en
Feedback
🇪🇹Ethio-Boostify🇩🇪

🇪🇹Ethio-Boostify🇩🇪

Open in Telegram

🚀 Ethio Boostify | Boost Your Social Media Presence We specialize in boosting your followers on Instagram, TikTok, YouTube, and more! Fast, reliable services to enhance your brand’s credibility and reach. Join us for updates, tips, and exclusive offers!🔥

Show more
The country is not specifiedEducation92 634
1 009
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1830 days
Posts Archive
#ትምህርት_ሚኒስቴር " ፈተናው የሚቀር አይደለም " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ * ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ተማሪዎቻችሁን አዘጋጁ ! የመውጫ ፈተና በ2015 ዓ/ም መሰጠት ይጀምራል። ይህን በተመለከተ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢፕድ ከሰጡት ማብራሪያ ፦ " ... በሙሉ አቅማችን እየተዘጋጀን ነው። የሚቀር ነገር አይደለም ፤ 2015 ትምህርት ዘመን ማብቂያ ላይ ፤ ከዚህ በፊት እንደነበረው ዝም ብሎ ዲግሪ የሚሰጥበት ነገር ሀገሪቱን በጣም ክፉኛ ጎድቷታል የሚል እምነት አለን። ይሄንንም ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች ጋር፣ ከግል ኮሌጆች ፕሬዜዳንቶች እና ኃላፊዎች ባለቤቶች ጋር ፣ ከዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ተማሪዎች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረግንበት ነው። ይሄ አዲስ ሀሳብ አይደለም አተገባበሩ ነው አዲስ የሆነው። ከዚህ በፊት ተሞክሮ ተቃውሞ ስለንበር ነው የተተወው። የህግና የህክምና ትምህርቶችን ብቻ እንዲሰጡት አድርጎ አሁንም እየተሰጡ ሌሎች በሙሉ ተትተው ነበር። አሁን ግን በአጠቃላይ ከከፍተኛ ትምህርት ጥራት ችግር ጋር በተገናኘ ምንም ልንወጣው የማንችለው እና ያን ጥራት ለማስተካከል ዩኒቨርሲቲዎቹ በራሳቸው ባስተማሩበት እና እራሳቸው በሰጡት ፈተና ብቻ የሚለኩበት ሁኔታ ከጀርባው ያለ ጠንካራ የሞራል መሰረት ይጠይቃል። ዩኒቨርሲቲዎቹ እራሳቸው ድግሪ ስንሰጥ ለማህበረሰቡ ይሄ ሰው እንዲህ እንዲህ አይነት ትምህርቶችን፣ እውቀቶችና ክህሎቶች አሉት ብለን ነው እየነገርን ያለነው። ... ከዚህ በፊት አንዱ የነበረው ችግር ማሳለፍ የሚባል ነገር አለ። ዝም ብሎ ማሳለፍ ምክንያቱም ተማሪዎች ከወደቁ የትምህርት ክፍሉን ድክመት ያሳያል እየተባለ ሲሳራበት የነበረው ነገር ምን ያህል ሀገሪቱን እንደጎዳት አሁን ለውይይትም የሚቀርብ አይደለም። እኔ በዚህ ጉዳይ ባለፉት ሰባት (7) ወራት በትምህርት ዘርፍ ከሚሰሩ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች የግል ኮሌጆች ባለቤቶች እንደዚህ አይን ያወጣ የለም መሆን የለበትም የሚል ክርክር አልሰማሁም። ሁሌ የሚሰማው ለምን በኛ ጊዜ ? ለምን ባንተ ጊዜ ለምን በሌላውስ ሰው ጊዜ የሚለውን ልትመልስ አትችልም ይሄ ዝም ብሎ ደረቅ ክርክር ነው። በአንድ በሆነ ጊዜ መጀመር አለበት ምክንያቱም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ላይ እየደረሳ ያለው ጉዳት ሀገሪቱን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት ነው። ይሄንን ዝም ብለን ማለፍ አንችልም ብለን እየሄድንበት ነው። ለተማሪዎችም ፣ ለወላጆችም፣ ለቤተሰብም አንድ (1) ዓመት የመዘጋጃ ጊዜ ሰጥተናል። ለኮሌጆችም ተማሪዎቻቸውን እንዲያዘጋጁበት ጊዜ ሰጥተናል ይሄን ጊዜ በደንብ ተጠቅመው ስራቸውን መስራት አለባቸው። ይሄ የመውጫ ፈተና የተማሪዎች ፈተና ብቻ አይደለም። ከተማሪዎች በላይ የትምህርት ክፍሎች፣ የኮሌጆች ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፈተና ነው። ምን እያደረጉ ነው ዩኒቨርሲቲዎቹ የሚለውን እንደትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ የምናገኘው ፤ እነዚህ ኮሌጆች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በእርግጥም ተማሪዎችን እያበቁ ነው ? ወይስ የዲግሪ ወፍጮ ቤት እንደሚሏቸው ዝም ብሎ ጊዜ እያስቆጠሩ ድግሪ የሚሰጡ ናቸው የሚለውን የምንለይበት ነው። ስለዚህ የሚቀር አይደለም። ሁሉም እንደማይቀር አውቆ የተሰጠውን የመዘጋጃ ጊዜ በደንብ ተጠቅሞ ትምህርትን በደንብ አስተምሮ በደንብ አስጠንቶ ቢያዘጋጅ ነው የሚሻለው " @Academic_learn @Academic_learn

ከ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ጋር ተያይዞ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች ቅሬታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። ተማሪዎች ቅሬታቸውን ወደ ከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ በአካ
ከ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ጋር ተያይዞ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች ቅሬታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። ተማሪዎች ቅሬታቸውን ወደ ከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ በአካል በመሄድ ማቅረብ እንደሚችሉ የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አበበ ቸርነት ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። የተማሪዎቹ ውጤት ወደየትምህርት ቤቶች መላኩን የገለጹት ኃላፊው፤ በተፈጠረው የኔትወርክ መጨናነቅ ምክንያት ውጤታቸውን ማየት ያልቻሉ ተማሪዎች ወደትምህርት ቤታቸው በመሄድ ማየት እና መውሰድ ይችላሉ ብለዋል፡፡ @Academic_learn @Academic_learn Stay Safe!

ጀግኖች አትሌቶቻችን በኦሪገን 2022 አትሌቲክስ ሻምፒና ባስመዘገቡት ስፓርታዊ ድል ላቅ ያለ ደስታ ተሰምቶናል። ለጀግኖች አትሌቶቻችን የተሰማንን ክብር በሚኒስቴር መስሪያቤታችንና ተጠሪ ተቋሞቻችን አ
+4
ጀግኖች አትሌቶቻችን በኦሪገን 2022 አትሌቲክስ ሻምፒና ባስመዘገቡት ስፓርታዊ ድል ላቅ ያለ ደስታ ተሰምቶናል። ለጀግኖች አትሌቶቻችን የተሰማንን ክብር በሚኒስቴር መስሪያቤታችንና ተጠሪ ተቋሞቻችን አመራሮች፣ ሠራተኞችና መላ ሕብረተሰባችን ስም ለመግለጽ እንወዳለን።

የ2014 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተኘ ውጤት ይፋ ሆነ፡፡ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛው መርሀ ግብር፣ በማታ እና በግል ለፈተና ከተቀመጡ 6494
የ2014 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተኘ ውጤት ይፋ ሆነ፡፡ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛው መርሀ ግብር፣ በማታ እና በግል ለፈተና ከተቀመጡ 6494 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውስጥ 4236 ተፈታኞች 50% እና በላይ ያመጡት አፈጻጸም በመቶኛ 65.87% መሆኑና በ2013ዓ.ም ተፈትነው 50% እና በላይ ያመጡ ተማሪዎች 51.1% የነበረ ሲሆን በ14.77% በመብለጥ አፈጻጸሙ የተሻለ ሆኗል፡፡ በ2014ዓ.ም ከተፈተኑት መደበኛ ተማሪዎች ውስጥ ማለፊያ ነጥቡን በማግኘት ወደ 9ኛ ክፍል ማለፍ የቻሉ ተፈታኞች 5261 ሲሆኑ ይህም 98% ሆኗል፡፡ ከእነዚህም ለፈተና ከተቀመጡ 90 የአፋን ኦሮሞ ተማሪዎች 100% ያለፉ ናቸው፡፡ ተማሪዎች በብቃታቸው ለማለፍና ከኩረጃ በጸዳ ሁኔታ ለመፈተን ያደረጉትን እንቅስቃሴ እያበረታታን በቀጣይ ክፍሎችም ይህንን አጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ ለነበሩ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የትምህርት ባለሙያዎች፣ ወላጆች፣ የወላጅ ኮሚቴዎች እና በየደረጃው ያሉ የትምህርት አመራሮች ምስጋናቸውን በማቅረብ በ8ኛ ክፍል የተመዘገበውን ውጤት በ12ኛ ክፍል ላይ ለመድገም ተማሪዎች በክረምት እየተሰጠ ያለውን ማጠናከሪያ ትምህርት አጠናክረው እንዲከታተሉ፤ ተማሪዎችን ጨምሮ የሚመለከታቸው የትምህርት ማህበረሰብ በሙሉ በቂ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት

#ነፃ_ጥቅል_ከኢትዮ_ቴሌኮም ኢትዮ ቴሌኮም በ2014 በጀት አመት 61 ነጥብ 3 ቢሊዮን ገቢ ማግኘቱን የገለፀ ሲሆን ደንበኞቼም 66 ሚሊየን ደርሰዋል ብሏል። ይህም የእቅዱን 87.6 በመቶ ነው። ይህን
#ነፃ_ጥቅል_ከኢትዮ_ቴሌኮም ኢትዮ ቴሌኮም በ2014 በጀት አመት 61 ነጥብ 3 ቢሊዮን ገቢ ማግኘቱን የገለፀ ሲሆን ደንበኞቼም 66 ሚሊየን ደርሰዋል ብሏል። ይህም የእቅዱን 87.6 በመቶ ነው። ይህን በማስመልከት ለሦስት ቀናት የሚቆይ ነጻ ጥቅል ስጦታ ማቅረቡን ገልጿል። በዚህም፦ 👉 1.5 ጌጋባይት ዳታ በቀን 512 ሜባ፤ 👉 45 ደቂቃ በቀን 15 ደቂቃ፤ 👉 100 መልዕክት በቀን 33 መልዕክቶችን፤ 👉 የ10 ደቂቃ አለምአቀፍ ጥሪ በቀን 3 ደቂቃ ለተጠቃሚዎች በነጻ አቅርቧል። ⚡️ስጦታው ከዛሬ ሐምሌ 21 ከሌሊቱ 06:00 ሰአት - እስከ ንጋቱ 12 ሰአት ድረስ ለ3 ቀናት ይቆያል። Join and share for more @Academic_learn @Academic_learn @Academic_learn

" ውጤታችሁን በየት/ቤታችሁ ማየት እና መወሰድ ትችላላችሁ " - ትምህርት ቢሮ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸድን በየትምህርት ቤታቸው ማየት እና መውሰድ ይችላሉ ብሏል። ቢሮው " ይፋ በተደረገው የውጤት መመልከቻ ሊንክ #በኔትዎርክ_መጨናነቅ ምክንያት ውጤታችሁን ያላያችሁ ተማሪዎች በየት/ቤታችሁ ማየት እና መውሰድ ትችላላችሁ " ብሏል። ተማሪዎች ውጤታቸውን እንዲያዩ ይፋ የተደረገው አድራሻ እስካሁን እየሰራ እንዳለሆነ ለማወቅ ችለናል። @Academic_learn

​​Where do the world's best doctors study?👨🏽‍⚕️ If you feel that medicine is your calling, you should aim for the following universities: 💊 Oxbridge (University of Oxford / University of Cambridge) "An overwhelming experience," is how one Oxford student describes his first year as a medical student. Oxford and Cambridge, two of the most prestigious universities in England, are also top-ranked in the list of the best medical schools. A win-win choice! 💊 Harvard University Harvard is home to some of the biggest discoveries in basic medicine. Students here have unique research opportunities in biochemistry, cell biology, immunology and stem cells. In 2009, Harvard genetics professor Jack Szostak won the Nobel Prize for his discovery of telomeres: parts of the DNA molecule that prevent cells from aging. Going to Harvard means being involved in the development of high-tech medicine. 💊 University College London (UCL) In 1997 UCL united under its aegis several of London's most prestigious specialized medical institutions. At one of them, St Mary's Hospital Medical School, Alexander Fleming discovered penicillin, the world's first antibiotic, in 1928. The first-class infrastructure allows UCL scientists today to conduct research that dramatically changes the face of medicine. 💊 Stanford University Stanford physicians were the first to synthesize an artificial DNA molecule, the first to perform heart transplant surgery, the first to isolate mouse stem cells, and the first to invent a technique that allows the ovaries of infertile women to produce eggs. This is, without any qualifications, a first-rate medical school. 💊 John Hopkins University Medical students at John Hopkins University train under conditions that are as close to combat as possible, as they practice in the best university hospital in the United States. With 33 state-of-the-art operating rooms, 902 labs, and top-notch physician training every day, medical school in Baltimore, Maryland, is a recognized brand in the world of health care. One of the best options for those who are focused on working with real patients. For more join👇👇👇👇👇👇 @Academic_learn @Academic_learn

ተማሪ ብንያም ቃል የተገባለትን አርቴፊሻል እጅ ተረከበ አቶ ሰለሞን አማረ የተባለ በጎ ፈቃደኛ በአሁን ሰዐት ወደ ትምህርት ገበታው ተመልሶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታ
ተማሪ ብንያም ቃል የተገባለትን አርቴፊሻል እጅ ተረከበ አቶ ሰለሞን አማረ የተባለ በጎ ፈቃደኛ በአሁን ሰዐት ወደ ትምህርት ገበታው ተመልሶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ትምህርቱን በመከታተል ላይ ለሚገኘው ተማሪ ብኒያም አንድ እጁ አካል ጉዳት ያለበት በመሆኑ አርቴፊሻል እጅ ለማስገጠም ከዚህ ቀደም ቃል ገብቶለት ነበር። አቶ ሰለሞን ቃል በገባው መሰረት በዛሬው ዕለት በተወካዩ በጋዜጠኛ ራሔል አበበ አማካኝነት አርቴፊሻል እጁን ከነሙሉ መገጣጠሚያው ለተማሪ ቢንያምና አባቱ አቶ ኢሳይያስ ፕሮፌሰር ብሩክ ላምቢሶ ቢሮአቸው ድርስ በመገኘት አስረክበዋል:: በቀጣይም ወደ ሀገር ቤት በሚመጣበት ጊዜ እጁን ለክቶ ጥሬ እቃዎቹን ገጣጥሞ ሙሉ ለሙሉ እንዲጠቀምበት እንደሚያደርግም ቃል ገብቷል። የሀገር ልጅ የማር እጅ 👏 @Academic_learn @Academic_learn

📚📑የministry ማለፊያ ውጤት ለሴት እና ወንድ በቅርቡ ይፋ ስለሚሆን በትግስት ይጠብቁ እስከዛ ለሁሉም ያጋሩ @Academic_learn @Academic_learn

#top_5 በአፍሪካ በወጣትነት እድሜ ክልል የሚገኙ አምስት መሪዎች❗️ 1⃣ የ38 ዓመቱ የቻድ ፕሬዝዳንት መሃማት ዲቢ 2⃣ የ 39 ዓመቱ የማሊ ፕሬዝዳንት አሲሚ ጎይታ 3⃣ የ41 ዓመቱ የጊኒ ፕሬዝዳ
#top_5 በአፍሪካ በወጣትነት እድሜ ክልል የሚገኙ አምስት መሪዎች❗️ 1⃣ የ38 ዓመቱ የቻድ ፕሬዝዳንት መሃማት ዲቢ 2⃣ የ 39 ዓመቱ የማሊ ፕሬዝዳንት አሲሚ ጎይታ 3⃣ የ41 ዓመቱ የጊኒ ፕሬዝዳንት ማማዲ ዱምቡያ 4⃣ የ41 ዓመቱ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት ፖዉል ሄንሪ ዳሚባ 5⃣ የ45 ዓመቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ በአፍሪካ በወጣትነት እድሜ ክልል የሚገኙ መሪዎች ሲሆኑ አብዛኞቹ ግን ከወጣትነት እድሜ ክልል ያለፉ መሆናቸው ታውቋል። © DW @Academic_learn

የአዲስአበባ ትምህርት ቢሮ የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት በonline መመልከት እንደሚቻል አሳውቁ ነበር ነገር ግን በአጋጠመው የኔቶርክ መጨናነቅ ምክንያት ለበርካታ ተማሪዎች እየሰራ አለመሆኑን ተገንዝቦ ችግሩን ለማስተካከል እየሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊ አቶ አበበ ለኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን ገልፀዋል። ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ @Academic_learn @Academic_learn

" የተቀመጠው አድራሻ በአግባቡ ስለማይሰራ ውጤታችንን ማየት አልቻልንም " - ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘንድሮው የስምንተኛ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን አሳውቋል። ቢሮው ተማሪዎች ውጤታቸውን https://aaceb.gov.et/%e1%8b%a88%e1%8a%9b-%e1%8a%ad%e1%8d%8d%e1%88%8d-%e1%8b%89%e1%8c%a4%e1%89%b5/ ወይም aaceb.gov.et ላይ በመግባት ማየት እንደሚችሉ ገልጾ ነበር። ነገር ግን ቢሮው ይፋ ያደረገው ውጤት መመልከቻ አድራሻ በትክክል ስለማይሰራ ውጤት ለማየት እንዳልቻሉ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች አሳውቀዋል። በመሆኑም ፤ የከተማው ትምህርት ቢሮ አድራሻው ላይ ያለውን ችግር እንዲያርም /እንዲያስተካክል እንዲሁም ለህዝብ ይፋ ከመደረጉ በፊት ተገቢውን ፍተሻ ማለፉን ሊያረጋግጥ ይገባል ብለዋል። በአዲስ አበባ ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 29 /2014 ዓ/ም በተሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና ከ71 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ይፋ በተደረገው መረጃ ለፈተናው ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 63.9 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፤ 85.5% ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል ለመዛወር ችለዋል። ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ @Academic_learn @Academic_learn

#Update በአዲስ አበባ የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች ተከታዩን ሊንክ በመጫን ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ፦ https://aaceb.gov.et/%e1%8b%a88%e1%8a%9b-%e1%8a%ad%e1%8d%8d%e1%88%8d%e1%8b%89%e1%8c%a4%e1%89%b5/ ወይም aaceb.gov.et ላይ በመግባት የሬጅስትሬሽን ቁጥር በማስገባት እና GO የሚለዉን በመጫን ውጤታችሁን ኦንላይን ማየት ትችላላችሁ፡፡ @Academic_learn

"አረንጓዴ አሻራን በማኖር ለትውልድ የተሻለች አገር ማስረከብ ይገባል" ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ................................................. አረንጓዴ አሻራን በማኖር
+7
"አረንጓዴ አሻራን በማኖር ለትውልድ የተሻለች አገር ማስረከብ ይገባል" ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ................................................. አረንጓዴ አሻራን በማኖር የአየር ንብረትን መጠበቅና ለትውልድ የተሻለች አገር ማስረከብ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናገሩ ። የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች እና ሰራተኞች ''ኑ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብስ'' በሚል መሪቃል የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በኦሮምያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን አደኣ ወረዳ ሆረ ክሎሌ ቀበሌ በተደረገው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለጹት አረንጓዴ አሻራን በማኖር አገር መውደድን በተግባር መግለጽ ይገባል። ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብና መጠበቅ እንደሚገባም ፕሮፌሰር ብርሀኑ አሳስበዋል ። የአደአ ወረዳ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አበበ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማቱ ሠራተኞቹ አረንጓዴ አሻራ በማኖራቸው አመስግነዋል። በወረዳው ለአረንጓዴ አሻራ 23 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተው 96 በመቶ ያህሉ መተከላቸውን ኃላፊው ጨምረው አስረድተዋል። በችግኝ ተከላው ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ( ዶ/ር) ፣የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አንዱአለም አድማሴ( ዶ/ር) ፣የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ( ዶ/ር) እና የትምህርት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።

#AddisAbaba የ8ኛ ክፍል ውጤት ይፋ ተደረገ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። ለፈተና ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 63.9 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡ ይህም ካለፉት አመታት ከተመዘገቡት ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ውጤቶች አንጻር ሲታይ ከፍተኛ ውጤት ሆናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 85.5% ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል ለመዛወር መቻላቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተፈና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዲናኦል ጫላ ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎች ውጤታቸውን ቀጥሎ ያለውን ሊንክ በመጫን https://aaceb.gov.et/%e1%8b%a88%e1%8a%9b-%e1%8a%ad%e1%8d%8d%e1%88%8d-%e1%8b%89%e1%8c%a4%e1%89%b5/ ወይም aaceb.gov.et በመጠቀም ሬጅስትሬሽን ቁጥር በማስገባት እና GO የሚለዉን በመጫን ውጤታችሁን ኦላይን ማየት ይችላሉ ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሳውቋል። በሌላ በኩል ፤ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ትምህርት ቢሮው ይፋ ያደረገው የውጤት መመልከቻ ድረገፅ እየሰራላቸው እንዳልሆነ በመጠቆም ያለው ችግር እንዲስተካከል ጠይቀዋል። @Academic_learn

ለዝች አጭር እድሜ ለዚህ ከንቱ አለም፣ እድሜያችን ተመዞ ላንኖር ዘላለም፣ በድንገት ተጠርተን ላይቀር መሄዳችን፣ መልካም ጥሩ ይሁን ሁል ግዜ ስራችን። ፧ 💐 @Academic_learn💐

​▬▬ ይህንን ያውቁ ኖሯል❓ ▬▬ ➠ በጣም ከፍተኛ ድምፅ ያለው ሙዚቃ የምንጠጣውን የአልኮል መጠን ይጨምረዋል፡፡ ➠ ግሪክ በአለማችን በጣም ረጅም ብሔራዊ መዝሙር ያላት ሀገር ስትሆን መዝሙሩም 158 ስንኞችን ይዟል፡፡ ➠ የምንሰማው የሙዚቃ ዓይነት ስለአካባቢያችን የሚኖረንን አመለካከት የመቀየር አቅም አለው፡፡ ➠ በ2015 ዓ.ም ቴይለር ስዊፍት በቀን ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ አግኝታለች፤ በየአመቱም በፈረንጆቹ ታህሳስ 13 የቴይለር ስዊፍት ቀን እየተባለ ይከበርላታል፡፡ ➠ አንድ ጥናት እንደሚያሳየው ከሆነ መኪና በሚያሽከረክሩበት ወቅት ሰምተው የማያቁትን ሙዚቃ ቢሰሙ ተረጋግተው እንዲነዱ ይረዳዎታል፡፡ ➠ ክላሲካል ሙዚቃዎች የአዳማጩን የአእምሮ ልህቀት ደረጃ ለመጨመር ይረዳል። ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ 🍁 @Academic_learn📸 ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯

Richard Nixon proposed to his wife on their first date. #People Join and share @Academic_learn

The Placebo Effect ▶️ጊዜው 2ተኛው የአለም ጦርነት ላይ ነው በሀገረ አሜሪካ የተጎዱ ወታደሮች ቁጥር በመብዛቱ ምክንያት የህመም ማስታገሻ መድሀኒት (Morphine) ከሆስፒታሉ ጠፋ እና በጊዜው የነበረው የህክምና ሀላፊ Henry Beecher ያደረገውን አስገራሚ ነገር ላጋራቹ 📌ሁሉንም የህክምና ባለሙያ ሰበሰበ እና የተጎዱትን ወታደሮች በድብቅ ውሃ እና ጨው በጥብጠው በመርፌ እንዲወጓቸው አደረገ በሚገርም ሁኔታም ወታደሮቹ በ 2 ቀን ውስጥ ከህመማቸው ሊድኑ ችለዋል 📌ይህ እንዴት የሆነ መሰላቹ መድሀኒት ስንወስድ የሚሰራው መድሀኒቱ ብቻ አይደለም "ሳይኮሎጂም" ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው ይህንንም ተከትሎ ምንም ጥቅም የሌለው ነገር ቢሰጠንም እስካመንበት ድረስ ልንድን እንችላለን። እንደውም ህፃን ሆነን ስንወድቅ በጣም ቢያመንም የምንወደው ሰው መቶ ሲስመን ህመሙ የተወን ይመስለን የለ😂 SOURCE: Ethiology 🇪@Academic_learn

You know you can’t put your shadow over mirrors like you do on other objects @Academic_learn