en
Feedback
طــــريــقــة الــنــجــاح

طــــريــقــة الــنــجــاح

Open in Telegram

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

Show more
623
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1630 days
Posts Archive
👉 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል ስድስት ነብዩላሂ ኢብራሂም የጌታቸውን ትእዛዝ ብቸኛ ልጃቸውን በማረድ ለመፈፀም ባሳዩት ቁርጠኛና አስገራሚ አቋም አላህ ሌላ ልጅም እንደሚሰጣቸው ብስራት ላከላቸው ። ይህም በተከበረው ቃሉ ከመጀመሪያ ሚስታቸው ሳራ ኢስሓቅና የልጅ ልጃቸው የዕቆብም የሚሰጣቸው መሆኑን በሚቀጥለው የሁድ ምእራፍ 71ኛው ላይ አንቀፅ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – وَامْرَأَتُهُ قَائِمَةٌ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَاهَا بِإِسْحَاقَ وَمِن وَرَاءِ إِسْحَاقَ يَعْقُوبَ ሚስቱም የቆመች ስትኾን (አትፍራ አሉት) ሳቀችም፡፡ በኢስሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ (በልጁ) በያዕቁብ (አበሰርናት)፡፡ ሳራ እኔ አሮጊት ሆኜ ባለቤቴም ሽማግሌ ሆኖ ሳለ እወልዳለሁኝ እንዴ አለች በመገረም ። መላኢካዎችም በአላህ ጉዳይ ትገረሚያለሽን አሉ ። አላህ ሁሉን ቻይ ነውና ያሻውን ይሰራል ። እሱ ካሻ ከአሮጊት ማህፀን ነብይ ይፈጥራል ። ይህንንም በዛው ምእራፍ ቀጥሎ ባለው አንቀፅ ይነግረናል : – قَالَتْ يَا وَيْلَتَىٰ أَأَلِدُ وَأَنَا عَجُوزٌ وَهَٰذَا بَعْلِي شَيْخًا ۖ إِنَّ هَٰذَا لَشَيْءٌ عَجِيبٌ (እርሷም) ዋልኝ! እኔ አሮጊት ይህም ባሌ ሽማግሌ ሆኖ ሳለ እወልዳለሁን ይህ በእርግጥ አስደናቂ ነገር ነው አለች ፡፡ قَالُوا أَتَعْجَبِينَ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۖ رَحْمَتُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ ۚ إِنَّهُ حَمِيدٌ مَّجِيدٌ «ከአላህ ትዕዛዝ ትደነቂያለሽን የአላህ ችሮታና በረከቶቹ በእናንተ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ይሁን እርሱ ምስጉን ለጋስ ነውና» አሉ ፡፡ ነብዩላሂ ኢብራሂም ኢስማኢልን ለማረድ ወስነው አላህ በሙክት ቀይሮላቸው ካበሰራቸው በኋላ ወደ ሻም ተመልስው ወደ አላህ አምልኮ ይጣሩ ጀመር ። ኢስማኢልም አደጉ እድሜያቸውም ለነብይነት ደረሰ አላህ ነብይ አደረጋቸው ። ዳዕዋ ማድረግ ጀመሩ ከጁርሁም ጎሳዎችም የሆነች ሴት አገቡ ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ቤተሰባቸውን ለማየት ወደ መካ መጡ ። ነብዩላሂ ኢስማኢል ለአደን ወጥተዋል ። ሚስትየውን አገኙ ስለኑሯቸው ጠየቁዋት በጣም በችግር ነው ያለነው ። አዝመራም የለም ። ምግብም ውሀም የለም ረሀብና ጥም ነው አለቻቸው ። አላህ በወሰነው ነገር ባለመውደድዋ ደስ አላላቸውም ። ባለቤትሽ ሲመጣ የቤትህን መቃን ቀይረው ብለኋል ብለሽ ንገሪው ብለው ወደ ሻም ተመለሱ ። ነብዩላሂ ኢስማኢል ከአደን ተመለሱ ። የመጣ ሰው ነበር ወይ ብለው ጠየቁ አው አንድ ሽማግሌ እንግዳ መጥቶ ነበር አለችው ። ምን ጠየቀሽ አሉ ስለኑሯችን ጠየቀኝ ከዛም ያለንበትን ችግር ነገርኩት አለች ። ያለሽ ነገር አለን አሉዋት አው የቤትህን መቃን ቀይር በይው ብሎኛል አለች ። እሱ አባቴ ነው የቤቴ መቃን አንቺ ነሽ ፍታት ብሎኛል ወደ ቤተሰቦችሽ ሂጂ አሏት ( ፈቱዋት) ። ነብዩላሂ ኢስማኢል ሌላ የአንድ ምስኪን ልጅ አገቡ በጣም አላህን የምትፈራ ባለው የምትብቃቃ ለባልዋ ታዛዥ ነበረች ። ነብዩላሂ ኢስማኢል በደስታ ወደ አላህ መገዛት እየተጣሩ መኖር ጀመሩ ። አንድ ቀን እንደ ልማዳቸው ወደ አደን ሄዱ ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ቤተሰባቸውን ለማየት መጡ ። ልጃቸው የለም ። ሁለተኛዋን ሚስት አገኙዋት ። እንግዳ ትወዳላችሁ ወይ ? ለእንግዳስ የምታቀርቡት ነገር አለ ወይ ብለው ሰላምታ አቅርበው ገቡ ። ሚስትየውም አልሐምዱ ሊላህ ምን ጠፍቶ ሁሉ ነገር አለ ግቡ አለች ። ነብዩላሂ ኢብራሂምም በሁኔታዋና መልሷ በጣም ተደሰቱ ። ምግባችሁ ምንድነው አሏት ስጋ አለቻቸው ። መጠጣችሁስ ምንድነው አሏት ውሀ ( የዘምዘም ውሀ ) አለች ። ዱዓእ አደረጉላቸው ። ባለቤትሽ ሲመጣ የቤትህን መቃን አጥብቀው ጥሩ መቃን ነው በይው ብለዋት ወደ ሻም ተመለሱ ። አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka

ዳዕዋ ዳዕዋ ዳዕዋ 📢 ‼️ አስላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድና የተከበራችሁ የሱና እአህቶችና ወንድሞች በያላችሁበት ቦታ ሁናችሁ ያአላህ እዝነቱና በረከቱ አይለየን አይለያችሁ በሱናም ላይ አላህ ያፅናን ያፅናችሁ እንኳን ለ (1445) ኢደል አድሃ በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ እነሆ አስደሳች ዜና ይዘን ዘልቀናል የፊታችን እሁድ ማለትም ሰኔ ቀን /16/2016/ታላቅ የዳዕዋ ዝግጅት ስላለን በተባለው ቦታ በጧት በመገኝት የዳዕዋው ተቋዳሽ ትሆኑ ዘንድ ታድማችኋል 🔄ብርቅየ ተጋባዥ እንግዶቻችነን ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው ↘️1 ሸይኽ ሙሐመድ ሃያት ከሃራ ↘️2 ሸይኽ ሁሴን ከረም     ከሃራ ↘️3 ሸይኽ ሙሃመድ ሲራጅ ከሃሮ ↘️4 ሸይኽ ሁሴን አባስ  ከጉራ    ወርቄ ↘️5 ኡስታዝ ኑራድስ           ከሃራ ↘️6 ኡስታዝ ኑረድን            ከመርሳ ↘️7 ኡስታዝ አብዱረህማን  ከመርሳ የሚጠቀሱትና የሚዳሰሱት እርዕሶች በሰአቱ በቦታው ላይ የሚነገሩ ሲሆን ጥሪውን አስታውሱ እንዳትረሱ 👁‍🗨የዳዕዋው ባታ አጆሜዳ ሲሆን ከጃራ ከፍ ያለች ከድሌሮቃ ዝቅ ብላ የምትገኝ የገጠር አድስ ከተማ ናት  ወረዳ ሃብሩ ቀበሌ ( 024) በድጋሜ አጆ ሜዳ 🕑 የሚጀመርበት ሰአት ከጧቱ ሁለት 2:00 ሰአት ጀምሮ እስከ 10:00 ሰአት ድረስ የዘልቃል የኦናይን ስርጭትም ስለሚኖረን ሳትርቁ ጠብቁን 🕌 መስጅደ ፉርቃን አጆ ሜዳ ሰኔ/ቀን/16/2016/1445/ዓ/ሂ https://t.me/hussenhas

🔶አዲስ የአቂዳ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ مـن أصـول عقيـدة أهـل السنـة والجمـاعة ➡️ ሚንኡሱሊ አቂደቲ አህሊሱነቲ ወልጀማአህ! 📝تأليف፡- الشيـخ صالـح بـن فـوزان بـن عبـد اللَّـه الفـوزان ▶"ደርስ ቁጥር 9⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2834 ⤵ክፍል ዘጠኝን ለማግኘት↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/3021 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

🔷  ውድ የሱና ቤተሰቦቻችን አላህ እንኳን ለዒደል አድሓ በሰላም አደረሳችሁ تقبل الله منا ومنكم አላህ ዒዱ የሰላም የፍቅርና የአላህን ውዴታና እዝንት የሚያስገኝ ያድርግልን ።    የዘንድሮ ዒድ ከሌላ ጌዜ ለየት ባለ መልኩ የሚዘረፍበት ነውና እንጠቀምበት ። ብዙ ወንድምና እህቶች በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ያሉበት ነው ። ከሞቀ ቤታቸው ከተረጋጋ ህይወታቸው አላህ ለሒክማው በፈለገው ነገር ሜዳ ላይ ወድቀው ህፃናቶቻቸውን ይዘው የሰው እጅ እያዩ ነው ። የዚህ አይነት ፈተና ይገጥመናል ብለው አስበውት በማያውቁት ፈተና ውስጥ ናቸው ። በርግጥ ሶብር ካደረጉ መጨረሻው ያመረ መሆኑ ጥርጥር የለውም ።     እናስታውሳቸው አብሽር እንበላቸው ሐዘናቸውን እናስረሳቸው ። ዒዱ የደስታ እንዲሆንላቸው እንድረስላቸው እንዘይራቸው ። የዱንያ ህይወት ፈተና አያጣውምና የኛም ሁኔታ አይታወቅም ስለዚህ የዛሬ መልካም ስራችን ለነገ ስንቃችን ነውና እንሰንቅ ። https://t.me/bahruteka

🔷 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል አምስት ሃጀር የህፃኗ ረሀብና ለቅሶ ረፍት ነሳት ረሀቡ በህፃኑ ላይ እየበረታ ሄደ ለቅሶዉም እየጨመረ ሄደ ። እናት የልጇን ስቃይ ማየት አቃታት ተነስታ ቆማ ታማትር ጀመር ። የሶፋ ኮረብታ ቅርብ ሆኖ አየችው ወደዛ ሄደች ኮረብታው ላይ ወጥታ ግራና ቀኝ ማማተር ጀመረች ። ምናልባት ከሩቅ የሚታይ ነገር ቢኖር ብላ ምንም የለም ። ከሶፋ 30 መቶ ሜትር አካባቢ ርቆ የመርዋ ኮረብታ ታያት ። ወርዳ ወደዛ አመራች የተወሰነ ቦታ በሶምሶማ ሄደች መቀጠል ግን አልቻለችም ቀስ ብላ ደረሰች። ወደ ኮረብታው ወጥታ ማማተር ጀመረች ። ምንም ነገር የለም ጭንቀቷ ጨመረ ወደ ህፃኑ ዞር ብላ ስታይ ጩኸቱ በድካም ቀንሶ በጣረ ሞት በእግሩ መሬት እየመታ አየችው ። ምድሩ ጠበባት እየሆነ ያለው ነገር እውነት አልመስልሽ አላት ። ወደ ሶፋ ሄዳ እንደመጀመሪያ አደረገች ። ወረደች ወደ መርዋ ሄደች እዛም እንደተለመደው አደረገች ። በዚህ መልኩ በሶፋና በመርዋ 7 ጊዜ ተዘዋወረች ። መርዋ ላይ ሆኗ ስታማትር የሆነ ድምፅ ሰማች ለራሷ እስኪ ዝም በይ አለች ። አሁንም ድምፅ ሰማች ሲሞት ላለማየት ወደ ህፃኗ ማየት አትፈልግም ነበረ ። ድምፁ በልጇ አቅጣጫ ነበር ማሰማቱስ አሰማህ የምትረዳው ነገር ካለህ አለች ። ዞር ስትል ጅብሪል በክንፉ ከልጇ እግር ስር ሲመታ አየች ወዲያ ምንጭ ፈለቀ ። የሞት ሞቷ ደረሰች ምንጩን ሁለት እጆቿን ዘርግታ ዘም ዘም ( እትሂድ አትሂድ ) እያለች ትከበው ጀመር ስሙም ዘምዘም ተባለ ። ጠጣች ልጇንም አጠባች ። እሷም ልጇም በሚገርም ሁኔታ ሀይል አገኙ ። አላህ በዚህ መልኩ የሀጀርን አላህ ከሆነ ያዘዘህ አይጥለንም ያለችበትን ተወኩል እውን አደረገው ። ከየመን ወደ ሻም የሚሄዱ ነጋዴዎች አሞራ ሲያንዣብብ ተመለከቱ ። እስከዛሬ ድረስ በዚህ ስናልፍ አሞራ ሲያንዣብብ አይተን አናውቅም አንድ የተከሰተ ነገር ቢኖር ነው አሞራ የሚያንዣብበው ውሀ ባለበት አካባቢ ነውና እስኪ ሄዳችሁ እዩ ተብሎ ሁለት ሰዎች ተላኩ ። ሰዎቹም ሃጀርና ህፃኗ ውሀ አጠገብ ሆነው አዩ ተመልሰው ያዩትን ተናገሩ ። ሃጀርን ከሷ ጋር ለመኖር ትፈቅድላቸው እንደሆነ ጠየቋት እሷም ከውሀው መብት የላችሁም እኔ ነኝ ባለቤቱ መቀመጥ ትችላላችሁ አለቻቸው ። ጁርሁም የሚባሉት የየመን ሰዎች ቤተሰቦቻቸውን ይዘው መጥተው ከሃጀር ጋር መኖር ጀመሩ ። እነርሱ የምትፈልገውን ነገር እያቀረቡ እሷ ከዘምዘም ውሀ ትሰጣቸዋለች ። በዚህ መልኩ መካ ተቆረቆረች ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ዘንድ 3 እንግዶች መጡ መልካቸው በጣም አስገራሚ ነበር ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ከኔ በስተቀር ማንም አያስተናግዳቸውም አሉ ። ራሳቸው ምግብ ሰሩላቸው አቀረቡ ነገር ግን አይበሉም ። ይህን ታሪክ አላህ በዛሪያት ምእራፍ ከ24 – 28 አንቀፅ እንዲ ብሎ ይነግረናል : – هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ ضَيْفِ إِبْرَاهِيمَ الْمُكْرَمِينَ የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? إِذْ دَخَلُوا عَلَيْهِ فَقَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ قَوْمٌ مُّنكَرُونَ በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ) ፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው ፡፡ فَرَاغَ إِلَىٰ أَهْلِهِ فَجَاءَ بِعِجْلٍ سَمِينٍ ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ ፡፡ فَقَرَّبَهُ إِلَيْهِمْ قَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው ፡፡ فَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۖ قَالُوا لَا تَخَفْ ۖ وَبَشَّرُوهُ بِغُلَامٍ عَلِيمٍ ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ ፡፡ «አትፍራ» አሉት ፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት ፡፡ ነብዩላሂ ኢብራሂም ቤተሰባቸውን ለማየት ከሻም ወደ መካ መጡ ። ልጃቸውን ኢስማኢልን ሲያዩ ከሚጠብቁት በላይ ተደሰቱ ። ኢስማኢል ወደ 14 አመታቸው አካባቢ ሆኗል ። ለአላህ የሰጡት አደራ በሚገርም ሁኔታ ተጠብቋል ። የልጃቸው እድገትና ሁኔታ ትልቅ ደስታ ፈጥሮባቸዋል ። ፍቅሩ በውስጣቸው ገባ አላህ ነብዩላሂ ኢብራሂም ከአላህ ውጪ የሌላ ነገር ፍቅር ውስጣቸው እንዲገባ አይፈቅድም ። ነብዩላሂ ኢብራሂም በመናማቸው ኢስማኢልን ሲያርዱት አዩ የነብያት መናም እውነት ነውና ለኢስማኢል ነገሩት ኢስማኢልም አባቴ ሆይ የታዘዝከውን ፈፅም ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ አላቸው ። ነብዩላሂ ኢብራሂምም ኢስማኢልን ይዘው ወደ ማረጃው ቦታ ማምራት ጀመሩ ። መንገድ ላይ ሸይጣን ኢስማኢልን አባትህ መናም ማየቱን እንዴት አመንክ እያለ ይወሰውስ ጀመር ። ኢስማኢልም ጠጠር አንስተው በሸይጣን ላይ ይወረውሩ ጀመር ። እናቱ ጋር ሄዶ መወትወት ጀመረ ። ተመሳሳይ ነገር ገጠመው ። ቦታው ላይ ሲደርሱ ነብዩላሂ ኢብራሂም ኢስማኢልን ሊያርዱዋቸው አስተኙዋቸው ። የነብዩላሂ ኢብራሂም ሁኔታ ያየው ኢስማኢል በፊት ለፊቴ አስተኛኝና በማጅራቴ በኩል እረደኝ አላቸው ይላሉ አንዳንድ ዘገባዎች ። አስተኝተው ሊያርዱት ሲሉ ጅብሪል ሙክት ይዞ መጥቶ በኢብራሂም ፈንታ ይህን እረድ አላቸው ። አላህ የፈለገው የኢስማኢል መታረድ ሳይሆን አባትና ልጅ ለአላህ ትእዛዝ ያላቸውን ቦታ ማሳየት ነበርና ታይቷል ። ይህን ክስተት ቁርኣን በሷፋት ምእራፍ ከ102 – 107 ድረስ ይነግረናል : – فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ السَّعْيَ قَالَ يَا بُنَيَّ إِنِّي أَرَىٰ فِي الْمَنَامِ أَنِّي أَذْبَحُكَ فَانظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَا أَبَتِ افْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِي إِن شَاءَ اللَّهُ مِنَ الصَّابِرِينَ ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ ፡፡ فَلَمَّا أَسْلَمَا وَتَلَّهُ لِلْجَبِينِ ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ) ። وَنَادَيْنَاهُ أَن يَا إِبْرَاهِيمُ ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ! قَدْ صَدَّقْتَ الرُّؤْيَا ۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْبَلَاءُ الْمُبِينُ ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው ፡፡ وَفَدَيْنَاهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው ፡፡ የነብዩላሂ ኢብራሂም የሃጀርና ኢስማኢል ታሪክ በአብዛኛው ከሀጅ ስራ ጋር ይገናኛል ። በየአመቱ ዒደል አድሓ ቀን የሚታረደው እርድም ይህን ታላቅ ክስተት ለማስታወስ ነው ። አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka

ያኣዩሃል ኢኽዋኒ እናንተ በፍልስጤናዊያን ደም ነጋዴዎች ያኣዩሃል ሙብተዲዕ  አያችሁዎይ!? ለፍልስጤናዊያን በሚሊዎን የሚቆጠሩ የኣለም ህዝቦች የኣረፋ ሁጥባ ላይ ዱኣ ሲያደርጉ ና ሰላምን ሲለምኑ ተመለከታችሁ!? #አቅሷ ሁሌም በልባችን አንረሳትም 🤲 اللهم استجب

በዱኣ እንበርታ🌅 لا اله إلا الله وحده لا شريك له له الملك وله الحمد وهو على كل شيء قدير
በዱኣ እንበርታ🌅 لا اله إلا الله وحده لا شريك له له الملك وله الحمد وهو على كل شيء قدير

የአረፋ ቀን ዱዓእ! ረሱል (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿خيرُ الدُّعاءِ دعاءُ يومِ عرفةَ، وخيرُ ما قلتُ أنا والنَّبيُّونَ من قبلي: ل
የአረፋ ቀን ዱዓእ! ረሱል (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿خيرُ الدُّعاءِ دعاءُ يومِ عرفةَ، وخيرُ ما قلتُ أنا والنَّبيُّونَ من قبلي: لا إلَهَ إلّا اللهُ وحدَهُ لا شريكَ لَهُ، لَهُ الملكُ ولَهُ الحمدُ وهوَ على كلِّ شَيءٍ قديرٌ.﴾ “ምርጡ ዱዓእ የዓረፋ ቀን የሚደረገው ዱዓእ ነው። እኔም ሆንኩ ከኔ በስተፊት የነበሩት ነቢያት ከተናገሩት ቃል መካከል በላጩም፦ ‘ከአላህ በስተቀር በሀቅ ሊመለክ የሚገባው አምላክ የለም። እሱ ብቸኛ ነው። አጋር የለውም። ንግስናም ለሱ ነው። ምስጋናም የሚገባው ለሱ ነው። እሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነውና።’ የሚለው ቃል ነው።” 📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 3274 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

التّكبير تعظيم لله عز وجل
‏الله أكبــر، الله أكبــر ، لا إله إلا الله الله أكبــر، الله أكبــر  ، ولله الحمد 🎙الشيخ محمد بن رمزان الهاجري -حفظه الله 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

🔶አዲስ የአቂዳ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ مـن أصـول عقيـدة أهـل السنـة والجمـاعة ➡️ ሚንኡሱሊ አቂደቲ አህሊሱነቲ ወልጀማአህ! 📝تأليف፡- الشيـخ صالـح بـن فـوزان بـن عبـد اللَّـه الفـوزان ▶"ደርስ ቁጥር 9⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2834 ⤵ክፍል ስምንትን ለማግኘት↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2995 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

👉 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ነብዩላሂ ኢብራሂም እሳት ውስጥ አላህን እያወሱና ለሱ እየሰገዱ ምንም ሳይሰማቸው ቆዩ ። አላህ መላኢካ ልኩ ያበስራቸው ነበር ። እሳቱ ሲያቆም ነምሩድ የሆነውን ለማየት ወጣ ። ያየውን ማመን አቃተው ቆመው እየሰገዱ ነበር ያ ኢብራሂም ብሎ ተጣራ እሳቸውም ከሶላታቸው ሲወጡ መልስ ሰጡት ። ከዚህ እሳት እንዴት ዳንክ አላቸው የኔና ያንተ ጌታ አላህ አዳነኝ አሉት ። ለጌታህ ቁርባን አቀርባለሁ አላቸው እሳቸውም አላህ የከሀዲያንን ቁርባን አይቀበልም አሉት ። ከዚህ መዕጂዛ በኋላ የነምሩድ ህዝቦች ነብዩላሂ ኢብራሂምን የበለጠ ማሰቃየት ጀመሩ ። ድግምተኛ ነውም አሉ ። በዚህን ጊዜ የአጎታቸው ልጅ ሳራና የወንድማቸው ልጅ ሉጥ ተከተሉዋቸው ዳዕዋቸውን ተቀበሉ ። ሳራንም አገቡዋት ። አላህ ዒራቅን ትተው እንዲወጡ አዘዛቸው ሳራንና ሉጥን አስከትለው ከዒራቅ ምድር ወጡ ። ዳዕዋ እያደረጉ ከዒራቅ ወደ ከንዓን ( ፍልስጢን) ወደ ሻም ከዛም ወደ ግብፅ ምድር አመሩ ። የግብፅ ምድር ሲደርሱ ዱንኳን ወጥረው አረፉ ። ስለ ሳራ ቁንጅና ተሰራጨ ። ንጉሱም ወታደሮቹን ልኮ ሳራን ከነብዩላሂ ኢብራሂም ነጥሎ ወደ ቤተመንግስት አስወሰዳት ። ሊቀርባትም ከጀለ ዱዓእ ታደርግ ጀመር ። ሆዱ ላይ ህመም ተሰማው ተዋት ። ጌታሽን ለምኝልኝ አልነካሽም አላት ። ዱዓእ አደረገችለት ተሻለው ። መልሶ ከጀላት ። አሁንም ዱዓእ አደረገችበት ህመም ተሰማው ‼ ጌታሽን ለምኝልኝ አልነካሽም አላት ። ዱዓእ አደረገችለት ። አሁንም ከጀላት ዱዓኡ ቀጠለ ተመልሶ ታመመ ከዚህ በኋላ አላስብም ዱዓእ አድርጊልኝ አላት አደረገችለት ተሻለው ። ወታደሮቹን ጠርቶ ሃጀርን በስጦታ ሰጥቶ ሌላም ጨምሮ ሂዱ ወዳመጣቹበት መልሷት አለ ። ወደ ኢብራሂም ተመለሰች ። አላህ ሉጥን ነብይ አድርጎ ወደ ሶዶም ህዝቦች ላከው ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ሳራን ይዘው ወደ ሻም ተመለሱ ። ነብዩላሂ ኢብራሂም ዘር እንዲሰጣቸው አላህን ለመኑ ። ሳራ መሀን ነበረች ። ልጅ ወልዳ የባልዋን የልጅ ፍላጎት ባለሟሟላቷ ተሰማት ። የዚህን ጊዜ ነብዩላሂ ኢብራሂም ቁጭ ብለው አላህ እንዴት ነው ሙታንን ህያው የሚያደርገው ብለው ያስተነትኑ ነበር ። አላህንም ሙታንን እንዴት ህያው እንደምታደርግ አሳየኝ አሉ ። ወዲያ ጂብሪል መጥቶ አላመንክም እንዴ ብሎ ጠየቃቸው ። እሳቸውም አምኛለሁ ግን ልቤ ሊረጋጋልኝ ነው አሉ ። ይህን ሁኔታ አላህ በላሚቷ ምእራፍ 260 ኛው አንቀፅ ላይ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ أَرِنِي كَيْفَ تُحْيِي الْمَوْتَىٰ ۖ قَالَ أَوَلَمْ تُؤْمِن ۖ قَالَ بَلَىٰ وَلَٰكِن لِّيَطْمَئِنَّ قَلْبِي ۖ قَالَ فَخُذْ أَرْبَعَةً مِّنَ الطَّيْرِ فَصُرْهُنَّ إِلَيْكَ ثُمَّ اجْعَلْ عَلَىٰ كُلِّ جَبَلٍ مِّنْهُنَّ جُزْءًا ثُمَّ ادْعُهُنَّ يَأْتِينَكَ سَعْيًا ۚ وَاعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ حَكِيمٌ ኢብራሂምም «ጌታዬ ሆይ! ሙታንን እንዴት ሕያው እንደምታደርግ አሳየኝ» ባለ ጊዜ (አስታውስ፡፡) አላህ ፡- «አላመንክምን» አለው፡፡ «አይደለም (አምኛለሁ)፤ ግን ልቤ እንዲረጋ» ነው አለ፡፡ (አላህም)፡- «ከበራሪዎች (ከወፎች) አራትን ያዝ፡፡ ወደ አንተም ሰብስባቸው፡፡ (ቆራርጣቸውም)፤ ከዚያም በየኮረብታው ሁሉ ላይ ከነርሱ ቁራጭን አድርግ፡፡ ከዚያም ጥራቸው፤ ፈጥነው ይመጡሃልና፡፡ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ መኾኑን ዕወቅ» አለው ፡፡ ሳራ ለነብዩላሂ ኢብራሂም አላህ ዘር እንዲሰጣቸው ሀጀርን እንዲያገቡዋት አደረገች ። ተጋቡም ። ሃጀርም ፀነሰች ። ሀጀር እርግዝናዋን ለመደበቅ መቀነት ታስር ነበር ። መቀነት የጀመረችውም እሷ ነች ይባላል ። ሳራ መፀነስዋን ባወቀች ጊዜ የቅናት ስሜት ተሰማት እኔና እሷ አንድ ሀገር ላይ መኖር አንችልም ፊቷን ዞር አድርግልኝ አለቻቸው ። ሀጀርም ነብዩላሂ ኢስማኢልን ወለደች ። አላህ ለነብዩላሂ ኢብራሂም ሀጀርና ህፃኑን ይዘው ከሻም እንዲወጡ አዘዛቸው ። በጅብሪል ጓደኝነት ጉዞ ጀመሩ መካ በደረሱ ጊዜ ጅብሪል አሁን በሶፋ ኮረብታና በዘምዘም ጉድጓድ መሀል ላይ ባለው ቦታ እዚህ እረፉ አላቸው ። ነብዩላሂ ኢብራሂም የያዙትን ተምርና ውሃ አስቀምጠውላቸው መሄድ ጀመሩ ። ሀጀር ስታይ በቦታው እንኳን ሰው እንሰሳም ይሁን አእዋፍት የለም ። ድንጋይና አሸዋ ብቻ ነው ያለው ። እልም ያለ በረሀ ነው ሙቀቱ ከሚገመተው በላይ ነው ። ሃጀር ያ ኢብራሂም እያለች ተጣራች ዝም አሉ ደጋግማ ተጣራች ዝም አሉ ወደፊት እየሄዱ ነው ። ድምፇን ከፍ አድርጋ አላህ ነው እንዴ ያዘዘህ አለቻቸው አው አሏት ። እንግዲያውስ አላህ አይጥለንም አለቻቸው ። ነብዩላሂ ኢብራሂም የአላህን ትእዛዝ ለሞምላት ውስጣቸው እየተረበሸ ከእይታዋ ተሰወሩ ። ከዛም የሚከተለውን ዱዓእ አደረጉ : – رَّبَّنَا إِنِّي أَسْكَنتُ مِن ذُرِّيَّتِي بِوَادٍ غَيْرِ ذِي زَرْعٍ عِندَ بَيْتِكَ الْمُحَرَّمِ رَبَّنَا لِيُقِيمُوا الصَّلَاةَ فَاجْعَلْ أَفْئِدَةً مِّنَ النَّاسِ تَهْوِي إِلَيْهِمْ وَارْزُقْهُم مِّنَ الثَّمَرَاتِ لَعَلَّهُمْ يَشْكُرُونَ إبراهيم ( 37 ) «ጌታችን ሆይ! እኔ አዝመራ በሌለው ሸለቆ ውስጥ በተከበረው ቤት (በካዕባ) አጠገብ ከዘሮቼ አስቀመጥኩ ፡፡ ጌታችን ሆይ! ሶላትን ያቋቁሙ ዘንድ (አስቀመጥኳቸው) ፡፡ ከሰዎችም ልቦችን ወደእነሱ የሚናፍቁ አድርግ ፡፡ ያመሰግኑህም ዘንድ ከፍሬዎች ስጣቸው ፡፡ ሃጀር ተምሩን እየበላች ከውሀው እየጠጣች ልጇን ማጥባት ጀመረች ። ነገር ግን ተምሩም ውሀውም አለቀ ። ህፃኑ በረሀብ ማልቀስ ጀመረ ። አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በኡስታዝ አቡ አብዱረህማን አልመርሲይ የሚቀሩ ደርሶችን በእህቶች መቅራት የምትፈልጉ ኑ በዚህ ⚠ እህቶች ብቻ⬇⬇ ድምፃችሁን ለማወቅ ሲባል🎤እያደረጋችሁ @Umu_Abdirehman 🔴ገብቶ ለማየት ሳይሆን ለመቅራት ጉጉት ያላችሁ ብቻ‼ የማይቀራ ሪሙቭ ይደረጋል። ⏺በመቀጠል ክፍያ የለውም ።

ኡስታዙና አላህ ይጠብቃቼው ሃሉን በደንብ ገልፀውታል جزاها الله كل خير ውድ እህቶች የዋህነት አታብዙ ሁሉም ነገር ልክና መልክ አለው ካልሆነ የዋህነት ሲበዛ ጅልነት ነው ከሰዎች በምታዩት ነገር ትምህርት ውሰዱ በግድ እኔ ላይ ካልደረሰ አልማርም አትበሉ ብልጥ ሴት ከሌሎች አይታ ነው የምትማረው ወንድሞችም የአረብ ሀገር ሴት ብሩን እንዴት እንደምታገኘው ብታውቁ ኖሮ ይህን ፀያፍ ድርጊት አትፈፅሙም ነበር ይልቁንስ ታዝኑላት ነበር አዕምሮህ ማገናዘብ ቢችል አይደለም ከሷ ተቀብለህ ልትቅምበት፣ልታጨስበት ይቅርና  ልትበላበት እንዲሁም ታመምኩ ይሄን ሆንኩ እያልክ ሰበብ ፈልገህ ልታስላካት ይቅርና በሩቁ ትፀየፈው ነበር። ይች የአረብ ሀገር ሴት በጠለብም ይሁን በኢቃማ  በባህር ሊሆን ይችላል ከሀገሯ ተሰዳ ስትመጣ በማታውቀው ቋንቋ ተቀብለው አገሯ ሳለች 2/3 ሰዎች ናቼው ተብላ የመጣች ሴት 11  ሆነው ታገኛቸዋለች!ከናቷ ቤት እናቷ የሰራችውን እየበላች፣ እናቷ የቀዳችውን ውሀ እየጠጣች፣ እናቷ ያጠበችላትን ልብስ እየለበሰች የኖረች ልጅ በማታውቀው ቋንቋ ስራውን ሁሉ ያስረክቧታል! ስራ ቢሉህ ስራ እንዳይመስልህ በጠረንቤዛ ላይ እግሯን አጣምራ ተቀምጣ የምሰራው ስራ አይደለም!ምን አይነት ስራ እንደምትሰራና በምን መልኩ ይህን ገንዘብ እንደምታገኝ በትንሹ ልንገርህ ቀን በቀን ውሎዋ ከምታከናውነው ድርጊቷ በጧት ተነስታ ፅዳት ትጀምራለች ፅዳት ስለህ ቤት አፅድታ የምትቀመጥ እንዳይመስልህ ጅፕላስ ቤቶች ፎቅና እምድር ይሁን ምድር ቤት ከነ ግርግዳው ፣ከነ መስኮቱ… …………………… እስከ ወለሉ ታፀዳለች!ሁሉንም ክላስ 10ም ይሁን ከዛ በላይ / በታች ይሁን እንዲህ በእንዲህ እያረገች ታፀዳለች! ከዛ የልብስ ዱላብ ቁምሳጥኖችን  ትረትባለች ህፃናት ካሉማ እሷ እየረተበች እነሱ እየናዱ ያደክሟታል እንዲህ ቀን በቀን ትረትባለች! ሀማሞችን /ሽንት ቤቶችን በየቀኑ ቢያንስ ሁለቴ ታጥባለች!! እሄን አፀዳሁ ጨረስኩ ስትል የምታርፋ መስሎሀል! መጥባህ /ኩሽና ቤት ትገባለች ምግብ ታበስላች የምግብ እቃወችን ታጥባለች ዱላቦቹን/የእቃ መደርደሪያወቹን እቃ እያወጣች ታፀዳለች! ይሄን ጨረስኩ ስትል ልብስ ማጠብ  መተኮስ ይጠብቃታል! የሰዎቹን አፍ አትጠይቅ ለደቂቃኳን ዝም አይሉምዴ ነው የሚያስብሉት ታዓሊ ወዲ ጂቢ  ሰውይ……………የቀራቸውን ጠለባት በዚህ ያካሂዳሉ! ታዳ ይች ሴት ደከመኝ ልረፍ  እንቅልፌ መጣ ልተኛ ሳትል ቆማ ውላ ቆማ ታመሻለች! በሰዓታት የሚቆጠሩ ከ4 _5ሰዓት ጎኗን ታሳርፋለች!  ይህ ሁሉ ታዳ የአንድ ቀን ብቻ ሳይሆን ሁሉም ቀን ተመሳሳይ የምታከናውነው ተግባሯ ነው!! እንድህ እየሆነች ለአንተ ና ለቤተሰቦቿ እንዳሰጉ በማለት ደህናነኝ ሰዎቹም ጥሩ ሰዎች  ናቸው ተመችቶኛል… ………… ትላለች እና ይች ሴት አታሳዝንም ??? አዕምሮ ያለው ሰው በትንሹም ቢሆን ያዝናል እዘንላት  አክብራት ውደዳት  ገንዘቧን አልባሌ ቦታላይ አታጥፋባት…። https://t.me/deawetu_selefiyya_Merssa

🔷 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል ሶስት ነብዩላሂ ኢብራሂም ዳዕዋቸውን ከንግግር ወደ ተግባር ለመቀየር ወሰኑ ። ለጣኦት አምላኪያን የሚያመልኩዋቸው ጣኦታት ያልተገዛቸውን መጎዳትም ሆነ የተገዛቸውን መጥቀም እንደማይችሉ ከዚህም በላይ ራሳቸውንም ከጥቃት የማይከላከሉ መሆናቸውን ማሳየት እንዳለባቸው አመኑ ። የባአላቸው ቀን ጠብቀው ሁሉም ተሰባስበው ወደ በአሉ ሲሄዱ ነብዩላሂ ኢብራሂም መጥረጢያቸውን ተሸክመው ወደ ጣኦቶቻቸው አመሩ ። የተለያየ ስለት እንዲሁም ምግብም አጠገባቸው ተቀምጦ አዩ ‼ አትበሉም እንዴ እያሉ ያናግሯቸው ጀመር መልስ የለም ። ትልቁን ብቻ አስቀርተው ጣኦታቱን ፈላልጠው ጨረሱ ። ከዛም መጠረቢያውን በትልቁ ጣኦት ላይ አስቀምጠው ጥለው ሄዱ ። ጣኦትአምላኪያኖቹ ከባአል ማክበሪያ ሲመለሱ በጣኦቶቻቸው ላይ የተሰራውን ጉድ አዩ ። ስለጣኦቶቻቸው ደካማነትና ስለራሳቸው ዐቅለቢስነት ከማሰብ ይልቅ በአማልክቶቻችን ላይ ማነው ይህን የሰራው እያሉ መጠያየቅ ጀመሩ ። ኢብራሂም የሚባል ነው ተባለ ፈልገው ጠየቋቸው ። እሷቸውም ትልቁን ጠይቁት የሚናገር ከሆነ ብለው መለሱ ። ይህን ክስተት ቁርኣን በሚቀጥለው የአል ንቢያ ምእራፍ ከ59 – 67 በዝርዝር ያስቀምጥልናል : – قَالُوا مَن فَعَلَ هَٰذَا بِآلِهَتِنَا إِنَّهُ لَمِنَ الظَّالِمِينَ «በአማልክቶቻችን ይህንን የሠራ ማነው እርሱ በእርግጥ ከበደለኞች ነው» አሉ፡፡ قَالُوا سَمِعْنَا فَتًى يَذْكُرُهُمْ يُقَالُ لَهُ إِبْرَاهِيمُ «ኢብራሂም የሚባል ጎበዝ (በመጥፎ) ሲያነሳቸው ሰምተናል» ተባባሉ፡፡ قَالُوا فَأْتُوا بِهِ عَلَىٰ أَعْيُنِ النَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَشْهَدُونَ «ይመሰክሩበት ዘንድ በሰዎቹ ዓይን (ፊት) ላይ አምጡት» አሉ፡፡ قَالُوا أَأَنتَ فَعَلْتَ هَٰذَا بِآلِهَتِنَا يَا إِبْرَاهِيمُ «ኢብራሂም ሆይ! በአማልክቶቻችን ይህንን የሠራህ አንተ ነህን» አሉት፡፡ قَالَ بَلْ فَعَلَهُ كَبِيرُهُمْ هَٰذَا فَاسْأَلُوهُمْ إِن كَانُوا يَنطِقُونَ «አይደለም ይህ ታላቃቸው ሠራው፡፡ ይናገሩም እንደ ኾነ ጠይቋቸው» አለ፡፡ فَرَجَعُوا إِلَىٰ أَنفُسِهِمْ فَقَالُوا إِنَّكُمْ أَنتُمُ الظَّالِمُونَ ወደ ነፍሶቻቸውም ተመለሱ፡፡ «እናንተ (በመጠየቃችሁ) በዳዮቹ እናንተው ናችሁም» ተባባሉ፡፡ ثُمَّ نُكِسُوا عَلَىٰ رُءُوسِهِمْ لَقَدْ عَلِمْتَ مَا هَٰؤُلَاءِ يَنطِقُونَ ከዚያም በራሶቻቸው ላይ ተገለበጡ፡፡ «እነዚህ የሚናገሩ አለመኾናቸውን በእርግጥ ዐውቀሃል፤» (አሉ)፡፡ የዚህን ጊዜ ጥሩ መግቢያ አገኙ ። ጠንከር ባለ ሁኔታ ዳዕዋ አደረጉላቸው ። ይህንንም ቁርኣን በዛው ምእራፍ በሚቀጥሉት አንቀፆች ላይ ይነግረናል :– قَالَ أَفَتَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَنفَعُكُمْ شَيْئًا وَلَا يَضُرُّكُمْ «ታዲያ ለእናንተ ምንም የማይጠቅማችሁንና የማይጎዳችሁን ነገር ከአላህ ሌላ ትገዛላችሁን» አላቸው፡፡ أُفٍّ لَّكُمْ وَلِمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ أَفَلَا تَعْقِلُونَ «ፎህ! ለእናንተ ከአላህ ሌላ ለምትገዙትም ነገር፤ አታውቁምን» (አለ)፡፡ ጣኦት አምላኪያኑም በመረጃ ሲሸነፉ ሐቅን ከመቀበል ይልቅ ወደ ሀይል ተሸጋገሩ ። ይህ የሁሉም የባጢል ተከታዮች ባህርይ ነው ። መረጃ ሲያጡ ጡንቻን መረጃ ያደርጋሉ ‼ ። ኢብራሂምንም አቃጥሉ ጣኦቶቻችሁንም እርዱ አሉ ። ይህም እውነታ ቁርኣ በሚቀጥለው አንቀፅ ያስቀምጠዋል : – قَالُوا حَرِّقُوهُ وَانصُرُوا آلِهَتَكُمْ إِن كُنتُمْ فَاعِلِينَ «ሠሪዎች እንደ ኾናችሁ አቃጥሉት፡፡ አማልክቶቻችሁንም እርዱ» አሉ፡፡ (በእሳት ላይ ጣሉትም)፡፡ ዐቅለ ቢሶቹም ነብዩላሂ ኢብራሂምን ለማቃጠል ወሰኑ ። ጥፋታቸው ጣኦታትን ራቁ አላህን ብቻ ተገዙ ማለታቸው ነው ። በወቅቱ የነበረው መንግስት ግንብ ገንቡና እሳት አቀጣጥላችሁ እዛ ውስጥ ጣሉት ብሎ አዘዘ ። ይህን ክስተት ቁርኣን እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – قَالُوا ابْنُوا لَهُ بُنْيَانًا فَأَلْقُوهُ فِي الْجَحِيمِ «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ ፡፡ በመንግስት ትእዛዝ ከፍታው 30 ሜትር ጎኑ የተራራ ጫፍ የሚሆን ምሽግ ተገነባ ። ማንኛውም ህዝብ እንጨት እንዲሰበስብ ታዘዘ ። ሴት ወንድ ፣ አዋቂ ልጅ ሁሉም ወደ 40 ቀን አካባቢ ስራውን ትቶ መሰብሰብ ጀመረ ። በዚህ ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ክምር እሳት ተለኮሰበት ። ነበልባሉ ከሰማይ አሞራ ይጠልፍ ነበር ይባላል ። ጣኦት አምላኪያን ጉድ ተሰሩ ‼ ። ኢብራሂምን እንዴት በዚህ እሳት ይወርውሩ ? የሰው ሸይጣን መጥቶ ወስፈንጥር ( ምንጀኒቅ ) ዛሬ በዘመናዊ መልኩ መድፍ የሚባለው አይነት ማለት ነው እንዲሰሩና እዛ ላይ አድርገው እንዲወረውሩዋቸው ሐሳብ አቀረበ ። እንደተባሉት አደረጉ ። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ጅብሪል መጣ ምን ትፈልጋለህ አላቸው ? ነብዩላሂ ኢብራሂምም ካንተ ምንም አልፈልግም ። አላህ በቂዬ ነው ምን ያማረ መጠጊያ ነው አሉ ። ወዲያውም የአላህ እርዳታ መጣ ። አላህ እሳትን አናገረ ። ይንንም ቁርኣን እንዲህ ብሎ አረጋገጠው : – قُلْنَا يَا نَارُ كُونِي بَرْدًا وَسَلَامًا عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ الأنبياء ( 69 ) «እሳት ሆይ! በኢብራሂም ላይ ቀዝቃዛ፤ ሰላምም ሁኚ» አልን፡፡ فَأَرَادُوا بِهِ كَيْدًا فَجَعَلْنَاهُمُ الْأَسْفَلِينَ الصافات ( 98 ) በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው ፡፡ አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka

🔶አዲስ የተውሂድ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ : كتاب التوحيد الذي هو حق الله على العبيد ➡️ ኪታቡ ተውሒድ 📝تأليف፡-لشيخ الإسلام المجدد محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ▶"ደርስ ቁጥር 7⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2921 ⤵ክፍል ስድስትን ለማግኘት↘↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/3010 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

🔶አዲስ የተውሂድ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ : كتاب التوحيد الذي هو حق الله على العبيد ➡️ ኪታቡ ተውሒድ 📝تأليف፡-لشيخ الإسلام المجدد محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ▶"ደርስ ቁጥር 6⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2921 ⤵ክፍል አምስትን ለማግኘት↘↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/3005 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

👉 የነብዩላሂ ኢብራሂም ታሪክ ክፍል ሁለት ነብዩላሂ ኢብራሂም አላህ ለትእዛዙ እጅ እንዲሰጡ ካዘዛቸው በኋላ ፍፁም ታዛዥነታቸውን ገልፀው ዳዕዋ ጀመሩ ። ማህበረሰባቸው አላህን አያውቅም ። ቤተሰቦቻቸው ጣኦት ያመልካሉ ያለባቸው ሀላፊነት ክብደት እረፍት አልሰጣቸውም ። ወደ አላህ መንገድ የመጣራቱን ሂደት ከጣኦት ቸርቻሪው አባታቸው መጀመር እንዳለባቸው ወሰኑ ። ወደ አባታቸውም ሄደው አባቴ ሆይ አላህ ሰዎች እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ልጣራ አዞኛል ። ዳዕዋዬን ካንተ መጀመር መረጥኩኝ እነዚህ የማይጠቅሙና የማይጎዱ የማይሰሙና የማያዩ ጣኦታትን ትተህ አላህን ብቻ ተገዛ እያሉ ወደ አላህ አምልኮት መጣራታቸውን አላህ በሱረቱል መርየም ከ41 – 45 ድረስ በሚከተለው መልኩ ይነግረናል : – وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِبْرَاهِيمَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صِدِّيقًا نَّبِيًّا በመጽሐፉ ውስጥ ኢብራሂምንም አውሳ ፡፡ እርሱ በጣም እውነተኛ ነቢይ ነበርና ፡፡ إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ يَا أَبَتِ لِمَ تَعْبُدُ مَا لَا يَسْمَعُ وَلَا يُبْصِرُ وَلَا يُغْنِي عَنكَ شَيْئًا ለአባቱ ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አባቴ ሆይ! የማይሰማንና የማያይን ከአንተም ምንንም የማይጠቅምህን (ጣዖት) ለምን ትግገዛለህ يَا أَبَتِ إِنِّي قَدْ جَاءَنِي مِنَ الْعِلْمِ مَا لَمْ يَأْتِكَ فَاتَّبِعْنِي أَهْدِكَ صِرَاطًا سَوِيًّا «አባቴ ሆይ! እኔ ከዕውቀት ያልመጣልህ ነገር በእርግጥ መጥቶልኛልና ተከተለኝ ፡፡ ቀጥተኛውን መንገድ እመራሃለሁና ፡፡ يَا أَبَتِ لَا تَعْبُدِ الشَّيْطَانَ ۖ إِنَّ الشَّيْطَانَ كَانَ لِلرَّحْمَٰنِ عَصِيًّا «አባቴ ሆይ! ሰይጣንን አትግገዛ ፡፡ ሰይጣን ለአልረሕማን አመጸኛ ነውና ፡፡ يَا أَبَتِ إِنِّي أَخَافُ أَن يَمَسَّكَ عَذَابٌ مِّنَ الرَّحْمَٰنِ فَتَكُونَ لِلشَّيْطَانِ وَلِيًّا «አባቴ ሆይ ! እኔ ከአልረሕማን ቅጣት ሊያገኝህ ለሰይጣንም ጓደኛ ልትኾን እፈራለሁ ፡፡» ነብዩላሂ ኢብራሂ በጣም አስደናቂና አስተማሪ በሆነ መልኩ ክብር በተሞላበትና እኔ አዋቂ ነኝ የሚል የኩራት ስሜት በሌለበት የሚገርም አካሄድ አባቴ ሆይ እያሉ ላደረጉት ለዚህ ጥሪ ከአባታቸው የተቸሩት ምላሽ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነበር ። የአባታቸው ምላሽ ምን እንደነበረ አላህ ሲነግረን እዛው በሱረቱል መርየም 46ኛው አንቀፅ እንዲህ ይለናል : – قَالَ أَرَاغِبٌ أَنتَ عَنْ آلِهَتِي يَا إِبْرَاهِيمُ ۖ لَئِن لَّمْ تَنتَهِ لَأَرْجُمَنَّكَ ۖ وَاهْجُرْنِي مَلِيًّا (አባቱም) «ኢብራሂም ሆይ! አንተ አምላኮቼን ትተህ የምትዞር ነህን ባትከለከል በእርግጥ እወግርሃለሁ ፡፡ ረዥም ጊዜንም ተወኝ» አለ ፡፡ ይሁን እንጂ ነብዩላሂ ኢብራሂም በአባታቸው መልስ ተስፋ ቢቆርጡም ሳይበሳጩ የሰጡት መልስ በዛው ምእራፍ 47 ኛው አንቀፅ እንዲህ የሚል መሆኑ ተነግሮናል : – قَالَ سَلَامٌ عَلَيْكَ ۖ سَأَسْتَغْفِرُ لَكَ رَبِّي ۖ إِنَّهُ كَانَ بِي حَفِيًّا «ደህና ኹን ፡፡ ወደፊት ከጌታዬ ምሕረትን እለምንልሃለሁ ፡፡ እርሱ ለኔ በጣም ርኅሩኅ ነውና» አለ ፡፡ ነብዩላሂ ኢብራሂም ዳዕዋቸው አባታቸው ዘንድ ፍሬ ባለማፍራቱ ስሜታቸው ቢጎዳም የዳዕዋ ጉዞዋቸውን ከመቀጠል አላገዳቸውም ። በዘመኑ ወደ ነበረው ነምሩድ ወደ ሚባለው ንጉስ ሄደው ዳዕዋ ማድረግ ጀመሩ የነመምሩድ ባለሟሎች ጌታችን ነምሩድ ነው የሚል መልስ ሲሰጡ ነብዩላሂ ኢብራሂም በቆራጥነትና በአላህ ላይ በመመካት ነምሩድ ጌታ እንዳልሆነና የሁላቸውም ፈጣሪ አላህ መሆኑን አስመልክቶ ያደረጉትን ዳዕዋ አላህ ሲነግረን እንዲህ ይለናል : – قَالَ بَل رَّبُّكُمْ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ الَّذِي فَطَرَهُنَّ وَأَنَا عَلَىٰ ذَٰلِكُم مِّنَ الشَّاهِدِينَ «አይደለም ጌታችሁ የሰማያትና የምድር ጌታ ያ የፈጠራቸው ነው ፡፡ እኔም በዚህ ላይ ከመስካሪዎቹ ነኝ» አለ ፡፡ የዚህን ጊዜ ነምሩድ ጌታ መሆኑን ሞገተ ። ነብዩላሂ ኢብራሂምም አላህ ማለት ምን አይነት ጌታ እንደሆነና የነምሩድን ደካማነት ያስመሰከሩበትን መረጃ አላህ በሱረቱል በቀራ 258 ኛው አንቀፅ ላይ ይነግረናል : – أَلَمْ تَرَ إِلَى الَّذِي حَاجَّ إِبْرَاهِيمَ فِي رَبِّهِ أَنْ آتَاهُ اللَّهُ الْمُلْكَ إِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّيَ الَّذِي يُحْيِي وَيُمِيتُ قَالَ أَنَا أُحْيِي وَأُمِيتُ ۖ قَالَ إِبْرَاهِيمُ فَإِنَّ اللَّهَ يَأْتِي بِالشَّمْسِ مِنَ الْمَشْرِقِ فَأْتِ بِهَا مِنَ الْمَغْرِبِ فَبُهِتَ الَّذِي كَفَرَ ۗ وَاللَّهُ لَا يَهْدِي الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ ወደዚያ አላህ ንግሥናን ስለሰጠው ኢብራሂምን በጌታው ነገር ወደ ተከራከረው ሰው አላየህምን ኢብራሂም «ጌታዬ ያ ሕያው የሚያደርግና የሚገድል ነው» ባለ ጊዜ «እኔ ሕያው አደርጋለሁ እገድላለሁም» አለ፡፡ ኢብራሂም፡- «አላህ ፀሐይን ከምሥራቅ በኩል ያመጣል (አንተ) ከምዕራብ በኩል አምጣት» አለው ፡፡ ያም የካደው ሰው ዋለለ ፤ (መልስ አጣ) አላህም በዳዮች ሕዝቦችን አይመራም ፡፡ ነምሩድ በዚህ መልኩ ማላገጥ ሲጀምር አላህ አዋርዶት ነብዩላሂ ኢብራምን በሐቅ ላይ የበላይ አድርጎ ተአምረኛው ጌታ ያ እኔ አምላክ ነኝ ሲል የነበረውን ነምሩድ አንድ ትንኝ በአፍንጫው ገብታ እራሱን እንኳን ከመከራ ማዳን እንደማይችል በማሳየት ለዘመናት ስታሰቃየው ቆይታ በዛው ፍፃሜው እንዲሆን አደረገው ። አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka

🔶አዲስ የተውሂድ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ : كتاب التوحيد الذي هو حق الله على العبيد ➡️ ኪታቡ ተውሒድ 📝تأليف፡-لشيخ الإسلام المجدد محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ▶"ደርስ ቁጥር 5⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2921 ⤵ክፍል አራትን ለማግኘት↘↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/3001 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

🔶አዲስ የተውሂድ ኪታብ ቂርአት 📚 اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ : كتاب التوحيد الذي هو حق الله على العبيد ➡️ ኪታቡ ተውሒድ 📝تأليف፡-لشيخ الإسلام المجدد محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ▶"ደርስ ቁጥር 4⃣ 🎙أبو عبد الرحمن المرسي(حفظه الله) 📜የኪታብ 𝐏𝐝𝐟  ለማግኘት⇩⇩ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2921 ⤵ክፍል ሶስትን ለማግኘት↘↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi/2992 ሌሎች ትምህርቶችን ለማግኘት ⤵ 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi 📲⇘»https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi

አላህ ገፍላችንን አስወግዶ ከወንጀል ጠብቆ እርሱ የሚወደውን ስራ በመስራት የምናሳልፍ ያድርገን አሚን ↘↘↘↘ https://t.me/Abu_Abdirehman_Almersi