1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
1 671
ለአንድ ሀገር ብልፅግና መሠረታዊ ከሚባሉት ጉዳዮች አንዱ፤ በዕውቀት ላይ የሚኖር የበላይነት ነው።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በዕውቀት ዘርፍ ተወዳዳሪ ሆና እንድትወጣና፤ በውጤቱም ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስኬትን ለማስመዝገብ፤ ትውልዱ በዕውቀት ታንፆ እንዲያድግ ማድረግ ይኖርብናል።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
1 671
ፈጠራ ለሀገር እድገት ለአዲስ ነገር መነሳሳት አስፈላጊ ነው።
አለም በየጊዜው በአዳዲስ ነገር ትሞላለች። አዳዲስ ጉዳይዮቹ ችግርም መልካም ነገርም ሊሆኑ ይችላሉ። በፈጠራ ላይ ለሚሰራ ትውልድ ችግርንም ሆነ መልካም ነገርን ወደ እድል ለመቀየር ያግዘዋል።
ትውልድ ማደግ፣ መበልፀግ የሚችለው ፈጠራን አንዱ የስራ አካል ሲያደርግ ነው። ፈጠራ ትውልድን ይገነባል። አዳዲስ ፈጠራዎችን ለሀገር ያስገኛል። የተለመደውን ኮፒ እያደረጉ መቀጠል ከዘመን ጋር እኩል እንዳንጓዝ ነገን ቀድመን እንዳንተነብይ ያደርጋል።ዠ ኩረጃ ትውልድን ገዳይ ሲሆን ፈጠራ ትውልድን የሚያንፅ አሻራ ለማሳረፍ እድል የሚፈጥር ነው።
ፈጠራን በማበርታት፣ በፈጠራ በመስራት ዘመኑን የዋጁ፣ ለዘመኑ ችግር መፍትሔ የሚሆኑ፣ ለዘመኑ ጥቅም የሚሰጡ ፈጠራዎችን እንፍጠር። ትናንት መሠረት እንጂ ዛሬን ሊሆን አይችልም። የዛሬን ስራዎች በፈጠራ በማጀብ ዘመኑን የሚመጥን ጊዜውን የሚዋጅ ለነገ የሚተላለፍ ስራ እንስራ!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity party-ብልፅግና
1 671
ትናንት የተሰሩት ወረት ሆነው ወይ ደግሞ እዳ ሆነው ለትውልድ ተላልፈዋል።
ፓርቲያችን ብልፅግና የትናንት ወረቶችን የበለጠ የሚያበለፅግ፣ ጠብቆ እና ተንከባክቦ በወረትነት ከመያዝ ባለፈ ለማካበት የሚሰራ ፓርቲ ነው። የትናንቱ ትውልድ በርካታ ወርቃማ ስራዎችን ሰርቶ ለትውልድ አበርክቶ አልፏል። የትናንቱ ትውልድ በርካታ ሊታረሙ የሚገባቸው እዳዎችንም አስቀምጧል።
በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከስህተቶች ከጉድለቶች የፀዳ ስራ መጠበቅ የዋህነት ነው። ግን ደግሞ ከእዳው ይልቅ ወረቱን ምንዳውን የበዛ ማድረግ ግድ ነው። ትናንትን መሠረት አድርገን ለመነሳት ከእዳውም ከምንዳውም እንደሚደርሰን መረዳት ነው። ዛሬ ላይ ሆነን ለነገ መሠረተ ፅኑ ግንባታ ማስጀመር ግድ ይላል። መሠረቱ የፀና ግንባታ ከጉድለቱ ይልቅ ወረቱ የበዛ ይሆናል።
የፓርቲያችን ብልፅግና ዋና አላማ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው፤ ይህንንም ለማሳካት የትናንትን ጥንካሬ በወረትነት ይዞ ወረቱን በማከማቸት ላይ ይገኛል። ትናንት ወረት ብቻ ሳይሆን ብዙ እዳም ሰጥቶን አልፏልና እዳውንም የመክፈል ግደታ በእኛ ላይ ነው።
ፓርቲያችን ብልፅግና ለነገ የሚያስተላልፈውን ወረት ለማብዛት መላው ህዝብን አሳትፎ በመስራት ላይ ይገኛል። ወረታችንን አብዝተን እዳውን ቀንሰን እና ከፍለን የነገውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት እውን ማድረግ የእኛ ኃላፊነት ነው። በወንድማማችነት መርህ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ጠብቀን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንትጋ!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#kolfe prosperity party - ብልፅግና
1 671
ኢትዮጵያ ብዝሃነት በፍቅር፣ በአብሮነት፣ በመተሳሰብ እና በመከባበር የመኖር ማሳያ ሀገር ነች።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች የነገ ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት እውን ያደረገች መሆን ነው። ፓርቲያችን ብልፅግናም ይህንኑ እውን ለማድረግ እየሰራ ያለ በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ ፓርቲ ነው።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
1 671
ሀገራዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን ለሀገራዊ ብልፅግና ወሳኝ ነው።
የሀገራዊ ብልፅግና የሚሳካው በዘላቂ ሰላም መስፈን ውስጥ ነው። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሁሉም አካል ፍላጎት እና ተግባርን ይጠይቃል። ሁሉም ሰው ለሰላም ዘብ ከቆመ፣ ፀረ ሰላም ኃይሎችን በመምከር ወደ ሰላም እንድመለሱ ካልተመለሱ የህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግን ከቻለ ዘላቂ ሰላም ይሰፍናል። ኢትዮጵያዊያን ሰላም ወዳድ ለሰላም ዘብ የሚቆም ህዝብ ነው። ሰላም ወዳድነታችንን በቅንጅት እና በትብብር ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ማዋል አለብን። በዘላቂ ሰላም ውስጥ እድገት አለ፤ በዘላቂ ሰላም ውስጥ ሀብት ማፍራት አለ፤ በዘላቂ ሰላም መስፈን ውስጥ ወልዶ ማሳደግ፣ አርሶ ማምረት፣ ነግዶ ማትረፍ፣ ተመራምሮ አዲስ እውቀት ማገኘት፣ ተምሮ ለወግ ማዕረግ መብቃት በቀላሉ ማሳካት ይቻላል። ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው። የታመመ ታክሞ መዳን የሚችለው፣ የሰራውን መጠቀም የሚቻለው ጭምርጨበዘላቂ ሰላም መስፈን ውስጥ ነው። ሁላችንም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የድርሻችንን እንወጣ። ዛላቂ ሰላምን በመገንባት የኢትዮጵያን ብልፅግና እናፋጥን!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
የትልቅ ህዝብ እናት፣ የትልልቅ ገድል ባለቤት፣ የብዙ ሀብት ፀጋ የተቸራት ኢትዮጵያ!
ኢትዮጵያ የጀግናና ኩሩ ህዝብ እናት ነች። የሀገራችን ሀብት በአንድ ነገር ላይ የተወሰነ አይደለም። የጥንተ ስልጣኔ የቱሪስት ቦታዎችን ከኤርታሌ ጀምረን፣ አክሱም፣ ነጃሽ፣ ላሊበላ፣ የፋሲል ግንብ፣ ጀጎል ግንብ፣ ሶፍዑመር ዋሻ፣ የንጉስ አባጅፋር ቤተ መንግስት፣ ጢያ ትክል ድንጋይ እያልን እንቆጥራለን። የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የባሌ ብሔራዊ ፓርክ እያልን ሌሎች ቆጥረን የማንዘልቃቸው ተፈጥሮ ያደለንን ሀብት እናገኛለን። በማዕድን ዘርፍ ብንገባ ወርቅ፣ ታንታኔም፣ ኦፓል ... ያልተነኩ በርካታ የሀብት ክምችት አለ። በግርድፍ ጥናት ኢትዮጽያ መታረስ ከሚችል 15% መሬት ውስጥ 3% የሚሆን ብቻ ነው የታረሰው። ኢትዮጵያ ያልተነኩ ሀብቶች ያሏት ሀገር ነች። የሰው ኃይሏ ከአለም ትልቅ የህዝብ ቁጥር ካላቸው መካከል ነች። የህዝቧ 70% ወጣትና ታዳጊ ሰሪ ኃይል ውስጥ የሚመደብ ነው። ኢትዮጵያ ተነግሮ የማያልቅ ታሪክ ተዝቆ የማያልቅ ሀብት አላት። ከልጆቿ የሚጠበቀው ያላትን ሀብት አውቆ ተስማምቶ ተግባብቶ ተግቶ በመስራት ታላቋን ሀያል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው። ሁላችንም ያለንን ሀብት አውቀን፣ ያለንን አቅም ደምረን በመስራት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
በደም የተከበረችን ሀገርን በላብ እናፀናታለን።
ኢትዮጵያ በየዘመናቱ ህይወት ተገብሮባት ዋጋ ተከፍሎላት የተከበረች ሀገር ነች። በታሪካችን እንደምናውቀው ከጥንት እስከ ዛሬ ኢትዮጵያን ለማዳከም ያልተሞከረ ሙከራ ያልተጠነሰሰ ሴራ አልነበረም። የተዳከመች ሲመስላቸው በራሳቸው በአካል ተሰይሞ የመሞከር፣ ጥንካሬዋን በፈሩ ጊዜ እርስ በራሳችን የሚያጋጭ አጀንዳ መስጠትና የውስጥ ችግር መፍጠር የውጪ ጠላቶቻችን ባህሪ ሆኖ እናገኘዋለን። የጠላትን ተቀያያሪ ባህሪ የመሰለ ምላሽ ሰጭ ህዝብ ስለነበር የሀገር ክብር ሳያስነኩ ዳር ድንበር ሳያስደፍሩ ከጥንት እስከ ዛሬ ኢትዮጵያ በደም ተከብራ ለኛ እንድትደርስ አድርገዋል። አሁንም ቢሆን ሀገር የሚደፍር ኃይል ሲመጣ ልክ እንደ ጥንቱ ደም የሚከፍል ጀግና ህዝብ አለ። ኢትዮጵያ በደም የተከበረች ነች አሁንም ለክብራ የሚከፈል ዋጋ ካለ የሚከፍሉ ልጆች አሏት። አንዱ ጉዳይ ግን በእጅጉ ስራ ይጠይቃል። አሱም በደም የተከረችውን በላባችን ማፅናት ይገባናል። ህዳሴ ግድብን በተባበረ ክንዳችን እውን አድርገነዋል። ለማጠናቀቅም እየተረባረብን ነው። እንደዚህ አይነት ትልልቅ ፕሮጀክቶች እውን ማድረግ በላብ ለማፅናት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። ስንዴ በኢትዮጵያዊያን የእንችላለን መንፈስ ባወጣነው ላብ ልክ ውጤት አምጥቷል። አረንጓዴ አሻራ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአለም እንደሚተርፍ ውጤቱ ያሳያል። ገበታ ለሀገር በላባችን እውን ያደረግነው የቱሪዝም ሀብቱ አይነጥፌ አጋዥ ሀብት ነው። ማዕድን ላይ የመጣው መነቃቃት በብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ በላብ ለማፅናት የሚደረገው ርብርብ ማሳያ ነው። አሁን ላይ የሀገር መከበሪያው ሚስጥር ከተዋጊነት በላይ ሀብት ነው። በሀብት ጡንቻውን ያፈረጠመ ሀገር መዳፈር ዋጋ እንደሚያስከፍል ሁሉም ይረዳል። ዋጋውም ከደም ላብ መክፈል በእጅጉ ይሻላል። ስለዚህም ሁላችንም ለሀገራችን ብልፅግና እውን መሆን ሙሉ ጊዜያችንን መስራት ይገባናል። በተሰማራንበት ሁሉ ሙሉ እውቀታችንን ጉልበታችንን መጠቀም ላይ ገና ይቀረናል። በተሰማራንበት ሁሉ የሚገባንን ኃላፊነት በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያን በላባችን እውን እናድርግ!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
እውቀት የችግሮች ሁሉ መፍቻ ቁልፍ፣ የእንቅፋቶች ሁሉ ማለፊያ መፍትሔ ነው። እውቀትን በብዙ መንገድ ልንሸምት እንችላለን። ዋና መሰረቱ ግን ትምህርት ቤቶች ናቸው።
ትምህርት ቤቶቻችን የእውቀት መሸመቻ፣ የትውልድ መገንቢያ፣ ስነ መግባር የሚታነፅበት፣ የነገ ተስፋ የሚለመልምበት ተቋም ነው። ብልፅግና የትምህርት ፍትሐዊ ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ፣ ብሎም የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፤ በመስራትም ላይ ይገኛል።
የትምህርት ጥራትና ፍትሐዊ ተደራሽነት ለማረጋገጥ ሁሉም ድርሻ አለው። ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ የድርሻችንን ስንወጣ ተደምሮ ብልፅግናን እውን ያደርጋል። ትምህርት ቤቶቻችን ላይ ጥራት፣ ፍትሀዊ ተደራሽነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ነገ ተባብረን ብሩህ እናድርግ።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
@Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
በሀገሬ ጉዳይ እኔም ያገባኛል ማለት እና መሳተፍ ለነገ ሊባል አይችልም። ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ጫፍ ከምስራቅ ጫፍ እስከ ምዕራብ ጫፍ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሀገሩ ጉዳይ ሊመክር ይገባል። በሀገራችን ጉዳይ እየተወያየን ጠላትን ማሳፈር፤ ለኢትዮጵያ ብልፅግና የእኛ ሀገራዊ ሁሉን አቀፍ አካታች ምክክር ማድረግ የማይተካ ሚና ይኖረዋል።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
kolfe prosperity party - ብልፅግና
1 671
የሀገር ፍቅር መገለጫው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ኃላፊነት መወጣት ነው።
ሰላም በሁሉም ሰው ሰላም ወዳድነት እውን የሚሆን ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራችን ከፍተኛ ፍቅር ያለን ለሀገር የሚያስፈልገውን ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ የሆንን ህዝብ ነን። የሀገር ፍቅር መገለጫው ሰላም ማስፈን ነው። ዜጎች በምቾት እንድኖሩ መትጋት ነው። በኢኮኖሚዋ የዳበረች እንድትሆን የግልም ሆነ የቡድን ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት ነው። የሀገር ወዳድነት መገለጫው ትውልድ መገንባት ለነገ አስቦ ዛሬን መስራት፣ የመጭውን ትውልድ ጥቅም እና ፍላጎት የሚያስጠብቅ አሻራ ማሳረፍ ነው። ሁላችንም ዘላቂ ሰላምን እውን በማድረግ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
1 671
ኢትዮጵያ ድንቅ ሀገር ናት የሚባለው በምክንያት ነው። ዛሬ ላይ በዓለም ሀያል ሀገራት የሰብዓዊ ህግ ሞራላዊ ግደታ እያሉ የሚተነትኑት ትናንት የእኛ አባቶች፣ አቶች፣ ቅድመ አያቶች የማህበራዊ እሴታቸው፣ የባህላዊ ህግ አድርገው የተመሩበት ነው። ኢትዮጵያዊያን ታላቅን ማክበር መንከባከብ መስማት በታላቅ መመረቅ ትልቅ የማህበራዊ እሴት ነው።ስራችን መልሶ ይከፍለናል ዛሬ ያልሰራነው ነገ አይገኝም የሚለው የትኛውም የኢትዮጵያ ጥግ የትኛውንም ማህበረሰብ ብንጠይቅ የሚሰጠን መልስ ነው። ዛሬ ላይ የምንተገብራት እያንዳንዷ ጉዳይ የነገ መዳረሻችንን ትወስናለች። ዛሬ አረጋዊያንን መጦር "ብድሩ ይድረስህ" የሚለውን ምርቃት ያስገኛል፤ ካልተንከባከብን ደግሞ በተቃራኒው ይሆናል።
ዛሬ የንከባከብነው ህፃናትን ስራ ካስተማርናቸው ነገን የመስራቱ ጅምር በስኬት ይጠናቀቃል ማለት ነው። የማይቻሉ የሚመስሉ ፕሮጀክቶችን እንደሚቻል አሳይቶ ለምረቃ ማብቃት እና መመረቅ ደግሞ በትውልድ ልብ ውስጥ የይቻላልን መንፈስ በልቡ መትከል ነው። ድምር ውጤቱ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች ለአለም የምትተርፍ የአፍሪካዋ የብልፅግና ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ያስችላል።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
1 671
እንኳን ለ2016 የኢትዮጵያችን አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ!
አቶ ሙሉጌታ ጉሉማ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
ኢትዮጵያ ተነግረው የማያልቁ ታሪኮች፣ ታይተው የማይጠገቡ ውብ ቦታዎች፣ ተዝቀው የማይጨረሱ ሀብቶች ያሏት ሀገር ነች፡፡ ተነግረው ከማያልቁት ገናና ታሪኮቿ ውስጥ አንዱ የጊዜ አቆጣጠር ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን የራሳችን የጊዜ አቆጣጠር አለን፡፡ በጊዜ አቆጣጠራችን መሰረት የ2015 አሮጌውን አመት ሸኝተን የ2016 አዲሱን አመት በመቀበል ላይ ነን፡፡ ጊዜ ይሄዳል ይመጣል፤ ትናንት ትናንት ነበር ላይመለስ ለአንዴዬ እና ለመጨረሻ ጊዜ ሸኝተነዋል፡፡ ትናንት ሌላ ቀን ነበር፤ ዛሬም ሌላ ቀን ነው፤ ነገም እንድሁ በፍፁም ትናንትን ዛሬ ላይ ማምጣት አንችልም ብንፈልግም፣ ባንፈልግም፣ ብንወድም፣ ባንወድም ትናንትን ላይመለስ ሸኝተነዋል፡፡ ዛሬም ቢሆን ይዘን የምናቆየው፣ የምናዘገየው አይደልም ወይ ደግሞ አፍጥነን የምናሳልፈው አይሆንም፤ ጊዜ ተፈጥሯዊ ኡደቱን ጠብቆ ይቀጥላል፡፡
በትናንትም መሄድ ሆነ በዛሬ ለእኛ መሰጠት ወይ ነገ ለእኛ መምጣቱ በምንሰራበት ስራ የሚወሰን ነው፡፡ ትናንትን በአግባቡ ተጠቅመነው ከሆነ ታሪክ ላይ ተመዝግቦልናል፡፡ የተፈጠርንለትን አላማም አሳክክንበት አልፎ ይሆናል፡፡ ዛሬ ለእኛ የተሰጠ እድል ነው፡፡ በአግባቡ መጠቀም የእኛ ፋንታ ነው፡፡ ነገ ግን ገና ያላወቅነው ተስፋ ነው፡፡ ነገን ማገኘታችን በእኛ ውሳኔ በእኛ እጅ ላይ ያለ ጉዳይ አይደለም፡፡ እናም በአዲሱ አመት ከትናንት ጉድለትም፣ ብርታትም፣ ትምህርትም እንውሰድበት፡፡ ዛሬ ላይ የትናንት ጉድለታችንን እንሙላበት፤ የትናንት ጥንካሬን የበለጠ እናበርታበት፡፡
በአዲሱ አመት አዲስ እቅድ እናቅድ አሻራችንን የምናስቀምጥበት ለትውልድ የምንተርፍበት እቅድ እናቅድ፡፡ በትናንት መቆዘምን እንተዎው፤ ‘ለአለፈ ክረምት ቤት አይሰራም' እንድሉ ነጋችንን እናስብ እና ዛሬችንን በአግባቡ እንጠቀመው፡፡ ትናንትን ማስታዎሱ ለትምህርት ብቻ ነው የሚጠቅመን፡፡ ዋናው ቁምነገር ያለው የተሰጠችን ዛሬ ላይ ብቻ ነው፡፡ ዛሬን በአግባቡ በመስራት የተጣለብንን አደራ እንወጣ፡፡ ነገ ተስፋ ነው፤ ተስፋችንን ብሩህ ለማድረግ ዛሬ መሰረት እንጣል፡፡
በ2015 አሮጌው አመት በክ/ከተማችንም ሆነ በከተማችንም ብሎም በሀገራችን በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡ ለትውልድ የተሰሩ ስራዎች አሻራ ሆነው በደማቅ ብዕር የተፃፉ ውብ ተግባሮች በስኬት ተመዝግበዋል፡፡ በክ/ከተማችን በቅርብ ያስመረቅነው በመደመር ትውልድ መፅሐፍ ሽያጭ ገቢ የመደመር ትውልድ ሜዳን እንኳን ብናይ ፓርቲያችን ብልፅግና ቃሉን በተግባር የሚቀይር ፓርቲ መሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ትናንት ከህዝባችን ጋር ሆነን በርካታ ስራ ሰርተናል፡፡ ምዕድ አጋርተናል፣ ቤት አድሰናል፣ አዲስ ግንብተን ሰጥተናል፣ የልማት ስራዎች በስኬት አጠናቀናል፣ ፕሮጀክቶች ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ የአገልግሎት መስጫ ተቋም በስኬት ገንብተን አጠናቀን አስመርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል፡፡
እንደ ሀገር ካየን ከአዲስ አመት መባቻ ቀደም ብለን የህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት በስኬት አጠናቀን ለህዝባችን የአዲስ አመት ስጦታ ሆኗል፡፡ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ኃይል የማመንጨት ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነ ሁላችንም እንረዳለን፡፡ ህዳሴ ኃይል ነው፤ ህዳሴ የራስን ሀብት በራስ አቅም ለጥቅም የማዋል ምልክት ነው፤ ህዳሴ አፍሪካዊያን በራሳችን ያለምንም ድጋፍ የእንችላለን ማሳያ ነው፤ ህዳሴ ትውልድ ሲተባበር የማይደፈር የመሰለንን ደፍሮ ማሳየት ነው፤ ህዳሴ አትችሉም ለሚሉን ችለን በተግባር የመቻላችን ምላሽ አፍሪካዊ ኩራት ነው፡፡ 2015 ሌላው የማይረሳ ገድል የፈፀምነው ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ መቅረብ የቻለ የስንዴ ምርት ማምረት መቻላችን ነው፡፡ ስንዴ ምግብ ብቻ ሳይሆን የተፅኖ ምንጭ፣ የራስ ያልሆነ ፖሊሲ የማስፈፀም ግደታ የመጫን መሳሪያ፣ እጅ የመጠምዘዥያ፣ የአንገት ማስደፊያ የርዳታ ሰጭች መሳሪያ ነበር፡፡ ሁልጊዜም ታሪክ ቀያሪዋ ሀገራችን አፍሪካዊያን እንችላለን፣ አይናችንን እንግለጥ ያለችበትን መልዕክት ያስተላለፈችበት ከእጅ መጠምዘዝ የሚያስወጣ ፕሮጀክት እውን ያደረገችበት ነው፡፡
የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካ የሚለው ጠንካራ እምነቷ የውጭ ጣልቃ ገብነት ሳይኖር አፍሪካዊያን እንችላለን ያስባለችበት የቪክቶሪያው የሰላም ስምምት እውን ማድረግ የቻልነውም በ2015 ነበር፡፡ 2015 ሀገራችን ኢትዮጵያ የብሪክስ አበልነት ተቀባይነት አግኝቶ አባል የሆነችበት አመት ነው፡፡ የብሪክስ አባልነት ቀልድ አይደልም መመዘኛው አባል ቢሆን ምን ጥቅም ያስገኝልኛል፣ ምን ያክል ድፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ተፅኖ ይፈጥራል ተብሎ ተመዝኖ የሚሰጥ ነው፡፡ በመሪያችንን አርቆ አሳቢነትና ብልህነት በፓሪቲያችን ብልፅግና ቃል በተግባር የመቀየር እውን አድራጊት 2015 በስኬት ተጠናቋል፡፡
2015ትን ዘወር ብለን ስናያቸው ቃል የተገቡት እውን ሆነው የአፍሪካ የኩራት ምንጭነትን አረጋግጠው እናያቸዋለን፡፡ ትናንት በርካታ ስኬቶች መታረም ካለባቸው ጉድለቶች ጋር አልፏል፡፡ ዛሬ ደግሞ ትናንት ስኬትን እንድናስቀጥል ጉድለት እንድናርምበት አዲስ እቅድ አዲስ ስኬት እንድናስመዘግብበት 2016 አዲሱ አመት እነሆ ተሰጥቶናል፡፡ የ2016 አዲስ አመት ስኬትን የምንጎናፀፍበት፣ ብልፅግናን የምናሳካበት፣ አንድነትን የምናጠናክርበት፣ ትውልድን በበጎ የምንቀርፅበት፣ ህዝብን በቅንነት የምናገለግልበት፣ ሌብነትን የምናጠፋበት፣ እቅዳችንን የምናሳካበት እንድሆን እመኛለሁ፡፡ መልካም አዲስ አመት!
#Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
1 671
ኢትዮጵያዊያን አብርሮነት የጥንካሬ ምንጭ የአንድነት ማሳያ ጠንካራ የትስስስር መፍጠሪያ መንገዳችን ነው።
በአብሮነት ችግሮችን አልፈናል፤ ስኬቶችን አስመዝግበናል፤ በጋራ ታሪክ ፅፈናል። አብሮነታችን የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ሆኗል። ኢትዮጵያዊያን የሚያምርብን አብሮነታችንን ስናጠነክር ነው።
በአብሮነታችን ለወዳጅ የደስታ ምንጭ ነው፤ ለጠላት ደግሞ አስፈሪ ግርማ ሞገስ የሚያላብሰን። ዛሬ የአብሮነት ቀን ነው።
አብሮነታችንን በማጠከ ብልፅግናችንን ለማሳካት እንትጋ! መልካም የአብሮነት ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
1 671
ሀገር የሚገነባው የሚበለፅገው በሚያመርቱ እጆች ነው።
ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ አቅሞች አሏት። የአንድ ሀገር የመበልፀግ አቅም ያለው የተፈጥሮ ሀብት የመልማት አቅም፣ መስራት የሚችል የተማረ የሰው ኃይል፣ ለማልማት መነሻ የሚሆን ካፒታል ነው።
ኢትዮጵያ እንደ እድል ሆኖ ሁሉም የመልማት አቅም አላት። ያለንን የተፈጥሮ ሀብት፣ የተማረ የሰው ኃይል አቀናጅተን በማምረት በመስራት አምራችነትን ከፍ ማድረግ ይጠበቅብናል። ሀገር የምትገነባው በሁሉም ዜጋ ርብርብ ነው። ሁሉም በተሰማራበት የድርሻውን፣ የተሰጠውን ኃላፊነት መወጣት ሲችል ድምር ውጤቱ የበለፀገች ኢትዮጵያን ኦእውን ማድረግ ይቻላል።
ሁላችንም በማምረት አቅማችን ሁሉ እናምርት። በሀገር ምርት የሚኮራ፣ የሀገሩን ምርት የሚጠቀም ከውጭ ከማስገባት ይልቅ ወደ ውጭ የመላክ አቅም የሚፈጥር እንሁን። ተባብረን፣ ተቀናጅተን አንድነት እና ወንድማማችነት አጠንክረን አምራችነትን አጎልብተን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
መልካም የአምራችነት ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe Prosperity party-ብልፅግና
1 671
በጎነት ከልብ የመነጨ ለሌሎች የመኖር የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ነው።
ከራስ አልፎ ለሰው መኖርን የምንገልጥበት ሰው የመሆን ሚስጥር ነው። በጎነት ለወገን አለኝታነት ወገን አለኝ የማለትን የኩራት ስሜትንም ማጋራት ነው። በጎነት ለሌችን ለማነሳሳት አርዓያ ለመሆን በአደባባይ የምናደርገው ሊሆን ይችላል። በጎነት ግን ከእዩልኝም የተሻገረ ለሙገሳ፣ ለክብር እና ለዝና ብቻ የሚደረግ ሳይሆን ሰው በመሆናችን ለሌሎች መኖር ነው። ወገኔ ተቸግሮ ደስታ አላገኝም። የእኔ ደስታ ሙሉ የሚሆነው በዙሪዬ የተቸገሩ ሳይ ማገዝ ከቻልኩ ነው የሚል እሳቤን መያዝ ይጠይቃል። በጎነት ሰው ያድንቀኝ ያውራልኝ ይናገርልኝ ብለህ ከምታደርገው በእጅጉ ይሻገራል። በጎነት ብድር ምላሽን፣ ምስጋናን አይሻም። በሚያደርገው ነገር መልሶ የሚቀበለውን አያሰላም ሰው በመሆን የሚገኝ ፀጋ ነው ሊባል የሚችለው ለዚሁ ነው። ትርፍና ኪሳራ፣ ሙገሳና ዝና፣ መስጠትና መቀበልን አስልቶ የሚያደርግ በበጎነት ሊገለጥ አይችልም። በቃ በጎነት የራስን ጎደሎ ትቶ የሌሎች ወገኖችን ችግር በማቃለሉ ምክንያት የሚገኝ የደስታ አሴት ነው።
ሁላችንም በጎነትን በውስጣችን እናዳብር። በጎነት በዘመቻ በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ሳይሆን በህይወት እስካለን ልንተገብረው የሚገባን ነው። ከጎረቤቶቻችን፣ ከአጠገባችን እንጀምር፣ በጎነታችን ከገንዘብ ከቁስ መስጠት የተሻገረ ይሁን። በጎነታችን ከሌሎች ለምናገኘው ምላሽ ጠብቀን ሳይሆን ሰው በመሆናችን ማድረግ የሚገባን ህሊናዊ ሞራላዊ ግደታ መሆኑን እንረዳ። ያኔ ከሰው አንጠብቅም ከእኛ የሚጠበቅብንን እንወጣለን እንጂ። በጎነትን ዛሬ እንጀምረው። ከእዩልኝ በላይ በማድረግ ለህሊና ታምነን ሁላችንም አጠገባችን ያለን ሰው ችግርን ብንቀርፍ ኢትዮጵያ ውስጥ መቸገርን ተረት ማድረግ ይቻለናል። ሳይታዩ የሚሰጡ በርካታ እጆች አሉ እነዚህን እጆች ያብዛልን።
መልካም የበጎነት ቀን ይሁንለዎ!
