en
Feedback
Kolfe P.P - ብልፅግና

Kolfe P.P - ብልፅግና

Open in Telegram
1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
የሰው ተኮር ተግባራችን እኔ ለወገኔ አለሁለት የሚል ጀግና ፈጥሯል። ምድር ላይ የሚሰራው ስራ ሁሉ የሰውን ልጅ የሚጠቅም ለማድረግ ነው። ምድር ላይ ያሉ ሁሉም ነገሮች ለሰው ልጅ መጠቀሚያነት የሚውሉ ሆነው የተፈጠሩ ናቸው። ፓርቲያችን ብልፅግና ሰው ተኮር ነው። የሰው ልጅ ፍላጎትና ጥቅምን ለማሟላት የሚሰራ ፓርቲ ነው። ቁሳዊ ነገሮች ሁሉ የሰው ልጅ መጠቀሚያ ከሆኑ፣ የምንሰራው ስራ ሁሉ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሰውን ልጅ ለመጥቀም ነው። ብልፅግና በእቅድ ይዞ በሰው ተኮር ተግባራት ከሰራቸው ስራዎች ውስጥ የተማሪዎች ምገባ አንዱ ነው። በብልፅግና እሳቤ ተመርተን ትውልድ ስንገነባ አስፈላጊው ነገር እያሟላን መሆን አለበት። በርሃብ የሚጮህ ሆድ ይዞ ስለሌላ ጉዳይ የሚመራመር አእምሮ ሊኖር አይችልም። ደብተር፣ እስኪርብቶ የሚያስጨንቀው ወላጅ ውስጥ ያለ ተማሪ ስለ መፍጠርና መመራመር ከማሰብ ይልቅ የተደቀነውን የቤተሰብ ፈተና ስለማለፍ ብቻ ይሆናል። ለዛም ነው ፓርቲያችን ብልፅግና የተማሪዎችን ምገባ ከመጀመር አንስቶ ዩኒፎርም አስፈቶ፣ ደብተር፣ እስኪርብቶ፣ አጠቃላይ የትምህርት ቁሳቁስ የተሟላለት ተማሪ እንድኖር የሰራው። ወላጅ ስለ ልጁ የትምህርት ብቃት የሚያስብበት፣ ልጅ ስለ ነገ የሚመራመርበት፣ በትምህርቱ ስለመጎበዝ የሚያስብበት እንድሆን እየተሰራ ያለው። በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችሉ ነዋሪዎቻችን በርካታ እንደነበሩ የሚታወቅ ነው። በቀን አንድ ጊዜ የማይመብ መኖር የለበትም የሚለው ቁርጠኝነት መመገቢያ ቦታዎችን ለመገንባት አነሳስቷል። በመገንባትም አሁን ላይ ምንም ያጣ፣ መስራት የማይችል፣ አቅመ ደካማ፣ ረዳት የሌለው ቢሆን እንኳን አዲስ አበባ ከተማ በቀን አንድ ጊዜ የመመገብ ቁርጠኝነትን ይዛ እየመገበች ነው። ሰው ተኮርነት በተግባር ሲገለጥ፥ በመወለድ፣ በቋንቋ፣ በማንነት ሳይሆን ሰው በመሆን ብቻ ወገን አለኝ፣ ደጋፊ፣ ጧሪ ሀገር አለችኝ የሚያስብል ተግባር ተጀምሯል። አለሁልህ ማለት በተግባር ችግሩን በማቃለል ነውና የሆነውም ይሄው ነው። የሰው ተኮር ተግባራችን ከሰራናቸው የሚያኮሩ ተግባራት ሌላኛው ጣሪያቸው የክረምት ዝናብን መቋቋም የማይችሉ የአቅመ ደካማ የአረጋዊያን ደሳሳ ጎጆዎች አምረውና ተዋበው ተሰርተው የአረገረዊያን የአቅመ ደካማ ወገኖቻችን የደስታ ምንጭ ሆነዋል። ከመጨነቅ ወጥተው ወገንን መርቀዋባቸዋል። የሰው ተኮር ተግባራችን ያንን ክፉ የኮረና ጊዜ፣ ሰው ሰውን በማይጠይቅበት አስከፊ ወቅት ሰው ባለመስራቱ ከበሽታው በፊት በርሃብ እንዳይሞት ማዕድ መጋራት እንድኖር ተደርጓል። በአንድ በኩል እኔ ለወገኔ አለሁለት የሚል ጀግና ስንፈጥር በሌላ በኩል ወገን አለኝ ለካ የሚል ጥልቅ የመተሳሰብ የወንድማማችነት/ እህትማማችነት መንፈስ ተፈጥሯል። በር ዘግቶ መብላት ዘመን አመጣሹ ባህልን አፍርሶ ያ የነበረ የሚያምረውን የጥንቱን የመረዳዳት የመተጋገዝ ባህላችንን መልሷል። ብልፅግና የነበረ እሴት መጠበቅ ማጎልበትና ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል ብሎ ያምናልና። በበዓላት አንዱ ጠግቦ አንዱ ተርቦ አንዱ ቤት በደስታ በፌሽታ እና በመትረፍረፍ ሌላው ቤት ደግሞ በእጦትና መቸገር እንዳይሆን ማዕድ ማጋራት ተግባራችን የሰው ተኮርነት መገለጫ ነው። ፕሮጀክቶቻችን በተያዘላቸው ጊዜ ሲሰሩ በሚሰሩበት ወቅት በርካታ የስራ እድል ፈጥረው ከጉልበት ሰራተኛ እስከ ተቋራጭ የስራ እድል ፈጥረዋል። የእለት ጉርስ ሸፍነው ለነገ የሚቆጠብ ገንዘብን አስገኝተዋል። ከቆሻሻ መጣያነት የሀገር ኩራትነት የዜጋ ተጠቃሚነት ማረጋገጫ ሆነዋል። ሁሉም የሚያስታውሰው የእንጦጦ ፓርክን ብንወስድ እንጦጦ እህቶች፣ እናቶች እንጨት ለቅመው ለመተዳደር የሚፈጉበት ቦታ ከመሆኑ ተጨማሪ መዘረፍ መደፈር ሊያጋጥም የሚችልበት አስፈሪ ቦታ ነበር። አሁን ላይ እንጨት ለቅመው ለሚተዳደሩ እናቶች ስራ እድል በቋሚነት የፈጠረ ለኢትዮጵዊያን የገቢ ምንጭ፣ የመዝናኛ ማዕከል፣ የይቻላል መንፈስ የሰጠ፣ የምንኮራበት ፕሮጀክት ነው። ለውጭ ዜጎች የጉብኝት ማዕከል የመዝናኛ ቦታ ሆኖም ያገለግላል። ሌሎችንም ፕሮጀክቶች ካየን ይህንኑ መገንዘብ እንችላለን። ለዚህም ነው ብልፅግና ሰው ተኮር ነው የምንለው። በእያንዳንዱ ተግባር የሰው ልጅ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ነገን ብሩህ የሚያደስጉ ተደርገው መሠራታቸው። ዛሬ ነዋሪውን የሚጠቅሙ ለነገ ትውልድ አሻራ እና ወረት የሚሆኑ ተግባራት በፓርቲያችን ብልፅግና መሪነት እውን ሆነዋል። ሁላችንም በተሰለፍንበት ለዛሬ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ለነገ ወረት የሚሆኑ እሳቤና ተግባራት ላይ እንትጋ! መልካም ሳምንት ይሁንለዎ!

በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ ትናንት የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ። ድጋፋችንን በተግባር ለማሳየት ሁላችንም በሐሳብ፣በገንዘብ፣በጉልበት እንዲሁም ያለንን ሁሉ
+3
በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ ትናንት የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ። ድጋፋችንን በተግባር ለማሳየት ሁላችንም በሐሳብ፣በገንዘብ፣በጉልበት እንዲሁም ያለንን ሁሉ ለትምህርት ቤቶች ለማዋል የሚያስችለንን "ትምህርት ለትውልድ" ሀገራዊ ንቅናቄ አስጀምረናል። የላቀች ኢትዮጵያን ለመገንባት፤ ቀድመን የላቁ ትምህርት ቤቶችን አብረን እንገንባ!

የዛሬ አሸናፊነት የትናንት ስራ ውጤት ነው። የነገ አሸናፊነት ግን ዛሬን በሚሰራው ልክ ይወስናል። ዛሬ የትናንት ስራ ውጤት ነው። የማህበራዊ ህይወት መስተጋብር ከማጠናከር ያለፈ ፋይዳ አለው። ጤናማ፣ አምራች፣ የማሰላሰል ብቃት ያለው፣ ታጋሽነትን በተግባር የተማረ ዜጋ እንድናፈራ ያግዛል ስፖርት። ስፖርት የማህበራዊ ዘርፍ ላይ ከሚያመጣው ፋይዳ ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የጎላ ሆኗል። በአሁኑ ጊዜ አለም ላይ እግር ኳስ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ፋይዳ ሁላችንም እንገነዘባለን። ለብዙዎች በቃል ለመጥራት የሚከብድ የገንዘብ መጠን የእግር ኳስ ተጫዎቾች ሳምንታዊ ደመዎዝ መሆኑን መስማት የተለመደ ነው። ስፖርት በአለም አቀፍ ወይ በአህጉር አቀፍ ውድድር ላይ ለሀገር የብሔራዊ አሸናፊነት መገለጫ ሆኖ ይቀመጣል። ለትውልድም የአሸናፊነት የታላቅነት መለኪያ ታሪክ ተደርጎ ይነገራል። አትሌት አበበ ቢቂላ በአለም አደባባይ ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገበት ታሪክ የእኛን ኢትዮጵያዊያን የአሸናፊነት ምልክት ሆኖ እንደሚወሳው ሁሉ በየዘርፉ አሸናፊ የሆኑ ሀገራት ድላቸውን በታሪክ ይዘክሩታል። ስፖርት ፉክክር ብቻ አይደለም ትብብርም አለው። በእግር ኳስ ውስጥ የቡድኑ አጠቃላይ የቡድን ስራ ለሚገኘው ውጤት ያደረጉትን የእርስ በራር ትብብርን ያክል ነው። ስፖርት የወንድማማችነት ማጠናከሪያ የትውውቅ መድረክ ነው። ስፖርት ለመተያየት የማይፈቅዱ ሀገራትን በፍቅር፣ በይቅር ባይነት ሲያስተቃቅፍ ልናይ እንችላለን። ስለዚህም ስፖርት ማህበራዊ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ ፋይዳም አለው ማለት ነው። ስፖርታዊ ውድድር የስፖርት አፍቃሪያንን በደስታ እንባ ሲያራጭ፣ በአሸናፊነት ድል ጮቤ ሲያስረግጥ ልናይ እንችላለን። በስፖርታዊ ውድድር መሸነፍ ከመጣ እንኳን ለእለቱ ቅስም የተሰበረ ቢመስልም ነገን ተስፋ ታደርጋለህ። በስፖርት ውስጥ ነገም ሌላ ቀን ነው። የዛሬ ስህተቶችህን አርመ፣ ትምህርት ወስደህባቸው፣ አስተያየት ተቀብለህ፣ አሰላለፍ ቀይረህ፣ ታክቲክ ቀይሰህ፣ ስትራቴጅ ነድፈህ ለአሸናፊነት ትገባለህ። ነገ ሌላ ቀን ነው፤ ትናንት በመሸነፍ ያዘነ ልብ ዛሬ በተስፋ ይሰራል፤ ነገን ለአሸናፊነት ይፋለማል፤ በጥረቱ፣ በልፋቱ በተለዋዋጭ አለም ውስጥ፣ በተለዋዋጭ የታክቲክ ቀያሪነት ብቃቱ አሸናፊ ሆኖ በመውጣት የትናንቱ የሽንፈት ሀዘን በዛሬ የአሸናፊነት ድል ይሽራል። ስፖርት ሁሉን ነገር እናይበታለን። የመደመር ትውልድ ስፖርታዊ የማዘውተሪያ ቦታዎች ግንባታ ትኩረት የነገ አሸናፊ ትውልድ ግንባታ መሠረቶች ጊዜን ለመቅደም የሚደረግ ሩጫ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

መፍጠር የሀገር እድገት የሚመጣበት መንገድ ነው በመፍጠር ውስጥ የእኛነት ግንባታ አለ። በመፍጠር ውስጥ ትውልድ ማነፅ አለ። መፍጠር በጣም አስፈላጊ ነው። መፍጠር እንደሚያስፈልግ ሁሉ መፍጠን ያስፈልጋ
መፍጠር የሀገር እድገት የሚመጣበት መንገድ ነው በመፍጠር ውስጥ የእኛነት ግንባታ አለ። በመፍጠር ውስጥ ትውልድ ማነፅ አለ። መፍጠር በጣም አስፈላጊ ነው። መፍጠር እንደሚያስፈልግ ሁሉ መፍጠን ያስፈልጋል። አለም አንድ በሆነችበት ውድድር በባዛበት አለም ውስጥ መፍጠን ምርጫ አይደለም ለአሸናፊዎች ግዴታ እንጂ። መፍር እና መፍጠን አንድ ላይ አቀናጅተን ስንተገብር አሻራ ይኖረናል ማለት ነው። አሻራችንን ለትውልድ ለማሳረፍ በመፍጠን እንፍጠር፣ በመፍጠር እንፍጠን! መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

መፍጠር የሀገር እድገት የሚመጣበት መንገድ ነው በመፍጠር ውስጥ የእኛነት ግንባታ አለ። በመፍጠር ውስጥ ትውልድ ማነፅ አለ። መፍጠር በጣም አስፈላጊ ነው። መፍጠር እንደሚያስፈልግ ሁሉ መፍጠን ያስፈልጋ
መፍጠር የሀገር እድገት የሚመጣበት መንገድ ነው በመፍጠር ውስጥ የእኛነት ግንባታ አለ። በመፍጠር ውስጥ ትውልድ ማነፅ አለ። መፍጠር በጣም አስፈላጊ ነው። መፍጠር እንደሚያስፈልግ ሁሉ መፍጠን ያስፈልጋል። አለም አንድ በሆነችበት ውድድር በባዛበት አለም ውስጥ መፍጠን ምርጫ አይደለም ለአሸናፊዎች ግዴታ እንጂ። መፍር እና መፍጠን አንድ ላይ አቀናጅተን ስንተገብር አሻራ ይኖረናል ማለት ነው። አሻራችንን ለትውልድ ለማሳረፍ በመፍጠር እንፍጠን! መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ሌብነት የህሊና ቢስነት መገለጫ የብልፅግናችን ሳንካ ነው። ሌብነት የራስ ህሊና ከመካድ ጀምሮ፣ ህዝብን የማሰቃየት፣ ሀገርን የመካድ ለሆድ የማደር፣ መገለጫ ባህሪ ነው። ሌብነት ከአስተሳሰብ ይጀምራል። ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት ሰው መብቱ የሆነውን አገልግሎት ግዛኝ ብሎ አፍ አውጥቶ ይጠይቃል። የተቸገረ ተገልጋይም የመገልገል መብቱን ደመዎዝ ከፍሎ የሚያሰራውን አገልጋይ፣ መልሶ ብር በመስጠት ከማይሰጡት የተሻለ ለመገልገል ይሞክራል። ህሊና ቢስነት መቀበል ብቻ አይደለም፣ መስጠትም እንጂ። ብር ልክፈልና ፈፅምልኝ ማለት መክፈል የማይችለው ወገኔ ይሰቃይ እኔ በገንዘቤ፣ አንተ በስልጣንህ ሀገርን እንካዳት ማለት ነው። ሰጭ በሌለበት ተቀባይ አይኖርም። ተቀባይ በሌለበት የሚሰጥ አይመጣም። ሌብነት ሰጭውንም ተቀባዩንም የሚመለከት ነው። ዛሬ አገልግሎት በገንዘብ የገዛ፣ ነገ ሀገር በሚፈልገው ነርር ሊሸጣት አያንገራግርም። ዛሬ ኃላፊነት በገንዘብ የሸጠ ሌባ፣ ነገ አቅሙን ካገኘ ሀገር ለመሸጥ ወደ ኋላ አያመነታም። ሌብነትን የምንፀየፈው ብቻ ሳይሆን የምንታገለውም ጭምር ነው። የሌብነት ትግል መስፈርት አሟልተህ ለመገልገል በተገኘህበት ወቅት አለገለግልም ሲል ነው መታገል መጀመር። ዛሬ መብታችን የሆነውን ግልጋሎት ሳናገኝ ስንቀር ለምን ብሎ መጠየቅ አስፈላጊ ነው። ሌብነት ማጥፋት የሚቻለው መንግስት ከህብረተሰቡ ጋር መቀናጀት ሲቻል ነው። ዛሬ በምን አገባኝ ስሜት የምናልፋት የአገልግሎት እንግልት ነገ ከፍተኛ የሀገር ችግር ትሆናለች። እናም ባለንበት ኃላፊነት ሁሉ ኃላፊነታችንን እንወጣ። በሄድንበት የግልጋሎት ቦታ ሁሉ መስፈርት ማሟላታችንንና የእኛን ግዴታ መወጣታችንን እርግጠኛ ሆነን ግልጋሎት ያጣንበትን ቦታ ሁሉ እናጋልጥ እንታገል። የማይገባንን አንጠይቅ የሚገባንን መብታችንን እናስጠብቅ። @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ጊዜው ውድድር የበዛበት ነው። በውድድር ውስጥ ፍጥነት አሸናፊ ያደርጋል። ፍጥነት ዘመኑን የሚመጥን ካልሆነ ዝም ብሎ መፍጠን ብቻ ነው። በመፍጠን ውስጥ ደግሞ መፍጠር ግድ ይላል። ዘመኑን የሚመጥን ስራ
ጊዜው ውድድር የበዛበት ነው። በውድድር ውስጥ ፍጥነት አሸናፊ ያደርጋል። ፍጥነት ዘመኑን የሚመጥን ካልሆነ ዝም ብሎ መፍጠን ብቻ ነው። በመፍጠን ውስጥ ደግሞ መፍጠር ግድ ይላል። ዘመኑን የሚመጥን ስራ መፍጠር ካልቻልን መፍጠናችን ተከታይ ከመሆን አያድንም። እንፍጠን ፍጥነቱ በፈጠራ የታጀበ ይሁን። እንፍጠር ፈጠራችን በፍጥነት ውስጥ ይሁን። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ለመላው የክፍለ ከተማችን እስልምና ተከታይ ነዋሪዎቻችን እንኳን 1444ኛው ኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! አቶ ሙሉጌታ ጉሉማ የብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አረፋ ለመስዋዕትነት ከመዘጋጀት፣ ለመስዋዕትነት ከመቅረብ፣ መስዕዋት ከማድረግ ቀጥሎ የመጣ የብስራት በዓል ነው። በእስልምና አስተምሮ እራሱን ለፈጣሪ መስዕዋት ለመሆን ተዘጋጅቶ በሙሉ ልብ በመቅረብ፣ ልጅን መስዕዋት በማድረግ ምክንያት የመጣ የደስታ በዓል ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ሀገራችንን ኢትዮጵያን የበለፀች ለማድረግ የሚጠይቀን መስዕዋትነት አለ። ትናንት ህይወታቸውን የከፈሉ በጊዜያቸውን ሙሉ ለሀገር የሰሩ አሉ። ዛሬ ከእኛ ሀገር የምትጠብቀው ኃላፊነት አለ። ዛሬ የሚጠበቀው ኃላፊነት የህይወት መስዋዕትነት አይደለም። ዛሬ የሚጠይቀን ያለንን ጊዜ፣ ጉልበት፣ እውቀት አንድ ላይ አቀናጅተን በመስራት  እራሳችንን ቀይረን ሀገር እንድትበለጽግ ማድረግ ነው። ዛሬ የሚጠይቀን ወንድማማችነትን/ እህትማማችነትን ማፅናት ህብረብሔራዊ አንድነትን መጠበቅ እና ማጠንከር ነው። ኢትዮጵያ መልከ ብዙ ነች፤ ብዙ መልኮች በአንድ ላይ ተሸምነው የተሰጧት ውብ ተፈጥሮ ያላት ሀገር ነች። አረፋ ልዩነታችንን ውበት አንድነታችንን ጥንካሬ መሆኑን የሚያሳይ በዓል ነው። አረፋ የመስጠት፣ የፍቅር፣ ለአመንበት ጠቃሚ እና አስፈላጊ ጉዳይ መስዋዕትነት የመክፈል በዓል ነው። ለታሳቢነት የሚታረደው እርድ ለ3 ተከፍሎ አንዱ አቅም ለሌለው ድሃ የሚሰጥ ነው። አንዱ እጅ ከጎረቤት ጋር የምንጋራው ይሆናል። አንዷን እጅ ብቻ ለራስ የመጠቀም እምነታዊ ትዕዛዝ ያለበት የመስጠትና የደግነት በዓል ነው። ይህንን በዓል በአስተምሮው መሰረት ጎረቤቶቻችንን ጠይቀን፣ አቅም የሌላቸውን ከአለን ላይ አካፍለን በደስታ፣ በፍቅር እናክብረው። እንደ አስተምህሮው ለሀገር ብልፅግና እውን መሆን፣ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት መጠናከር የሚጠበቅብንን መስዕዋትነት ለመክፈል እንዘጋጅ። በድካሜ መልካም የአረፋ በዓል ይሁንልን። ኢድ ሙባረክ!

የመጭው አለም የሚያስፈልጋት ከምንም በላይ ንፁህ አየር መሆኑ አይቀሬ ነው። ንፁህ አየር እውን መሆኛው አንዱ መንገድ አረንጓዴ ማልበስ ይሆናል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity P
የመጭው አለም የሚያስፈልጋት ከምንም በላይ ንፁህ አየር መሆኑ አይቀሬ ነው። ንፁህ አየር እውን መሆኛው አንዱ መንገድ አረንጓዴ ማልበስ ይሆናል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ወንድማማችነት በፅንፈኝነት ይቀጭጫል ። ፅንፈኝነት አጥፊ አስተሳሰብ፣ አጥፊ ተግባር ነው፡፡ በፅንፈኝነት የሚመጣ ጥፋት ደግሞ ብዙ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ፅንፈኝነት ከኔ ውጭ ላሳር ማለት ከመንገድ የሚያ
ወንድማማችነት በፅንፈኝነት ይቀጭጫል ። ፅንፈኝነት አጥፊ አስተሳሰብ፣ አጥፊ ተግባር ነው፡፡ በፅንፈኝነት የሚመጣ ጥፋት ደግሞ ብዙ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ፅንፈኝነት ከኔ ውጭ ላሳር ማለት ከመንገድ የሚያስቀር ወደ ኋላ የሚጎትት አስተሳሰብ ነው፡፡ሁላችንም ፅንፈኝነትን በመታገል ያንድነት ምሶሶ የሆነውን ወንድማማችነትና እህትማማችነትን እንገባ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ህብረ-ብሄራዊነት በኢትዮጵያዊ አንድነት ይታሰራል፡፡ በወንድማማችነት እና እህትማማችነት ፍቅር ይፀናል፡፡ መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
ህብረ-ብሄራዊነት በኢትዮጵያዊ አንድነት ይታሰራል፡፡ በወንድማማችነት እና እህትማማችነት ፍቅር ይፀናል፡፡ መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

በየደቂቃው በሚለዋወጥ አለም ውስጥ መፍጠን አስፈላጊ ነው። በውድድር ሜዳ ውስጥ ፍጥነት ከሌለ አሸናፊ ሆኖ መውጣት አይቻልም። በመፍጠን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለመደው አሰራር ተጉዞ
በየደቂቃው በሚለዋወጥ አለም ውስጥ መፍጠን አስፈላጊ ነው። በውድድር ሜዳ ውስጥ ፍጥነት ከሌለ አሸናፊ ሆኖ መውጣት አይቻልም። በመፍጠን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለመደው አሰራር ተጉዞ የተለየ ውጤት መጠበቅ አይቻልም። የተለየ ውጤት የምንፈልግ ከሆነ መፍጠር ያስፈልጋል። በመፍጠን እና በመፍጠር የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ! መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

የሀገር ሉዓላዊነት ጠባቂ፣ ህይወት ሰጥቶ ሀገር የሚጠብቅ፣ በሀገር ክብር የማይደራደር ወታደር ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን የአድዋ ድል ባለቤት ልጆች የጀግንነት መገለጫ ለሀገር ክብር ሟቾች ነን። ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀት፣ የሀገር ክብር ያስቀደመ፣ ለሀገር ሲል ቀድሞ የሚሰዋ በዳር ድንበር የማይደራደር የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት። ሊተናኮስ ያሰበን ጠላት ቀድሞ ሀሳቡን የሚያስለውጥ ሀይል ባለቤት፣ ለእኛ ኢትዮጵያዊያን ኩራት፣ ለወዳጆቻችን ግርማ ሞገስ የአድዋ ልጆች መከላከያ ሰራዊት! መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

"የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፖለቲካ፣ ከሀይማኖት፣ ከብሄር ነፃ የሆነ ንፁ የመላው የኢትዮጵያዊያን የኩራት ምንጭ ነው።" ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግ
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፖለቲካ፣ ከሀይማኖት፣ ከብሄር ነፃ የሆነ ንፁ የመላው የኢትዮጵያዊያን የኩራት ምንጭ ነው።" ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ሁሉም ነገር ሲጀመር ከባድ ይመስላል። አብዛኞቹ ሌማታችን በከተማ ግብርና ስራችን ሞልቶ ይትረፈረፋል ሲባል እውነት አልመሠላቸውም። ዛሬ ላይ ግን አዋጭነቱ ጥያቄ ውስጥ አይገባም ምክንያቱም ብዙዎች አሳ
ሁሉም ነገር ሲጀመር ከባድ ይመስላል። አብዛኞቹ ሌማታችን በከተማ ግብርና ስራችን ሞልቶ ይትረፈረፋል ሲባል እውነት አልመሠላቸውም። ዛሬ ላይ ግን አዋጭነቱ ጥያቄ ውስጥ አይገባም ምክንያቱም ብዙዎች አሳክተውት አይተናልና። ባለን ቦታ የከተማ ግብርና ስራን በመስራት ሌማታችን ይትረፍረፍ ለጎረቤት እንትረፍ። #የሌማት_ትሩፋት በኮልፌ መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

"አበክረን ልሰራበት ከሚገባ ኮር ኤሪያ አንዱ ጤና ነው። ጤና ማለት ሆስፒታል ማለት ብቻ አይደለም ጤና ማለት መድሀኒት ማለት ብቻ አይደለም የአኗኗር ዜይ ነው።" ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ @K
"አበክረን ልሰራበት ከሚገባ ኮር ኤሪያ አንዱ ጤና ነው። ጤና ማለት ሆስፒታል ማለት ብቻ አይደለም ጤና ማለት መድሀኒት ማለት ብቻ አይደለም የአኗኗር ዜይ ነው።" ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

የመደመር ትውልድ፤ ልዩነቱን የሚያከብርና አንድነቱን የሚያጠናክር ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
የመደመር ትውልድ፤ ልዩነቱን የሚያከብርና አንድነቱን የሚያጠናክር ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና