Apostolic Fellowship |ሐዋርያዊ ኅብረት|
Open in Telegram
"፤ በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት . . . ይተጉ ነበር።" (ሐዋ 2: 42) 💒 በሐዋርያት ትምህርት እና መሰረት ላይ የሆኑ 👉 ጽሁፎች ፣ ትምህርቶች 👉 የተለያዩ ስብከቶች ፣ መልዕክቶች 👉 የስነፅሁፍ ስራዎች ፣ የመጽሀፋ ጥቆማ 👉 አዳዲስ እና ቆየት ያሉ ዝማሬዎች እንዲሁም የተለያዩ ፕሮግራሞችን ያቀርባል። https://t.me/joinchat/AAAAAE6XG8VGJqIqD4slvw
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
2 454
Subscribers
+224 hours
+197 days
+11530 days
Posts Archive
የምስራች ታላቅ የወንጌል እንቅሰቃሴ ቀን የፊታችን አርብ ግንቦት 20/09/13 በአዲስ አበባ የቃሊቲ ሩሐማ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቷል በዚህ ፕሮግራም ላይ
✨የእ/ር ቃል በተለያዩ የእግዚአብሔር ሰዎች
✨የህብረት መዘምራን ግዜ
✨የግል ዝማሬን ጨምሮ የተለያዩ
ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል እርሶም የወንጌል አደራን ተቀብለው እንግዳ በመጋበዝ እንዲሁም በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት የፕሮግራሙ ተካፍይ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዘዋል።
አድራሻ: ቃሊቲ ሸገር ህንጻ በቀኝ በኩል ወደ ማምኮ ወረቀት ፋብሪካ በሚወስደው መንገድ በባቡር ሀዲዱ በኩል ወደ ውስጥ 100 ሜትር
የእግዚአብሔር ቃል | በወንድም ወሰነ ኃይሉ |
ርዕስ:- መታለል እና መሳት (ክፍል 1)
"፤ እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ። "
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2: 8)
* ከመታለል በኋላ መማረክ አለ። አንዳንድ ጊዜ ከየት እንደመጣ የማናውቀው ስሜት እና አመለካከት ሰውን ይስባል÷ያስታልም።
* አንዳንዶቻችን እንደውም የዘራነው ነገር እና ነገ ምናጭደው ነገር እንዲለያይልን ሁሉ እንፈልጋለን...ምንም ይዝራ ምን መልካሙን ለማጨድ መሞከር ማለት ነው።...በዚህም ምክንያት ብዙ ሰው ይስታል።
1. ሰው በራሱ ሃሳብ እና ስሜት ይታለላል
"፤ ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል። "
(የያዕቆብ መልእክት 1: 14)
"፤ አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና። "
(ወደ ገላትያ ሰዎች 6: 3)
*ብዙውን ጊዜ ሰዎች ያልሆኑትን ነን ብለው ያስቡና ነገር ግን ሰው የሚሰጣቸው ቦታ እነርሱ ካሰቡት ሳይጣጣምላቸው ሲቀር ግጭት ይፈጠራል።
2. ሰው በሌላ ሰው ይታለላል
."፤ እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፥ "
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4: 14)
*ሰዎች በራሳቸው ምክንያት ወይም ተንኮል ሰዎችን ያታልላሉ።
3. ሰው በሰይጣን ሊታለል ይችላል
"፤ መንፈስም መጣ፥ በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ። እኔ አታልለዋለሁ አለ። እግዚአብሔርም። በምን? አለው። "
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 18: 20)
ሰዎች በተለያዩ መንገዶች ሊታለሉ ይችላሉ
ይቀጥላል.......
© Bole hermon
@apostolicfellowship
ሰው ከዘላለም እሳት በምን ይድናል🗣
📖👉 መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።
ሐዋ 4፥12
ማቴ 1፥21 ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።
ሐዋ 10፥43 በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል።
ሐዋ 13፥26 እናንተ ወንድሞቻችን፥ የአብርሃም ዘር ልጆች ከእናንተ መካከልም እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ ለእናንተ የዚህ የመዳን ቃል ተላከ።
1ጢሞ 2፥5 ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤
ዩሐ 14፥6 ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።
ዩሐ 3፥16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
ዩሐ 10፥9 በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማርያም ያገኛል።
ሉቃ 2፥11 ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
ዩሐ 4፥42 ሴቲቱንም፦ አሁን የምናምን ስለ ቃልሽ አይደለም፥ እኛ ራሳችን ሰምተነዋልና፤ እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን ይሉአት ነበር።
ፊል 3፥20 እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤
1ኛጢሞ 1፥15 ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤
ቲቶ 2፥12-13 ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤
@apostolicfellowship
እስራት ፣የክርስቶስ ስቃይ እና ያለው አልማ፣
የሃጢያታችን ክብደት የደም ዋጋ ያስከፍላል፣ስለዚህ የክርስቶስ መሞት ለኛ ጥቅም ሆነልን ፣
+👉ሮሜ 5 (Romans)
6፤ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።
7፤ ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል።
****👉1 ጴጥሮስ 2 (1 Peter)
22፤ እርሱም ኃጢአት አላደረገም፥ ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤
23፤ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
*👉*ዕብራውያን 9
18፤ ስለዚህም ፊተኛው ኪዳን እንኳ ያለ ደም አልተመረቀም።
*👉*ዕብራውያን 10 (Hebrews)
1፤ ሕጉ ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር እውነተኛ አምሳል ሳይሆን የነገር ጥላ አለውና፥ ስለዚህም በየዓመቱ ዘወትር በሚያቀርቡት በዚያ መሥዋዕት የሚቀርቡትን ሊፈጽም ከቶ አይችልም።
በርባንን ለመፍታት ኢየሱስ መሰቀል ስላለበት ነውበሱ መሰቀል ብርሃን ተፈታ ሊያስፈታው ነበር እና ኢየሱስ የተሰቀለው
*** ለኛም ስጦታ ይሆንልን ዘንድ ተሰቃዬ፣
👉📖 ኤፌሶን 4 (
7፤ ነገር ግን እንደ ክርስቶስ ስጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን።
በስቃዬ ነፃ ስጦታ ተሰጠን
ለኛ ሲል
📖👉1 ዮሐንስ 5 (
6፤ በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፡ መንፈስ እውነት ነውና።
፣መንፈሱ ደሙ ፣ውሃ ፣የዘላለም ስጋ ውድ ስጦታ ናቸው በመከራው የተሰጠን 👐
ዮሐንስ 6 (
51፤ ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
📖👐ማቴዎስ 26 (Matthew)
26፤ ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፡— እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡ አለ።
27፤ ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፡— ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
28፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
ስጋና ደሙን ለመካፈል በስሙ የሃጢያታችን ስርዓት መጠመቅ አለብን ፣
1 ቆሮንቶስ 15
50፤ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ፡— ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
👉📖ዮሐንስ 19 (
34፤ ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
👐በመከራው በአዲስ መንገድ ደሙ ተመርቆ ተሰጠን 📖ዕብራውያን 10 (Hebrews)
19-20፤ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥
21፤ በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን ስላለን፥
22፤ ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልባችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ፤
ሌላው በመከራ የተቀቡልነው ስጦታወች ፣
የሰማያዊ ፀጋዎች እና በረከቶች እና ፈውሶች አሉ፣
📖ገላትያ 5 (
22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን 👉ፍቅር፥ ደስታ፥👉 ሰላም፥ 👉ትዕግሥት፥ ቸርነት፥👉 በጎነት፥ 👉እምነት፣
23፤ የውሃት፥ 👉ራስን መግዛት👉 ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።
👉📖ኢሳይያስ 53 (
12፤ ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።👇
በዋጋ ተገዝተናል እና እራሳችንን በመግዛትና በፅድቅ በቅድስናእንኖር ዘንድ ለእያንዳዳችን የልብ አይናችን ያብራልን ፣።አሜን
@apostolicfellowship
🚶 እውነተኛ መሆንን ራስን ማስለምድ!!!
“እውነትን ግዛ አትሽጣትም !!"
ምሳሌ 23፥23
► እኛ ሰዎች አብዛኛዎቻችን በልባችን ላይ የእውነትና የሀሰት ኪሶችን እንዳበጀን ይታየኛል። አሰፋፉም እኩል አይደለም ሰፊው ኪስ ብዙ እየተንቀሳቀስንበት ያለውን ድርጊት ስለሚገልጠው ማንም ባይነግረንም ይገባናል ...!!! የእውነትን ኪስ እንደ ምስጢር ኪስ አጥብቦ ሰፍቷታል። ምክንያቱም ቶሎ ቶሎ የሚጠቀመው ሀሰትን ስለሆነ እንደልቡ እየመዘዘ ለማውጣት እንዲመቸው .....,
► ሌላው ፍጥረት አያታልልም! የሰው ልጅ ብቻ ሀሰትና እውነትን ደባል አድርጎ ይኖራል። እስቲ እራሳችንን እንፈትሽ!!በኑሮአችን ሁሉ እውነተኞች ነን ወይስ ....???? ልባችን ቢፈተሽ አካሄዳችን ቢመዘን በሚዛን ቀለን ወይስ ከብደን እንገኝ ይሆን?? ዛሬ ለእውነት የሚፈርደው ጌታ ቢመጣ አንተ ታማኝ ባሪያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይባልልናል ወይስ በደጅ ይዘጋብናል?????
አቤቱ አድነን እኛም እንድናለን!!!
► እውነትና ስንቅ ለጊዜው ከባድ ይመስላል እየቆየ ግን ይቀላል። ክርስቲያን እውነት የሆነው የክርስቶስ ተከታይ ነው። ታዲያ አንዱን እውነት የሆነ ጌታ እየተከተልን ንግግራችንና ስራችን ለምን መንታ ይሆናል? እውነት መናገር ቢያቅተን እንጸልይ ለምን ሀሰት እንናገራለን?
► እውነት ሁለተኛም ሶስተኛም የላትም። አንዲት ናት። ወዳጆቼ እውነትን ውደዱ።
ሐናንያና ሰጲራ ጌታን አምነው ለመከተል ቢወስኑም ሀሰትን ገርዘው መጣል አልቻሉምና በሞት ተቀጥተዋል። እውነት የሀሰት ተቃራኒ ነው። እውነተኛ ሁኑ! ለህሊናችሁ ህልውና ኑሩ!ለዚህ የማይኖኑ ብዙ አሉና።
► ህሊና የእግዚአብሔር ድምፅ የሚተላለፍበት፣ መልካም የሆነውን እንድንፈፅም የሚጠቁመን፣ ስህተት ስንሰራ ዕረፍት የሚነሳን፣ ፀጥታን የሚነፍገን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው። ህሊና ጽድቅንም ፍርድንም ይመሰክራል።
► እዚህ ምድር ላይ ሁሉም ነገር የልምምድ ውጤት ነው። ውሸት የገዛን ምክንያት ውሸትን ደጋግመን ስለተለማመድናት ነው።እንዲሁ እውነት መናገርንም ራስችንን ካስለመድን እውነተኛነት ትገዛናለች።
@apostolicfellowship
ACIMCA 2021 - Virtual Youth Conference - via Zoom
የወጣቶች ኮንፍራንስ በዙም
Meeting ID: 6477022625
Password: 2625
Join the meeting by clicking on this link or using the details above in the zoom app
Saturday 3rd April
16:00 CEST -
“ እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ፥ አንተ ግን ወደ እነርሱ አትመለስም።”
— ኤርምያስ 15፥19
@apostolicfellowship
📌 ሌላ ሸክም አልጭንባችሁም ያላችሁን ጠብቁ
የዮሐንስ ራእይ 2፡18-25 ... ሌላ ሸክም አልጭንባችሁም፥ ነገር ግን እስክመጣ ድረስ ያላችሁን ጠብቁ።
📌እምነት
📌ትዕግስት
📌ፍቅር
📌ሥራ
📌አገልግሎት
በቄስ ወንደሰን ታደሰ
በሚያዝያ 21, 2012
@apostolicfellowship
Let us consider where Hagar was when she called on God as El-Roi. She was invisible, she was hungry, she was hurting, she was rejected, she was running, she was hopeless, she was without family... Hagar was empty. It was in that emptiness and that desolation that Hagar felt seen by God. It was in the valley that Hagar knew there was the One who sees her, and so she knew she can look upon Him for strength, satisfaction, and security.
We should pray that in this world that often urges us, women, to look within for answers, to look within for strength and satisfaction, I pray sincerely that we are women devoted to looking to Him who sees us through and through. Our help comes only from Him, sisters.
አጋር እግዚአብሔርን ኤል-ሮኢ (የሚያየኝን አሁን አየሁት) ብላ ስትጠራው በሕይወቷ የት እንደነበረች እስቲ እንመልከት፡፡ እሷ የሚያያት ያጣች ነበረች፣ የተራበች፣ የተጎዳች፣ ውድቅ የተደረገች፣ የተባረረች፣ እየሮጠች ያለች፣ ተስፋ የቆረጠች ፣ ቤተሰብ የሌላት፣ የሚቆምላት ያጣች ነበረች ... አጋር ባዶ ነበረች፡፡ አጋር በእግዚአብሔር ፊት እንደታየች የተሰማት በዚያ ባዶነት እና በዚያ መጥፋት ውስጥ ነበር፡፡ አጋር እሷን የሚያይ አንድ አምላክ እንዳለ፣ የሚቆረቆርላት አባት እንዳለት ያወቀችው በሸለቆው ውስጥ ነበር። ከዚያም ቦታ ለማለፍ ጥንካሬን፣ እርካታን እና ደህንነትን እንዲሰጣት ወደ እርሱ ወደሚያያት ብቻ ማየት እንዳለባት የተማረችውም እዚያ ነው።
ብዙውን ጊዜ እኛ ሴቶች፣ ለሕይወታችን ጥያቄ መልስ ለማግኘት ወደ ውስጥ እንድንመለከት፣ ጥንካሬን እና እርካታን ለማግኘት ወደ ራሳችን እንድናተኩር በሚያሳስበን በዚህ ዓለም ውስጥ፣ እኛ ወደ ሚያየን፣ ወደ የሚቆረቆርልን፣ ወደ እርሱ ለመመልከት የወሰንን ሴቶች እንድንሆን ከልብ እንፀልይ፡፡
march 8 by
Diana Y.
@apostolicfellowship
ዓመታዊ የገንደባ ኮንፍረንስ ላይ የቀረበ መልዕክት
በቢሾፕ ጌታሁን ላምቤቦ
@apostolicfellowship
#MissitNot From #ACIFNA
ሁላችሁም ኮንፍራንሱን በ video እንድትታደሙ ተጋብዛችኋል
የአለም አቀፍ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ህብርት በሰሜን አሜሪካ
#Virtualconference
You are cordially invited to be blessed in this virtual conference via zoom.
From Jan 30 - 31, 2021
Morning 9:00 am - 1:00 pm CST
Afternoon 2:00pm - 6:00:pm CST
Zoom meeting ID : 848 2692 3348
To join Audio : Dial 346 248 7799
Metting ID : 848 2692 3348
May Lord Jesus Christ bless you all.
@apostolicfellowship
" እንድትሰጠኝ እለምንሃለሁ "
📌 ለፆም የበረታ ሰውነት
📌 ለፀሎት የሚተጋ ልብ
📌 በጎ የሚያደርግ ህሊና
📌 መልካም የሚያይ አይን
📌 በደልን የሚረሳ አዕምሮ
📌 ይቅርታ የሚጠይቅ አንደበት
📌 ለተቸገሩ የሚመፀውት እጅ
እንድትሰጠኝ እለምንሃለሁ !!!
“እኔም እላችኋለሁ፦ ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።”
ሉቃ11፥9
@apostolicfellowship
''ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ ንስሐ ግቡ ተመለሱም ''
በቄስ ወንደሰን ታደሰ
“እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።”
ሐዋ3፥19-20
▸ በተለያየ አገር ለምትኖሩ አዲስ ዓመት ለሆነላችሁ ቅዱሳን ሁሉ ይሄንን መልዕክት ጋብዘናችኋል!
የመጽናናት ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
@apostolicfellowship
