en
Feedback
Kolfe P.P - ብልፅግና

Kolfe P.P - ብልፅግና

Open in Telegram
1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
photo content

አረንጓዴ አሻራ ከእኛ የተሻገረ የአፍሪካ ኩራት የአለም የስጋት መፍትሔ! ያለንበት ዘመን አለም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በተለያዩ ጊዚያት ያልተተነበዩ ድንገት የተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የሰው ልጅ ህይወትን እና ንብረት ሲያጠፋ እናያለን። ሰደድ እሳት የጎርፍ አደጋ ተከሰቱ የሚሉት ዜናዎች ለጆሮ አዲስ አልሆን ብሎ አይተናል። ኢትዮጵያ የመፍትሔው አካል በመሆን ያለፉትን አራት አመታት ለውጡን ተከትሎ የአረንጓዴ አሻራ ማስቀመጥ ችላልች ቢሊዮን ችግኞች ወደ ዛፍነት መቀየር ተችሏል። ዘፈናችን ለመምለሟ ሀገሬ እያልን የተራቆተ መሬት ያላት ሀገር ይዘን እንዳንቀጥል ወደ ለምለምነት እየመለሳት ይገኛል። ያለፉት አራት አመታት የመጀመሪያው ዙር አረንጓዴ አሻራ ተግባራችን ከእቅዳችንም የተሻገረ አሻራ ማስቀመጥ ችለናል። አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር አረንጓዴ አሻራ ስንጀምር ከኢትዮጵያ ፕሮጀክትነት የተሻገረ የአፍሪካ ህልም መሆን እንድችል እየተሰራ ነው። የኢጋድ አባል ሀገራትም አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ መሆኑን በመውሰድ ተግባሩን በመሪዎቹ በጋራ አስጀምረውታል። ኢትዮጵያ የሀይል ምንጫ ታዳሽ ሀይል ነው። ታዳሽ ሀይል አማራጭ የሚጠቀም ደግሞ አረንጓዴ አሻራ የማይነጥፍ ወቅቱን የጠበቀ የተስተካከለ ዝናብ እንድኖር በማድረግ ተፈጥሮ ኡደቷን ጠብቃ እንድትቀጥል ያደርጋል። የበረሃማነት መስፋፋትን የሚያጠፋ፣ የድርቅ መከሰትን የሚያስቀር የንፁህ አየር ምንጭ የአረንጓዴ አሻራ ውጤት ነው። አረንጓዴ አሻራችን ችግኝ የመትከል ዛፍ የማድረግ ጉዳይ ብቻ አይደለም። የምንተክላቸው ችግኞች ዛፍ ሲሆኑ ለምግብነት የሚውሉ ማድረግ ጭምር እንጂ። የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ስርዓታችን እውን የሚሆንበት አንዱ መንገድ አረንጓዴ አሻራችን ነው። አረንጓዴ አሻራ ያለንን ተስማሚ አየር ጠብቆ የማቆየት፣ የአፈር ለምነትን የመመለስ፣ የአፈር መሸርሸርን የመከላከል፣ በረሃማነትን የማስቀረት፣ ድርቅ እንዳይከሰት የመከላከል አቅሙ እንዳለ ሆኖ በራሱ ምርት የሚሰጥም ይሆናል። የችግኝ ተከላ ስራችን አሻራ ማስቀመጥ ነው የምንለውም ለዚሁ ነው። ንፁህ አየርን አጎናፅፎ፣ የአለም ስጋትን ቀርፎ ምርታማነትን የሚጨምር ፕሮጀክት ለነገው ትውልድ የሚቀመጥ ለአለም የሚበረከት አሻራ ነው። የያዝነውን እቅድ አሳክተን የበለፀገች ተስማሚ ለምለም ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁላችንም አሻራችንን እናስቀምጥ። መልካም ሳምንት ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

የነገዋ ኢትዮጵያ ርጥብ፣ ለም፣ እና በዛፎቿ ጥላ ስር የሚታረፍባት ትሆናለች።መትከል እንጂ መንቀል ባህል መሆኑ ይቀራል።ማሳደግ እንጂ መቁረጥ ልማድነቱ ያበቃል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Pr
የነገዋ ኢትዮጵያ ርጥብ፣ ለም፣ እና በዛፎቿ ጥላ ስር የሚታረፍባት ትሆናለች።መትከል እንጂ መንቀል ባህል መሆኑ ይቀራል።ማሳደግ እንጂ መቁረጥ ልማድነቱ ያበቃል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

የነገዋ ኢትዮጵያ ርጥብ፣ ለም፣ እና በዛፎቿ ጥላ ስር የሚታረፍባት ትሆናለች።መትከል እንጂ መንቀል ባህል መሆኑ ይቀራል።ማሳደግ እንጂ መቁረጥ ልማድነቱ ያበቃል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Pr
የነገዋ ኢትዮጵያ ርጥብ፣ ለም፣ እና በዛፎቿ ጥላ ስር የሚታረፍባት ትሆናለች።መትከል እንጂ መንቀል ባህል መሆኑ ይቀራል።ማሳደግ እንጂ መቁረጥ ልማድነቱ ያበቃል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

"ለሚቀጥለው ትውልድ የሚተው መልካም ነገር ማኖር ካለብን አንደኛውና ቀላሉ ነገር ነገን ዛሬ መትከል ነው፡፡" - ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity P
"ለሚቀጥለው ትውልድ የሚተው መልካም ነገር ማኖር ካለብን አንደኛውና ቀላሉ ነገር ነገን ዛሬ መትከል ነው፡፡" - ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ መልካም ቀን ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ሚዲያ ሀገር ይገነባል ወይ ደግሞ ሀገር ያፈርሳል። አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ መገንባት የፖለቲካዊ ህልም ነው። የዚህ ህልም መሳኪያ ብቸኛው መንገድ ሚዲያው ነው። እሱም በሀሳብ የመግባባት
ሚዲያ ሀገር ይገነባል ወይ ደግሞ ሀገር ያፈርሳል። አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ መገንባት የፖለቲካዊ ህልም ነው። የዚህ ህልም መሳኪያ ብቸኛው መንገድ ሚዲያው ነው። እሱም በሀሳብ የመግባባት የጋራ የሆነ ነገር ማበጀት መቻል ነው። የጋራ ጉዳይ እንዲፈጠር ሚዲያ የማይተካ ሚና አለው። ሚዲያ የሚግባባ ማህበረሰብ የመፍጠር አቅም አለው። እኛ ኢትዮጵያዊያን በሁለንተናዊ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ እንፈልጋለን። ፍላጎታችን እውን እንዲሆን በሁሉም የሚዲያ አማራጮች ላይ የሚያግባቡንን ሀሳብ እንዝራ። የሚከፋፍሉ፣ ከህልማችን የሚነጥሉ ሀሳቦች የጠላት መሆናቸውን አውቀን እንታገላቸው። ተባብረን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተገራ ሚዲያ አጠቃቀም ይኑረን። የሚዲያ አጠቃቀማችን አንዳንዱ በማወቅ አብዛሃኛው ባለማወቅ ሀገር አፍራሽ ሲያደርገው ይታያል። ዘመኑ በእጃችን ላይ ባለ ስልክ ሁላችንንም ጋዜጠኛ፣ መረጃ ሰጭም ተቀባይም ስላደረገን ይህንን ሁኔታ በመጠቀም ሚዲያውን ለሀገር መገንቢያ እናውለው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

የሀገር ከፍታ የሚረጋገጠው በዜጎች በመስራትና በማምረት ብቃት ነው። ዜጎች አምራች ዜጋ ሲሆኑ የግል ፍላጎት አሟልተው ለሌላው መትረፍ ይችላሉ። ለሌሎች የስራ እድል ይፈጥራሉ። ስራ እድል ሰሪ ኃይልን
የሀገር ከፍታ የሚረጋገጠው በዜጎች በመስራትና በማምረት ብቃት ነው። ዜጎች አምራች ዜጋ ሲሆኑ የግል ፍላጎት አሟልተው ለሌላው መትረፍ ይችላሉ። ለሌሎች የስራ እድል ይፈጥራሉ። ስራ እድል ሰሪ ኃይልን ያበራክታል። ሰሪ ኃይል መበራከቱ የዜጎች የመግዛት አቅምን ያሳድጋለል። የዜጎች የመግዛት አቅም ማደግ የአቅርቦት መጨመርና ጥራት ላይ ውድድር መፈጠር የሀገር እድገትን የዜጎች ምቾትን ያመጣል። ዜጎች ገቢያቸው ከፍ ሲል ግብር ይከፍላሉ። የከፈሉት ግብር አገልግሎቱን ያሳልጣል፤ መሰረተ ልማት ይሟላበታል። ስለዚህም የሀገር እድገት መሠረት የዜጎች ጠንካራ የስራ ባህል መኖሩ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

"ነገን ዛሬ እንትከል" ምንጊዜም ቢሆን ነገ ዛሬ ነው የሚተከለው። ዛሬ ያልሰራነው ነገ በፍፁም አይኖርም። ህልም ያላቸው ሰዎች ነገን ዛሬ ነው የሚያዩት። ማየት ብቻ ሳይሆን ዛሬ ላይ ይሰሩታል። ዛሬን እየኖርን ያለነው ትናንት ላይ ሆነው ለነገ ብለው በአስቀመጡልን አሻራ ነው። የዛሬዎቹ እኛ ደግሞ ለነገዎቹ አሻራ ማስቀመጣችን ግድ ይለናል። አለም ጭንቅ ላይ የሆነችበት፣ በለፀጉ የምንላቸው ሀገራት በካርቦን ልቀት አለምን መበከላቸው ሳያንስ አለምን በሚያጠፋ የጦር መሳሪያ ይፎካከራሉ። የጭንቀቱ መፍትሔዎች መሆን ያስፈልጋል። የችግሩ መፍትሔ ስንሆን የችግራችን መፍትሔ ይገኛል። ከሚያስፈልገን ነገር አንዱ ገቢ ነው። ከገቢ ምንጮች አንዱ ደግሞ ቱሪዝም ነው። አረንጓዴ አሻራ በራሱ የቱሪስት መስህብ ነው። ለአለም ጭንቅት መፍትሔ፣ የኢትዮጵያን ምድረ ገነትነት እውን የምናደርግበት፣ ልምላሜዋን የምናስጠብቅበት አረንጓዴ አሻራ ነው። የመጭው አለም የሚያስፈልጋት ከምንም በላይ ንፁህ አየር መሆኑ አይቀሬ ነው። ንፁህ አየር እውን መሆኛው አንዱ መንገድ አረንጓዴ ማልበስ ይሆናል። እኛ ኢትዮጵያዊያን ደግሞ ለአለም የምናበረክተው መልካምን ነገር አለን። አለም በአየር ንብረት ለውጥ ጭንቀት ውስጥ ባለችበት ጊዜ በአሁኑ ወቅት በአረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያን እያለበስን እንገኛለን። ባለፉት 4 አመታት 20 ቢሊዮን ችግኝ መትከል አቅደን 25 ቢሊዮን ችግኝ በማልበስ አረንጓዴዋ ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ላይ ነን። የኢትዮጵያችን አፈር እንኳንስ ተክለንበት የወደቀ አብቅሎ ለምርት የሚያበቃ ነው። በአረንጓዴ አሻራችን ስራችን ሀገር በቀል ችግኞች ላይ ከማተኮር ባለፈ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች ላይ እናተኩር። በከተማችን አዲስ አበባ የማንጎ እና የአቡካዶ ዛፍ ከውበቱ ተጨማሪ ፍሪያማ እንደሆነ ባለፉት ጊዜያት ከተተከሉት አይተናል። በጊቢያችን አንድ የአቡካዶ እና አንድ የማንጎ ዛፍ ለመትከል ለራሳችን ቃል እንግባ። በመጭው ክረምትም ቃላችንን አክብረን እንትከል። የዚህ አመት አረንጓዴ አሻራችን ላይ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን እንትከል። በአንድ በኩል ለምግብ ጥያቄ፣ በሌላኛው ደግሞ ለአየር ንብረት ለውጥ ስጋት መልስ እንስጥ። ሁላችንም የድርሻችንን ከተወጣን የለመለመች፣ የበለፀገች፣ ለአለም የተረፈችን ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይቻለናል። መልካም ሳምንት ይሁንለዎ! Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና @

"እኛ ኢትዮጵያውያን ለልጆቻችን ባንክ የምናስቀምጠው ገንዘብ ባንችል ለልጆቻን በየመስኩና በየተራራው የምናኖረው ዛፍ ቢኖር ይህ ዛፍ ምግብ ይሆናል፤ ይህ ዛፍ መድሃኒት ይሆናል፤ ይህ ዛፍ አለምን ከሚያ
"እኛ ኢትዮጵያውያን ለልጆቻችን ባንክ የምናስቀምጠው ገንዘብ ባንችል ለልጆቻን በየመስኩና በየተራራው የምናኖረው ዛፍ ቢኖር ይህ ዛፍ ምግብ ይሆናል፤ ይህ ዛፍ መድሃኒት ይሆናል፤ ይህ ዛፍ አለምን ከሚያሰጉና ዋነኛው ከሆነው የአየር ንብረት ለውጥ አደጋ የሚታደገን ነው።" - ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

አንድ ሀገር እርዳታ እስከጠየቀ ጊዜ የሰጭውን ፍላጎት ለማሟላት መስራት ግድ ይለዋል። ሰጭና ለጋስ የሚያደርገውን ሀብት ማመንጨት ከቻለ ግን ያሰበውን ያለመውን መተግበር ይችላል። ለልመና የተዘረጋ እጅ
አንድ ሀገር እርዳታ እስከጠየቀ ጊዜ የሰጭውን ፍላጎት ለማሟላት መስራት ግድ ይለዋል። ሰጭና ለጋስ የሚያደርገውን ሀብት ማመንጨት ከቻለ ግን ያሰበውን ያለመውን መተግበር ይችላል። ለልመና የተዘረጋ እጅ የተሰጠውን ሀብት የሚከፍል ስራ እንድሰራ መገደዱ አይቀሬ ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን የተሟላ ተፈጥሮ፣ የሚሰራ የሰው ኃይል፣ የሚመረትበት አፈር ይዘን ከራሳችን ሌማት አልፈን ለሌሎች ሀገራትን መመትረፍ ያስችለናል። ኢትዮጵያ ተሟልቶ የተሰጣት ተፈጥሮ ያላት ሀገር ነች። ሁሉም የአየር ንብረት የተቸራት ሀገር ነች። በአለም ላይ በምርምር ከተገኙት 28 የአፈር አይነቶች 25ቱ የተቸራት ድንቅ ሀገር ነች። እኛ ኢትዮጵያዊያን የሚጠበቅብን ያለንን የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ሀብት 24/7 በመስራት ሀብታችንን በአግባቡ መጠቀም መቻል ነው። ከዛሬ የተሻገረ ለነገ የሚሆን ለልጅ ልጅ የሚተርፍ አሻራ የማስቀመጥ ኃላፊነትን መወጣት ነው። #የሌማት_ትሩፋት ተመግቦ ከማደር ያለፈ ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን በሌማታችን ላይ የማሟላት ጉዳይ ነው። የሌማት ትሩፋት በትንሽ ቦታ ለራስ የሚመግብ ለገበያ የሚተርፍ ምርት በማምረት ትኩስ፣ ጤናማ የተትረፈረፈ ማዕድ ማሟላት ነው። በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ አስተዳደር በከተማ ግብርና ስራችን እሰከአሁን ያየናቸውን መልካም ጅማሮ በ3ኛው የ90 ቀን የሌማት ትሩፋት ተግባራችን የበለጠ አጠናክረን መቀጠል አለብን። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ችግሮቻችን በውይይት የመፍታት ልምድ ማካበት ለተውልድ ግንባታው አስተዋጽኦው የጎላ ነው። ለኢትዮጵያ ብልፅግና የእኛ ሀገራዊ ሁሉን አቀፍ አካታች ምክክር ማድረግ የማይተካ ሚና ይኖረዋል። መልካም ቀን
ችግሮቻችን በውይይት የመፍታት ልምድ ማካበት ለተውልድ ግንባታው አስተዋጽኦው የጎላ ነው። ለኢትዮጵያ ብልፅግና የእኛ ሀገራዊ ሁሉን አቀፍ አካታች ምክክር ማድረግ የማይተካ ሚና ይኖረዋል። መልካም ቀን ይሁንልዎ! @

የመደመር ትውልድ እኩልነትን በአንድ ዓይነትነት ውስጥ ሳይሆን፤ በመከባበርና አብሮ በማሸነፍ እሴቶቹ ውስጥ የሚያይ ትውልድ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና
የመደመር ትውልድ እኩልነትን በአንድ ዓይነትነት ውስጥ ሳይሆን፤ በመከባበርና አብሮ በማሸነፍ እሴቶቹ ውስጥ የሚያይ ትውልድ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ትምህርት ቤቶቻችን የእውቀት መሸመቻ፣ የትውልድ መፍለቂያ፣ የነገ ተስፋ የሚለመልምበት ተቋም ነው። ትምህርት ቤቶቻችን ላይ ጥራት፣ ፍትሀዊ ተደራሽነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ነገ ተባብረን ብሩህ
ትምህርት ቤቶቻችን የእውቀት መሸመቻ፣ የትውልድ መፍለቂያ፣ የነገ ተስፋ የሚለመልምበት ተቋም ነው። ትምህርት ቤቶቻችን ላይ ጥራት፣ ፍትሀዊ ተደራሽነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ነገ ተባብረን ብሩህ እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

ዴሞክራሲ ስር መስደድ የሚችለው የህግ የበላይነት ሲከበር ነው። በብዝሃነት ውበት የተቸረች ሀገር ዴሞክራሲ እጅግ አስፈላጊ ይሆናል። ህብረ ብሔራዊ በአንድነት ገመድ መታሰር ለሁለንተናዊ ብልፅግና ወሳኝ
ዴሞክራሲ ስር መስደድ የሚችለው የህግ የበላይነት ሲከበር ነው። በብዝሃነት ውበት የተቸረች ሀገር ዴሞክራሲ እጅግ አስፈላጊ ይሆናል። ህብረ ብሔራዊ በአንድነት ገመድ መታሰር ለሁለንተናዊ ብልፅግና ወሳኝ ነው። ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ያለ ዴሞክራሲ እውን ማድረግ አይቻልም። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ፅንፈኝነት የሀገር ነቀርሳ፤ የሰላማችን ጠንቅ ነው! ፅንፈኝነት የእኔ ብቻ እውነት፣ እኔ ብቻ ተጎ፣ እኔ ብቻ ትክክል ወይ እኔ ብቻ አስፈላጊ ብሎ የማመን የአንድነት ፀር የሆነ አስተሳሰብ ነው። አንድነትን በመናድ የሰላም አማራጭን በመርገጥ እኔ ያልኩት ካልሆነ የጠፋው ይጥፋ የሚል የሞኝ አስተሳሰብ ነው። ሚዛናዊነትን ካጣን የእኔ እውነታ ከእሱ እውነታ ጋር ያለው ልዩነት ብለን ካልመዘንን፣ ከእኔነት ወጥተን ወደ እኛነት ካልመጣን ብዝሃነት ባለበት ሀገር ውስጥ ሁልጊዜም የጥፋት ምንጭ ይሆናል። ፅንፈኝነት ባለበት በፍፁም ሰላም ሊሰፍን አይችልም። ሰላም የሚሰፍነው በአንድነት ውስጥ ነው። አንድነት በብዙሃነት ውስጥ ደግሞ መምጣት የሚችለው በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነው። ፅንፈኝነት አንድነትን የሚያጠፋ ወንድማማችነትን እህትማማችነትን የሚበጣጥስ ነው። አለም አንድ በሆነችበት በዚህ ዘመን እኔነት ወደ እኛነት ማደግ ካልቻለ ያለምናትን ኢትዮጵያ እውን ማድረግ አንችልም። ኢትዮጵያ የብዙ ማንነቶች ባለቤት ናት። ኢትዮጵያ የብዙ ባህል፣ ቋንቋ፣ እምነት፣ ወግ፣ ስርዓት ያላቸው ብዝሃነታቸውን እንደ ድር እና ማግ በአንድነት ሸምና ከአንዱ እውቀትን፣ ከሌላኛው ጥበብ ከዛም ብልሃትን ደምራ የያዘች ሀገር ነች። ጥበብ ያለ እውቀት፣ እውቀት ያለ ብልሃት ውብ ነገርን ሊፈጥር አይችልም። ኢትዮጽያ ውስጥ በእምነት ወይ በብሔርም ጭንብል ውስጥ ሆኖ የራሱን አላማና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረግ ጥረት ህዝብን የሚጎዳ የሀገርን ጥቅም የመናድ አላማ ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ጉልበታችን ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት መሰረት ላይ አጠንክሮ መገንባት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሰላምን ይሻል። የልብ መሻት በተግባር መገለጥ አለበት። ተግባሩም ፅንፈኝነትን በመዋጋት አንድነትን በማጠንከር ሰላማችንን በማስፈን ይገለጣል። መልካም ሳምንት ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party-ብልፅግና

ንቁ ትውልድ ነገሮችን የሚከታተል፣ አዝማሚያዎችን በቶሎ የሚለይ እና የሚያዋጣውን መንገድ በፍጥነት የሚቀይስ ትውልድ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና
ንቁ ትውልድ ነገሮችን የሚከታተል፣ አዝማሚያዎችን በቶሎ የሚለይ እና የሚያዋጣውን መንገድ በፍጥነት የሚቀይስ ትውልድ ነው። መልካም ቀን ይሁንለዎ! @Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና