en
Feedback
Kolfe P.P - ብልፅግና

Kolfe P.P - ብልፅግና

Open in Telegram
1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
ኢትዮጵያ በመስዋዕትነት የተገነባች ከራሳቸው በላይ ከህይወታቸው አስቀድመው የሚወዷት ልጆች ያሏት ሀገር ነች። መስዋዕትነት ሀገርን አፅንቷል አንድነትን ክብርን ታሪክን ይቻላልን አላብሷል። ኢትዮጵያዊያን በሀገር ጉዳይ ለመጣ የማይመለሱ ታላቅ ታሪክ የሰሩ እየሰሩም ያሉ በብዙ ጀግንነት በብዙ መስዋዕትነት በጋራ ያነፅናት ቤታችን ነች። የአፍሪካ ኩራት የጀግንነት ልክ አዋቂ ሁሉም ነገር ከሀገር በታች መሆኑን የተረዱ ልጆች ያሏት ድንቅ ሀገር አለችን። መስዋዕትነት ሲባል በጦር ሜዳ የምናደርገው ተጋድሎ ትልቁ ቢሆንም እሱ ብቻ ግን አይደለም። በተሰለፈበት ሁሉ አለመመቻቸትን ችሎ፣ ሌብነትን ተፀይፎ፣ ሌብነትን ታግሎ፣ ህይወት አደጋ ላይ የሚጥል ትግል እንኳን ቢገጥም ለሀገር ሲባል የሚደረግ ትንቅንቅ፣ በአስቸጋሪ የተፈጥሮ ቦታ ውስጥ ለመሰረተ ልማት ዝርጋታ እራስን መስጠት፣ በብዙ ዘርፎች መስዋዕትነት አለ። ኢትዮጵያ በሚያስፈልጋት ቦታ ሁሉ ተሰልፎ የሚመጣውን ዋጋ ሁሉ መቀበል መቻል የመስዋትነት መገለጫ ነው።  የሀገር መስዋዕትነት በምንም የሚለካ አይደለም። ለሀገር ዋጋ የሚከፈለው ሀገር መልሳ ውለታ ትከፍለኛለች ከሚል የተሻገረ የአፍቅሮተ ሀገር መነሻ ነው። ለሀገር መስዋዕትነት የተዘጋጀ የማያግባባ ጉዳይ ቢኖር፣ በግል ጉዳይ ምቾት ማጣት ቢያጋጥም፣ የህይወት ዋጋ የሚያስከፍል ጉዳይ ቢገጥም ሁሉም ከሀገር በታች ናቸው ይላል። ማለት ብቻ ሳይሆን በተግባርም ዋጋ ከፍሎ በመስዋዕትነት ሀገር ያፀናል። ኢትዮጵያዊያን ከጥንት እስከዛሬ ያልተቀየረ ጀግንነት፣ ያልተቀየረ ሀገር ወዳድነት፣ ያልተቀየረ የመስዋዕትነት ከፋይ ጀግንነት የተላበስን ነን። በየዘርፉ፣ በተሰማራችሁበት ሁሉ ለሀገር መስዋዕትነት የምትከፍሉ የተነገረላችሁ፣ የተዘመረላችሁ ጀግኖች፣ ያልተዘመረላችሁ፣ ያልተነገረላችሁ ጀግኖቻችን የሰራችሁትም የከፈላችሁት ዋጋም ሀገር አፅንቶ ሀገር ለማሳደግ ሰርቷል እና ክብራችሁ ሀገር፣ ደስታችሁ የሀገር ፅናት ነውና ገድላችሁ ህያው ሆኖ ይኖራል። በየቀኑ ህይወት ያለ ስስት ለመስጠት የምትዘጋጁ በአስፈለገ ጊዜ የምትከፍሉ ጀግናው ሀገር መከላከያ ሰራዊታችንን በበርካታ መስዋዕትነት ሀገር የምታፀኑ ጀግኖች ክፍያችሁ የሀገር አንድነት የህዝብ ሰላም ነውና ክብር ይገባችኋል። ተፈጥሮ ያደላት የ13 ወር ፀጋ ባለቤት ኢትዮጵያ በመስዋዕትነት አፅንተን በአርቆ አሳቢነት ገንብተን ለትውልድ ለማስተላለፍ የምናደርገው ጥረት አጠንክሮ መቀጠል ይገባል። ሁላችንም በተሰማራንበት መስዋዕትነት ለመክፈል በመዘጋጀት የከበረች የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ እናሻግር!

photo content
+1

ማገልገል ክብር ነው። ማገልገል ክብር ነው። ህዝብን ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው። ኢትዮጵያ ታሪክ ሰሪ ልጆች ያሏት ሀገር ነች። አመቱን ሙሉ በተሻለ የአገልጋይነት መንፈስ ህዝብን ለማገልገል በዛ
+9
ማገልገል ክብር ነው። ማገልገል ክብር ነው። ህዝብን ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው። ኢትዮጵያ ታሪክ ሰሪ ልጆች ያሏት ሀገር ነች። አመቱን ሙሉ በተሻለ የአገልጋይነት መንፈስ ህዝብን ለማገልገል በዛሬው የአገልጋይነት ቀን የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ አስተዳደር በርካታ ተግባራትን በመከወን ላይ ነው። አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ፣ አቶ ሙሉጌታ ጉሉማ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ክፍሌ ለማ የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ አስተዳደር ምክትል ስራ አስፈፃሚ፣ አቶ አለማየሁ ፍቃዱ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ፣ አቶ ወርቅነህ ሞርካ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ድርጅት ዘርፍ ኃላፊ ሌሎች የክ/ከተማው ኃላፊዎች፣ ባለሞያዎች፣ ከትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀምሮ በርካታ የአገልግሎት ሰጭነት ተግባራትን በማከናዎን ላይ ናቸው። ዛሬ አመቱን ሙሉ በተሻለ ለማገልገል ቃል የምንገባበት እለት ነው። መልካም የአገልጋይነት ቀን ይሁንለዎ!

ተገልጋይ ንጉስ አገልጋይነት ክብር ነው። ኢትዮጵያ የራሷ የጊዜ አቆጣጠር ያላት የ13 ወር ፀጋ ባለቤት ነች። ኢትዮጵያ የቅድመ ስልጣኔ ባለቤት መሆኗን ከሚያሳዩን በርካታ ጉዳዮች አንዱ የራሷ የጊዜ አ
ተገልጋይ ንጉስ አገልጋይነት ክብር ነው። ኢትዮጵያ የራሷ የጊዜ አቆጣጠር ያላት የ13 ወር ፀጋ ባለቤት ነች። ኢትዮጵያ የቅድመ ስልጣኔ ባለቤት መሆኗን ከሚያሳዩን በርካታ ጉዳዮች አንዱ የራሷ የጊዜ አቆጣጠር ያላት ወራቶቿሞ በ13 ወር ፀጋ የተሞላ መሆኑ ነው። በዛሬው 01/13/2015 እለት ጳግሜ አንድ የአገልጋይነት ቀን ስያሜ ተሰጥቶታል። ኢትዮጵያ የብዙ ሀገር ወዳድ ልጆች እናት ነች። ብዙዎች ለሀገር ሲሉ ህይወት የከፈሉ ዳር ድንበሯን ያስከበሩ ልጆች አሏት። ልክ እንደዛው ሁሉ በአገልግሎቱ ዘርፍ የተሰማራን ሰዎች የምናገለግለው ወገኖቻችንን ኢትዮጵያዊያንን መሆኑን መረዳት ይፈልጋል። ማገልገል ክብር ነው የሀገር ወዳድነት መገለጫ። ማገልገል ከውስጥ የመነጨ የሀገር ወዳድነት ስሜት ነው። የሚቆጣጠረን አካል ሲኖር ግልጋሎት የምንሰጥ ከሆነ የአገልጋይነት ትርጉሙ አልገባንም ማለት ነው።  ሀገር ማለት ሰው ነው ሰው ማለት ሀገር ከሆነ ደግሞ የምናገለግለው ልንሰዋላት ዝግጁ ለሆንላት ሀገራችን ነው። ክብር የሆነውን አገልግሎት መስጠት በዛሬው እለት የአገልጋይነት ቀን ተብሎ ተሰይሟል። አመቱን ሙሉ አገልጋይነት አለ። ዛሬ ግን ለአገልጋዮቹ ክብር የሰጠ ተገልጋዮቹን ንጉስ ያደረገ ያገልግሎት ቀን ተብሎ ስያሜ የተሰጠበት ነው። አገልጋይነት ክብር ነው፤ ወገንን ሀገርን ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው! መልካም የአገልግሎት ቀን!

ኢትዮጵያዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ፅኑ መሠረት ላይ የተገነባ ማንነት ነው! ብዝሃ ማንነት ሲኖር አንድነትን ከሚፈጥሩ መሠረቶች አንዱ ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነው። ወንድማማ
ኢትዮጵያዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ፅኑ መሠረት ላይ የተገነባ ማንነት ነው! ብዝሃ ማንነት ሲኖር አንድነትን ከሚፈጥሩ መሠረቶች አንዱ ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነው። ወንድማማችነት/እህትማማችነት አንድነትን የማጠንከሪያ ዋልታና ማገር ነው። ኢትዮጵያዊያን ህብረ - ብሔራዊነታችን ከተፈጥሮ ያገኘነው ውብ ማንነታችን ነው። በወንድማማችነት/ እህትማማችነት መሰረት ላይ የሚገነባ ህብረ- ብሄራዊ አንድነት ከፍቅር፣ ፍትህ፣ መተሳሰብ እና አብሮነት ሌላ አማራጭ ሊያደርግ አይችልም፡፡ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን አጠናክረን ጠንካራ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

ብልፅግና - የአሁኑም የመጪውም ትውልድ ፓርቲ ! ኢትዮጵያችን የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ማንነት፣ ቋንቋ፣ እምነት፣ ባህል ህብርም መገኛም ናት፤ እጅግ በጣም ሰፊ ብዝሃነት ያለባት ድንቅ ሀገር ናት።
ብልፅግና - የአሁኑም የመጪውም ትውልድ ፓርቲ ! ኢትዮጵያችን የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ማንነት፣ ቋንቋ፣ እምነት፣ ባህል ህብርም መገኛም ናት፤ እጅግ በጣም ሰፊ ብዝሃነት ያለባት ድንቅ ሀገር ናት። የብዝሃነት ፀጋዋ ነገ ሁለንተናዊ ብልፅግና የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት የሚያስጎመጅ ሰናይ ዕድል እንጂ፣ ስጋቷ ሊሆን በፍፁም አይገባም። መሪ ፓርቲያችን ብልፅግናም ይህንን መልካም ዕድል በመጠቀም በአንድ በኩል ብዝሃነታችንን በአግባቡ የሚያስተናግድበትን ፣በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራዊ አንድነታችንን የሚያረጋግጥበትን እውነተኛ ህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓት ለመገንባት እየሰራ ይገኛል። ይህ ደግሞ ዛሬን ለማለፍ ብቻ ሳይሆን ነገንም ሰላምና አንድነት፣ እኩልነትና ብልፅግና ሰምረውልን እንደ አገርና ህዝብ ለመኖር ያስችለናል፤ ለዚህም ነው ብልፅግና - የአሁኑም የመጪውም ትውልድ ፓርቲ ነው የምንለው።

የፓርቲያችን ብልፅግና ዋና አላማ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው፤ ይህንንም ለማሳካት መላው ህዝብን አሳትፎ በመስራት ላይ ይገኛል። በወንድማማችነት መርህ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ጠብቀን
የፓርቲያችን ብልፅግና ዋና አላማ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው፤ ይህንንም ለማሳካት መላው ህዝብን አሳትፎ በመስራት ላይ ይገኛል። በወንድማማችነት መርህ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ጠብቀን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንትጋ! መልካም ቀን ይሁንለዎ! kolfe prosperity party - ብልፅግና

ስኬት አላማችን እስከሚሳካ ያለምንም ተስፋ መቁረጥ በመስራት የሚመጣ ነው። ስኬት የልፋት፣ የጥረት፣ የትጋት፣ ተስፋ ያለመቁረጥ፣ የትብብር ድምር ውጤት ነው። ስኬታማ ለመሆን ዋናው መዘንጋት የሌለብን
ስኬት አላማችን እስከሚሳካ ያለምንም ተስፋ መቁረጥ በመስራት የሚመጣ ነው። ስኬት የልፋት፣ የጥረት፣ የትጋት፣ ተስፋ ያለመቁረጥ፣ የትብብር ድምር ውጤት ነው። ስኬታማ ለመሆን ዋናው መዘንጋት የሌለብን ጉዳይ ለማሳካት በተሰለፍንበት አላማ ላይ መፅናትን ነው። የስኬት ታሪኮች ዋና ሚስጥር በመስራት ውስጥ መፅናት ነው። ብልፅግና ለሀገራችን እንዲሳካ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን መሻት ነው። መሻት እውነት ሆኖ ማየት የሚቻለን በተሰማራንበት ለስኬትና ለውጤት ስንተጋ ነው። ሁልተናዊ ብልፅግና እውንነት የሁል ጊዜ ትጋት ይጠይቃል። በተሰማራንበት በትጋት በመስራት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!

አፍሪካ የአለም የተፈጥሮ ሀብት ማማ ነች!! አፍሪካዊያን በራሳችን ምንም ነገር ማድረግ እንችላለን የሚለው የኢትዮጵያ አቋም ከምንም ተነስቶ በግብታዊነት ሳይሆን ያለንን አቅም ጠንቅቆ ከማወቅ የመነጨ
አፍሪካ የአለም የተፈጥሮ ሀብት ማማ ነች!! አፍሪካዊያን በራሳችን ምንም ነገር ማድረግ እንችላለን የሚለው የኢትዮጵያ አቋም ከምንም ተነስቶ በግብታዊነት ሳይሆን ያለንን አቅም ጠንቅቆ ከማወቅ የመነጨ ነው። አፍሪካ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር አላት። አብዛሃኛው የሰው ሃይል ወጣት ሰሪ ሀይል ነው። ኢትዮጵያ አፍሪካ ከአለም አቀፍ ተቋማት ለአለም እያበረከተች ያለችውን አስተዋፅኦ ታሳቢ ያደረገ ጥቅም ማገኘት አለባት የሚለው ፅኑ አቋሟ ይህንን ታሳቢ ያደረገ ነው። ኢትዮጵያ ሀሳብ ስታመነጭ ጠቅላላ የአፍሪካ ሀገራት ይከተሏታል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተስፋና ተምሳሌት ነች። ሁሉም አፍሪካ የኢትዮጵያ መጠንከር ያጠነክረዋል። በአለም ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑት የነፃነት ታጋዩ ኔልሰን ማንደላን ወታደራዊ ስልጠና በመስጠት ካበረከተችው አስተዋፅኦ ተጨማሪ ዛሬ ላይ ስንዴን ከነጭ ልመና ወጥቶ በራስ አምርቶ ለሌሎች መትረፍ ይቻላል የሚል ትምህርት በተግባር ሰጥታለች። እኛ አፍሪካዊያን ለአለም የሚተርፍ ሀብታችንን በራሳችን ማልማት ይኖርብናል። ተፈጥሮ ሀብታችንን በራሳችን አቅም ለጥቅም በማዋል ከራስ የተረፈ ለአለም የመትረፍ ውጥናችንን ማሳካት ይጠበቅብናል። መልካም ቀን ይሁንለዎ!

የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያችን እጣ ፋንታ እየወሰነ ያለ ትውልድ ነው። የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች የነገ ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት እውን ያደረገች መሆን ነው። ፓርቲያችን ብልፅ
የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያችን እጣ ፋንታ እየወሰነ ያለ ትውልድ ነው። የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች የነገ ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት እውን ያደረገች መሆን ነው። ፓርቲያችን ብልፅግናም ይህንኑ እውን ለማድረግ እየሰራ ያለ በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ ፓርቲ ነው። ብልፅግና የዛሬውን ሀገራዊ ብልፅግና እውን ለማድረግ የሚሰራው የነገው ትውልድ ጥቅም እና ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ ነው። የመደመር ትውልድ የነገዋ ኢተዮጵያ ልዕለ ሃያል በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች በልጆቿ ወንድማማችነት/ እህትማማችነት መሰረት ላይ ህብረ ብሄራዊ አንድነቷን ያፀናች ሀገር ለማድረግ እየሰሩ ያሉ ናቸው፡፡ ለትውልድ የሚሻገር ታሪክ ሰሪ ትውልድ እውን ሆኗል። ሁላችንም የድርሻችንን ኃላፊነት በመወጣት አሻራችን ለትውልድ እናሳርፍ!! መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ፈተና የጠንካሮች ነጥሮ መውጫ መንገድ ነው። የመደመር ትውልድ በርካታ የሚያስደምሙ ስኬቶችን እያስመዘገበ ያለው በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ነው። በተመቻቸ መንገድ ውስጥ፣ አልጋ በአልጋ በሆነ ጉዞ
ፈተና የጠንካሮች ነጥሮ መውጫ መንገድ ነው። የመደመር ትውልድ በርካታ የሚያስደምሙ ስኬቶችን እያስመዘገበ ያለው በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ነው። በተመቻቸ መንገድ ውስጥ፣ አልጋ በአልጋ በሆነ ጉዞ ላይ ደካማውም ጠንካራውም እኩል መጓዝ ይችላሉ። ለውጥ የማያመጡ ድርጊቶች ብዙ ፈተና አይበዛባቸውም። አለምን የቀየሩ ሀሳቦች፣ ተግባሮችና ስራዎች ግን በበርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ ያለፉ ናቸው። ወርቅ በእሳት ይፈተናል እንድሉ የሁለንተናዊ ብልፅግና ጉዞ ፈተናዎች እየገጠሙት በፈተና ሳይበገር ወርቃማ ስኬት እያስመዘገበ ቀጥሏል። በሚገጥሙ ፈተናዎች ሳንበገር የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በምናደርገው ጉዞ ውስጥ እንቅፋቱን ለመስፈንጠር ችግሩን ወደ እድል ለመቀየር መስራት የመደመር ትውልድ አደራ ነው። የመደመር ትውልድ ዛሬ የሚገጥሙትን የጉዞ እንቅፋቶች እያፀዳ ተጉዞ ለነገው ትውልድ ጥቅም ፍላጎት መሟላት እየሰራ ያለ ትውልድ ነው። ሁላችንም ኃላፊነታችንን በመወጣት ለትውልድ የሚሻገር ታሪክ በመሰራቱ ሂደት ላይ አሻራችንን እናሳርፍ! መልካም ቀን ይሁንለዎ!

ኢትዮጵያዊያን በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተዋበ ማንነት አለን ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የጠነከረ ነው። አንዱ ለአንዱ ግርማ ሞገሱ የጥንካሬው ምንጭ ነው። ህብረ ብሔራ
ኢትዮጵያዊያን በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተዋበ ማንነት አለን ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የጠነከረ ነው። አንዱ ለአንዱ ግርማ ሞገሱ የጥንካሬው ምንጭ ነው። ህብረ ብሔራዊ አንድነት በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የታሰረ ሲሆን የጥንካሬ ምንጭ ይሆናል። ለጥላት አስፈሪ ግርማ ሞገስ የተላበሰ ለወዳጅ የኩራት ምንጭ የሆነ ማንነትን ያላብሳል። አንድነታችንን አጠንክረን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ፍቅር አስረን የጋራ ቤታችን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንትጋ! መልካም ቀን ይሁንለዎ!

ኢትዮጵያዊያን በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተዋበ ማንነት አለን ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የጠነከረ ነው። አንዱ ለአንዱ ግርማ ሞገሱ የጥንካሬው ምንጭ ነው። ህብረ ብሔራ
ኢትዮጵያዊያን በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተዋበ ማንነት አለን ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የጠነከረ ነው። አንዱ ለአንዱ ግርማ ሞገሱ የጥንካሬው ምንጭ ነው። ህብረ ብሔራዊ አንድነት በወንድማማችነት/ እህትማማችነት የታሰረ ሲሆን የጥንካሬ ምንጭ ይሆናል። ለጥላት አስፈሪ ግርማ ሞገስ የተላበሰ ለወዳጅ የኩራት ምንጭ የሆነ ማንነትን ያላብሳል። አንድነታችንን አጠንክረን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ፍቅር አስረን የጋራ ቤታችን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንትጋ! መልካም ቀን ይሁንለዎ!

በጎነት ሰው በመሆናችን ብቻ በዚህች አለም ለሌላው የሚጠቅም፣ የሚያስደስት፣ ችግሩን የሚፈታ ወይ የሚያቃልል ተግባር መፈፀም ነው። በጎነት ሁሉም ሰው ማድረግ የሚቻለው የልብ ቅንነትን ብቻ የሚጠይቅ ተ
በጎነት ሰው በመሆናችን ብቻ በዚህች አለም ለሌላው የሚጠቅም፣ የሚያስደስት፣ ችግሩን የሚፈታ ወይ የሚያቃልል ተግባር መፈፀም ነው። በጎነት ሁሉም ሰው ማድረግ የሚቻለው የልብ ቅንነትን ብቻ የሚጠይቅ ተግባር ነው። መልካም ቀን ይሁንለወ!

ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚሳካው በዘላቂ ሰላም ውስጥ ነው። የዘላቂ ሰላም ግንባታ እንዲሳካ ደግሞ አብሮነታችንን የበለጠ ማጠናከር ይጠይቃል። ኢትዮጵያዊነት ብዙ ማንነቶች አንድ ላይ ሆነው በውብ ህብረ ብ
ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚሳካው በዘላቂ ሰላም ውስጥ ነው። የዘላቂ ሰላም ግንባታ እንዲሳካ ደግሞ አብሮነታችንን የበለጠ ማጠናከር ይጠይቃል። ኢትዮጵያዊነት ብዙ ማንነቶች አንድ ላይ ሆነው በውብ ህብረ ብሔራዊነት የተገነባ ማንነት ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ!

መደመር የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን የማድረጊያ መንገድ ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች እንድትሆን ይፈልጋል። የበለፀገች ለማድረግ ደግሞ ትክክለኛውን መንገድ መከተል ይጠይቃል
መደመር የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን የማድረጊያ መንገድ ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች እንድትሆን ይፈልጋል። የበለፀገች ለማድረግ ደግሞ ትክክለኛውን መንገድ መከተል ይጠይቃል። አሸናፊዎች መንገዳቸውን አይለቁም። በመደመር መንገድ ተጉዘን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ! መልካም ቀን ይሁንለዎ!

ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ ረገድ ለውጥ እያመጣች እየበለፀገች ያለች ሀገር ናት። ተፈጥሮን ጠብቃ ከተፈጥሮ የተቸሯትን ፀጋዎች ወደ ጥቅም በመቀየር በአፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት ተርታ በአጭር ጊዜ
ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ ረገድ ለውጥ እያመጣች እየበለፀገች ያለች ሀገር ናት። ተፈጥሮን ጠብቃ ከተፈጥሮ የተቸሯትን ፀጋዎች ወደ ጥቅም በመቀየር በአፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት ተርታ በአጭር ጊዜ በብዙ ፈተና ውስጥ ሆና አስመዝግባለች። ያለንን ሀብት በአግባቡ መጠቀም ለነገው ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት መስራት አስፈላጊ ነው። በዚህ እረገድ የሚታዮ የሚጨበጡ ከተስፋ ተሻግረው እውን የሆኑ ውጤቶች መጥተዋል። ሁላችንም የድርሻችንን በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንለዎ!

ኢትዮጵያዊያን ብዝሃነትን በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት ገመድ ላይለያይ የተገመደ ማንነት ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
ኢትዮጵያዊያን ብዝሃነትን በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት ገመድ ላይለያይ የተገመደ ማንነት ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና