከእግዚአብሔር መንፈስ ጉልበት ይታነፅ ቅጥራቸው
በቃ !! በቃ እዛው በዛው ጉዞ ባለሁበት መሄድ
የየአባቴ መንፈስ በጉባኤው ይጓደድ
......................ስሙኝ👂👂
አልነበሩም ወይ ሀዋሪያት እኔንና አንተን
በጥላቸው ሙት ሲነሳ ሲያበሩ የታወሩትን
መች ኖሩ ለክብር ክብራቸውን ጥለው
ሲታሰሩ ተገርፈው ተጥሎ አንበሳ እንዲበላቸው
በሞታቸው ከበራ ከሰራ ወንጌል ተሰብኮ
መሰረቱ ሲናወጥ ሰምተናል በአምልኮ
እሱ ነው!!እሱ ነው አምልኮ እሱ ነው ክርስትና
አዎ እሱ ነው መኖር ሞቶ አኑሮናልና
እኔም በዘመኔ ካልታየ ጌታ ስቆም በመሰዊያ
ሰው መጥቶ ከተመለሰ ካልፈታ ማሰሪያ
አዎ አውርዱኝ ልሰወር እስካገኘው ጌታን
ስመላለስ እስኪሸተኝ እስክዳስስ ህልውናውን
ልንበርከክ ልሂድ በጉልበቴ
ኑሮዬን ልስበክ ላገልግል ከልቤ
ለታይታ ከሩጥኩኝ ይብቃ ያ ሩጫ
ጌታዬ ቀድሞ ይታይብኝ ያለ አንዳች ምርጫ
በደጅ ነውና ቀኑ ሙሽራው ሊመጣ
ሊሸልምና ሊፈርድ እንዲሁም ሊቀጣ
ቤቴን አሰናድቼ በፅድቅ ቅድስና
ኩራዜን ለኩሼ ነቅቼ እንደገና
ላየው እሻለሁ አክሊሌን ጠብቄ
መንፈሱ እንዲረዳኝ አውቃለሁ ጠንቅቄ
✍✍✍በጌታሁን አናሞ✍✍✍
602
እስከ ሽምግልና ድረስ እኔ ነኝ፥ እስከ ሽበትም ድረስ እሸከማችኋለሁ፤ እኔ ሠርቻለሁ እኔም አነሣለሁ፤ እኔ እሸከማለሁ እኔም አድናለሁ።
— ትንቢተ ኢሳይያስ 46:4
602
Repost from Gospel Revival Movement Ethiopia 🌏
#ወንጌልን_በትክክል_ለመስበክ_አራት_ህጎች አሉ፡፡
⭐️የመጀመሪያው ህግ⭐️
“ እግዚአብሔር ይወድሃል ስለዚህም ለሕይወትህ አስደናቂ የሆነ ዕቅድ አዘጋጅቶልሃል፡፡ “
… በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዷልና፡፡ (ዮሐ 3፤16)
እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ፡፡ (ዮሐ 10-10)ነገር ግን ሰዎች ሁሉ ይህንን ሙሉና አርኪ ሕይወት አልተለማመዱም ምክንያቱም
⭐️ሁለተኛው ህግ⭐️
#ሰው_ኃጢያተኛ_ነው፡፡
በዚህም ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይቷል፡፡ ስለዚህም የእግዚአብሔርን ፍቅርና ዕቅድ ማወቅና በሕይወቱ መለማመድ አልቻለም፡፡ ሁሉ ኃጢያትን ሠርተዋልና፤ የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሏቸዋል፡፡(ሮሜ 3፤23)
⭐️ሦስተኛው ህግ⭐️
“ ለኃጢያታችን ክፍያ ወይም ካሳ #እግዚሐብሔር_ያቀረበው ብቸኛ ነገር #ኢየሱስ_ክርስቶስ ነው “
በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ኃጢያታችን ይቅር ተብሎልን ከእግዚሐብሔር ጋር የሚኖረን ትክክለኛ ግንኙነት ይታደስልናል።” ሮሜ 5፡8 እግዚሐብሔር ለኛ ያለውን ፍቅር ሲያረጋግጥልን እንዲህ ይነግረናል፡ “ነገር ግን ገና ኃጢያተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለኛ ሞቷአልና።
” ድነታችንን ለማረጋገጥ ምን ማወቅ እንዳለብንና ማመን እንደሚገባን 1ኛ ቆሮ 15፡ 3-4 እንዲህ ያስረዳናል “…መጽሐፍም እንደሚል ክርስቶስ ስለኃጢያታችን ሞተ፣ተቀበረም። መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሳ።”
የድነት ብቸኛ መንገድ መሆኑን ራሱ ኢየሱስ በዮሐንስ 14፡ 6 “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ። በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም” ሲል ተናግሯል።
👉 ይህንን የድነት አስደናቂ ስጦታ እንዴት ላገኘው እችላለሁ?
⭐️ አራተኛው ህግ ⭐️
“ የድነትን ስጦታ ለመቀበልና እግዚሐብሔር ለህይወታችን ያለውን አስደናቂ እቅድ ለማወቅ እምነታችንን በኢየሱስ ክርስቶስ መጣልና አዳኝነቱን ማወቅ አለብን።”
ዮሐንስ 1፡ 12 በዚህ ሁኔታ ያብራራዋል፡ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፣ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚሐብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው።” ዮሐ 1;12 በግልፅ እንዲህ ያስቀምጠዋል
“በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተሰቦችህም ትድናላችሁ።” እኛ የምንድነው በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ባለን እምነትና በፀጋው ነው(ኤፌሶን 2፡ 8-9)
🌟🌟Share_the_Gospel 🌟 🌟
🔥 #የወንጌል_እሳት 🔥
#Gospel_Revival_movement_Ethiopia
ሉቃስ 12:49፤ “በምድር ላይ እሳት ልጥል መጣሁ፥ አሁንም የነደደ ከሆነ ዘንድ ምን እፈልጋለሁ?
🌟 #Share #story 🌟
✨ተቀላቀሉን ✨
⚜️ @GospelMovementEthiopia ⚜
602
🌸 ጨለማው ያልፋል! 🤗
በህይወታችሁ ውስጥ ነገሮች ሁሉ የጨለሙ ቢመስሏችሁም፣ እግዚአብሔር ግን አሁንም በዙፋኑ ላይ ነው። እናንተ የምታዩት ማዕበሉን ነው፤ እርሱ ግን ማዕበሉን የሚያቆመውን ኃይል በእጁ ይዟል። ዛሬ ላላችሁበት ጭንቀት የሰማይ መልስ ቅርብ ነው።
"በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፥ የልባችሁንም መሻት ይሰጣችኋል።" (መዝሙር 37:4)
602
መንፈስ ቅዱስ በኛ የሚኖረው እኛን ለማኖር ነው እንዲ በኛ ለመኖር አይደለም፣ ከዘለዓለም በፊት የለምን እርዳታ የሚኖር መለኮት ነው መንፈስ ቅዱስ የለኝ መኖር ይችላል ፣እኛ ግን ያለ እርሱ መኖር አንችልም ለምን ከተባለ የህይወት ውሃ ነው ።
ዮሐንስ 7 (John)
38፤ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።
602
የእለቱ መልዕክት
የአለም ብርሃን የሆንከው /ሽው አንተ/ቺ📖ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ እሱ የአለም ብርሃን እንደሆነ ተናግሯል ደግሞም ነው!! እርሱ ሲያርግ ግን አለም ይሄንን ብርሃን እንድታጣ አልፈለገም ነበር ስለዚህ አርሱ በምድር ሳለ የአለም ብርሃን☀️ ነው(ሁሌም ነው) 👉ሲያርግ ግን ሌሎች ብርሃናትን 🌏ለአለም አዘጋጅቶላት ነበር የሄደው እርሱም ደግሞ እያነበብክ ያለኸው አንተ ነህ አንቺ ነሽ ☑️በዚህኛው ግን የዘፍጥረት 1 አይነቶቹ ፀሐይ🌞 እና ጨረቃ🌙 አይደሉም አለም ከዚያ የሚልቅ የብርሃን ምንጭ አግኝታለች እነርሱም የክርስቶስ ተከታዮች(Christians) እኔና አናንተን ማለቴ ነው 👉አነዚህ እንደ ፀሐይ☀️ አይደሉም ምክንያቱም በቀን ብቻ አያበሩም አንደ ጨረቃም🌗 አይደሉም ለመታየት እስኪመሽ አይጠብቁም ምክንያቱም Already ሊሰወሩ በማይችሉበት ከፍታ ላይ🤷♂ የተቀመጡ ስለሆኑ ማለት ነው 🌞ፀሐይ በአንድ ጊዜ አለምን በሙሉ የማብራት አቅም የላትም አንዱን የአለም ክፍል ስትጎበኝ ሌላኛው የአለም ክፍል መጨለም ይኖርበታል 😎አነዚህኞቹ ግን ኢየሱስ እንዳለው ለኢትዮጵያ🇪🇹 ብቻ አልተዘጋጁም ለአፍሪካም እንደዛው ነገር ግን 😱አለምን ሁሉ አንዲያበሩአት የተዘጋጁ ናቸው 💯ለምድር ከምንም በላይ የሚያስፈልጓት ፀሐይና ጨረቃ አይደሉም የክርስቶስን ህይወት የተሸከምከው/ሽው አንተ ነህ አንቺ ነሽ እራስህን/ሽን እንደ ተራ ሰው መመልከት አቁም/ሚ ለዚህ ምድር በጣም አስፈላጊው ሰው አንተ ነህ አንቺ ነሽ ልብ በሉ በአለም ፍፃሜ አውሬው መለቀቁን ብቻ ሳይሆን አማኞች እንደሚነጠቁ አትርሱ ያ ማለት ምድር ብርሃኖቿን ስትነጠቅ ማለት ነው ያኔም ፍፃሜ የሚሆነው አውሬው ስለሚፈታ ብቻ ሳይሆን ብርሃኖቿን(አንተን አንቺን) ስለምታጣም ጭምር ነው ✅በውስጥህ በውስጥሽ ያለውን የክርስቶስን ብርሃን ለመገናኘት ፍጥረት በናፍቆት የሚጠብቁት አንተ ነው አንቺን ነው በጣም አስፈላጊ ሰው ነህ አስፈላጊ ሰዉ ነሽ
602
#rivivalforethiopia
ቤቱን ለማስተካከል እግዚአብሔር በምድር ላይ ያለው ሰው አንተ ነህ።
በአንድ ጥናት ውስጥ በተገኘው መረጃ መሰረት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከሚገኘው ምዕመን ውስጥ 80 በመቶው ምን እየተካሄደ እንዳለ እንኳን የማያውቅ ደርሶ ሄያጅ ሲሆን 15 በመቶው ደግሞ ምን እየተካሄደ እንዳለ ጠንቅቆ የሚያውቅ ነገር ግን በማንኛውም ሁኔታ እጁን ማስገባት የማይፈልግ እና የማይመለከተው ሆኖ የሚገኝ እንደ ሆነ ያሳያል።
ከቀረው 5 በመቶ ውስጥ 3 በመቶው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዋና አጀንዳ የሆኑ የቀረውን ምዕመን እና አስተዳዳር የሚበጠብጡ አጀንዳዎች ሲሆኑ 2 በመቶው ብቻ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ንቁ ተሳታፊዎች ሆነው በቤተ ክርስቲያን እንደሚገኙ ይጠቁማል።
ይህም ቤተ ክርስቲያንን ግለሰቦች እንደፈለጉ ለግል ጥቅማቸው የሚያዉሏት የቤተሰብ ንብረት ከማድረግ ጀምሮ፣ ሃላፊነቷን የረሳች፣ ንጉሷን ከመድረኳ ያራቀች፣ በዚህ አለም ነገር የተጠላለፈች፣ ማንም እንደፈለገ የሚፈነጭባት የወንበዴዎች ዋሻ እንድትሆን አድርጓታል።
ከላይ በተጠቀሰው ቁጥር መሰረት አብዝሃኛው ሰው ሐይማኖተኛ ብቻ የሆነ፣ እምነቱን በውል ያልተረዳ፣ በመጣው ሁሉ የትምህርት ነፋስ ወዲህና ወዲያ የሚወሰድ፣ የእግዚአብሔር ቤት ነገር የማይገደው ባይተዋር ነው። የቀረው ደግሞ እያወቀ ለማስተካከል እጁን የማያስገባ ወይም አጀንዳን የሚሰጥ በጥባጭ መሆኑ በመዳናችን ውስጥ ያገኘነውን የመንግስቱ ወራሽነት እና ባለቤትነት የዘነጋንበት፣ የተሰጣትን የነፍሳት መናጠቅ ኃላፊነት ቸል ያልንበት ጉዳይ ነው።
እንደገና_በህይወት_መኖር /ሪቫይቫል ለኢትዮጲያ/ ከሚለው መፅሐፍ ገፅ 418 ጀምሮ ካለው ክፍል የተወሰደ
ሙሉ መፅሃፉን ለማግኘት ከታች ያለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑት!
https://t.me/Intruthlife/5
