en
Feedback
🇪🇹Ethio-Boostify🇩🇪

🇪🇹Ethio-Boostify🇩🇪

Open in Telegram

🚀 Ethio Boostify | Boost Your Social Media Presence We specialize in boosting your followers on Instagram, TikTok, YouTube, and more! Fast, reliable services to enhance your brand’s credibility and reach. Join us for updates, tips, and exclusive offers!🔥

Show more
The country is not specifiedEducation92 634
1 009
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1830 days
Posts Archive
#MoE " የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች በተላከውን እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው ደብዳቤ መመልከት ችለናል። በዚሁ መሠረት ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ዩኒቨርስቲዎች ፦ 1. ምንም አይነት የመደበኛ ተማሪ በግቢ እንዳይኖር እንዲያደርጉ፤ 2. በቀጣይ በሚገለጸው ተማሪ ቁጥር ልክ ምግብ እንዲቀርብ ዝግጅት እንዲያደርጉ፤ 3. ለፈተናዎች ማቆያ ቦታ እንዲዘጋጅ እና 4. የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በፕሬዚዳንት የሚመራ ዋና ግብረ-ኃይልና በየካምፓሶቹ በዲን /ካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ-ኃይል እንዲያደራጁ መልዕክት ተላልፎላቸዋል። ዩኒቨርሲቲዎች የ2ዐ15 የአካዳሚክ ካላንደር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወቅት (ከመስከረም 28 - ጥቅምት 17) ታሳቢ በማድረግ እንዲያዘጋጁ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳስበዋል። @Academic_learn

#ደምቢ_ዶሎ • " በሆስፒታሉ እንዲህ አይነት ክስተት ሲከሰት ይህ የመጀመሪያው ነው " - ዶ/ር ፀጋዬ ሚደክሳ • " እንዲህ አይነት ክስተት የመከሰት እድሉ በጣም አናሳ ነው " - ዶ/ር ናጋሳ ቶላሳ
+1
#ደምቢ_ዶሎ • " በሆስፒታሉ እንዲህ አይነት ክስተት ሲከሰት ይህ የመጀመሪያው ነው " - ዶ/ር ፀጋዬ ሚደክሳ • " እንዲህ አይነት ክስተት የመከሰት እድሉ በጣም አናሳ ነው " - ዶ/ር ናጋሳ ቶላሳ በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት ማስተማሪያ ሆስፒታል 2 ጭንቅላት ያለው ህፃን ተወለደ። የዩኒቨርሲቲው የጤና ሳይንስ ማስተማሪያ ሆስፒታል የጽንስና ማህፀን ህክምና እስፔሻሊስት ዶ/ር ፀጋዬ ሚደክሳ በሰጡት ማብራሪያ ህፃኑ ሁለት ጭንቅላት ኖሮት መወለዱን ተናግረዋል። ዶ/ር ፀጋዬ ፤ በሆስፒታሉ እንዲህ አይነት ክስተት ሲከሰት ይህ የመጀመሪያው መሆኑን በመግለፅም ህፃኑ በተሳካ ቀዶ ጥገና መወለዱን አስረድተዋል። በአንዳንድ ነፍሰ ጡር እናቶች ላይ እንደዚህ አይነት ክስተቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ እና በእናቶች ማህፀን ውስጥ በሚስተናገዱ እንቁላሎች ብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ዶ/ር ፀጋዬ አብራርተዋል። በኢኒስቲትዩቱ የህጻናት ህክምና ስፔሻሊስት ዶ/ር ናጋሳ ቶላሳ በበኩላቸው ክስተቱ በመንታ ምድብ የሚመደብ እና የመከሰት እድሉ በጣም አናሳ መሆኑን ገልፀዋል። በአሁኑ ጊዜ እናትም ሕፃኑም #በጥሩ_ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia @tikvahuniversity

ማሳሰቢያ ለሁሉም የትምህርት ተቋማት አዲሱ ስርዓተ ትምህርት አተገባበር በተመለከተ አጭር ማብራሪያ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ1ኛ_8ኛ ክፍል ተግባራዊ ይደረጋል። አዲሱ የመፀሀፍት ህትመት እንዳለቀ ለትምህርት ቤቶች ይሠራጫል በሳምንት የሚሠጠዉ የክ/ግዜ ብዛት 35 ነዉ። የክፍለ ግዜ ስርጭት በቅርቡ ይላካል 7ኛ እና 8ኛ ክፍል ICT ትምህርት ስለሚሰጥ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባል። ቅድመ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አዲሱ ስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ይካሄዳል። ነባሩን ስረዓተ ትምህርት መፀሀፍት በ2015 ዓ.ም ማስወገድ አይቻልም ።አወጋገዱን በተመለከተ ትምህርት ቢሮ አቅጣጫ ያስቀምጣል። አዲሱ የስረዓተ ትምህርት መፀሀፍ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለመምህራን የማስተዋወቅ ስራ ይሠራል።ቀኑ ወደፊት ይገለጻል። የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከነሀሴ 3 ጀምሮ ከአዲስ አበባ ትምሀርት ቢሮ መፀሀፍ መግዛት ይችላሉ። Via የካ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት @Academic_learn

ማንኛውም የግል ትምህርት ቤት መፅሃፍም ሆነ ደብተር መሸጥ እንደማይችል ማሳሰቢያ ተሰጠ‼️ አንድ የትምህርት ተቋም ፍቃድ የተሰጠው ለማስተማር እንጂ፤ መጽሐፍም ሆነ ደብተር ለመሸጥ አይደለም ሲል የ #አዲስአበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፍቅርተ አበራ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ማንኛውም የግል ትምህርት ቤቶች ከመመሪያ ውጪ ያልተገባ ክፍያ አስከፍለው በተገኙ ተቋማት ላይ ርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል።። በመመሪያ አተገባበሩ ላይ የተለያዩ ጥቆማዎች እየደረሱ እንደሚገኝም ኃላፊዋ አክለዋል። በመመሪያ አተገባበሩ ላይ ከመጡት ጥቆማዎች ውስጥ አንዳንድ ተቋማት የምዝገባ ክፍያ መጨመር፣ በዓይነት መቀበል ለአብነት እሽግ ወረቀት እና የመፀዳጃ ቤት የንፅህና እቃዎችን የሚጠይቁ እንዳሉበት ገልፀዋል። በተጨማሪም ባልተፈቀደ ክፍያ ጭማሪ እያደረጉ ያሉ የትምህር ተቋማት እንደሚገኙ ጥቆማ ደርሶናል ወርደን እናስተካከልን ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ማንኛውም የግል ትምህርት ቤቶች ከመደበኛ ክፍያ ውጪ በየትኛውም መልኩ ክፍያ ማስከፈል አይቻሉም፤ አንድ የትምህርት ተቋም ፍቃድ የተሰጠው ለማስተማር እንጂ መጽሐፍም ሆነ ደብተር ለመሸጥ አይደለም ብለዋል።ከተሰጠው ፍቃድ ውጪ ሲንቀሳቀስ በሚገኝ ተቋም ላይ ርምጃ ይወሰድበታል፤ የሰበሰበውን ገንዘብም ሆነ ማንኛውንም አይነት ቁሳቁስ እንዲመልስ ይደረጋል ሲሉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፍቅርተ አበራ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። #share_please🙏🙏🙏 Invite your friends @Academic_learn

📌Advanced Synonyms 🔥 Very calm ― Screen Very ugly ― Hideous Very small ― Petty Very funny ― Hilarious Very quiet ― Hushed Very rich ― Wealthy Very expensive ― Costly Very dirty ― Filthy Very tall ― Towering Very easy ― Effortless Very wet ― Soaked Very slow ― Sluggish Very good ― Excellent Very stupid ― Idiotic Very happy ― Ecstatic Very exciting ― Exhilarating Very warm ― Hot Very weak ― Frail Very little ― Tiny Very bright ― Luminous Very busy ― Swamped Very careful ― Cautious Very clear ― Obvious 📣SHARE 📢SHARE ╔════════════ 📚JOIN: @Academic_learn 📚JOIN: @Academic_learn

"የሚገነቡት ትምህርት ቤቶች ዘመናዊና የወደፊቷን ኢትዮጵያ የሚመስሉ ናቸው" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ የትምህርት ሚኒስትር ................................................
+4
"የሚገነቡት ትምህርት ቤቶች ዘመናዊና የወደፊቷን ኢትዮጵያ የሚመስሉ ናቸው" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ የትምህርት ሚኒስትር ................................................................................... በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በጦርነቱ ከወደሙ ትምህርት ቤቶች መካከል በሰሜን ወሎ ዞን በሐብሩ ወረዳ በመርሳ ከተማ መልካ ጨፌ ትምህርት ቤት ግንባታ መሠረት ድንጋይ ተቀመጧል፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በአማራ እና አፋር ክልል ሙሉ በሙሉ የወደሙ 1ሺሕ 300 ትምህርት ቤቶችን በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ለመገንባት መታቀዱን አንስተዋል። የሚገነቡት ትምህርት ቤቶችም ዘመናዊና የወደፊቷን ኢትዮጵያ የሚመስሉ ናቸው ብለዋል። የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የተቋማቱን ደረጃ የማሳደግ ሥራ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በትኩረት እየሠራ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ፕሮፌሰር ብርሀኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአማራ ክልል 8 ትምህርት ቤቶችን በአማራ እና አፋር ክልሎች የሚገነባውን ሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅትም አመስግነዋል። የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪ ጋሻው አስማሜ በበኩላቸው አሸባሪው ሕወሓት የሰሜን ወሎ ዞን የሚገኙ 777 ትምህርት ቤቶች ላይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ውድመት ማድረሱን ገልጸዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፋንታ ማንደፍሮ፣ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ተጠሪ አቶ ይልማ ታዬን ጨምሮ የሀብሩ ወረዳ እና የመርሳ ከተማ አስተዳዳሪዎች እንዲሁም መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።

ነፃ የትምህርት ዕድል ! የሳንድፎርድ ኢንተርናሽናል ት/ቤት በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር በሚገኙ የመንግሥት ት/ቤቶች በመማር ላይ ከሚገኙ #በትምህርታቸውና #በፀባ
+1
ነፃ የትምህርት ዕድል ! የሳንድፎርድ ኢንተርናሽናል ት/ቤት በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር በሚገኙ የመንግሥት ት/ቤቶች በመማር ላይ ከሚገኙ #በትምህርታቸውና #በፀባያቸው የተመሰከረላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ የነፃ ትምህርት ዕድል ለመሥጠት ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ አሳውቆናል። ተወዳዳሪ ተማሪዎች ለነፃ ትምህርቱ ውድድር ለመመዝገብ ሲመጡ የሚከተሉትን መስፈርቶች አሟልተው የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት መግለጫ ኮፒ ይዘው መምጣት ይጠበቅባቸዋል። 1. በአ/አ ከሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪ መሆን 2. ተማሪው የተወለደው እ.ኤ.አ ነሐሴ 31/2008 ድረስ 14 ዓመት የሚሞላዉ ነገር ግን 15 ዓመት በታች የሆነ ይህንንም የሚያረጋግጥ የልደት የምሥክር ወረቀት ይዘው መቅረብ የሚችሉ 3. በ2014 የትምህርት ዘመን መጨረሻ የ8 ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አማካይ ወጤት ከ95% በላይ የሆነ 4. የ7ና 8 የክፍል ትምህት ለየብቻው አማካይ ውጤቱ ከ90% በላይ የሆነ 5. ስለመልካም ሥነምግባሩ ወይም ፀባዩ ከሚማርበት ት/ቤት የጽሁፍ ማስረጃ በሳንድፎርድ ተቀባይነት ሲያገኝ ማምጣት የሚችል 6. ት/ቤቱ የሚሰጠውን የመግቢያና ቃለመጠይቅ ፈተናዎችን የተሻለ ዉጤት ማስመዝገብ 7. የወላጅ/የአሳዳጊ ሙሉ ፈቃድ ያገኘ 8. አሸናፊ የሚሆነው ተማሪ በአሥረኛ (10) ክፍል በት/ቤቱ ተመዝግቦ ለመማር ፈቃደኛ የሆነ ናቸዉ። 9. የምዝገባ ሰዓት ጠዋት 2፡30 - 6:00 ከሰዓት ከ7:30 - 9:30 መስፈርቱን ያሟሉ ተማሪዎች ነሐሴ 19/2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ለፅሁፍ ፈተና ይቀርባሉ። ቦታ፦ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል አካባቢ በሳንድፎርድ ት/ቤት እስከ ነሐሴ 18 ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል።

ቢልጌት በአንድ ወቅት ኢንተርቪው ተደርጎ ከተናገረው ንግግር ላካፍላችሁ ወደድኩ የአለማችን ቀዳሚ ባለፀጋ ቢልጌት በአንድ ወቅት በኢንተርቪው እንዲህ ተጠየቀ ከአንተ የሚበልጥ ባለፀጋ ማን ነው? ከአንተ የሚበልጥህ ባለፀጋ አለ? አዎ የሚበልጠኝ ሰው አለ..የሚበልጠኝ አንድ ጥቁር ሰው ብቻ ነው...ከብዙ ዓመት በፊት ወደ ኒውዮርክ መሄድ ነበረብኝ...ወደ ኒውዮርክ ለመሄድ አየር መንገድ ላይ ሳለሁ የተለያዩ ጋዜጦችን የጋዜጣ አዟሪዎች እጅ ላይ አየሁ። ካየኋቸው ጋዜጦች መካከል አንዱን ወደድኩት ለመግዛት አስቤ ኪሴ ስገባ ዝርዝር ስላጣሁ ሳልገዛው መልሼ ተውኩት። በድንገትም አንድ ጥቁር ጋዜጣ አዟሪ ልጅ መጣና ጋዜጣውን ሰጠኝ። ዝርዝር የለኝም አልወስደውም አልኩት እርሱም ችግር የለውም በነጻ ውሰደው አለኝና በነጻ ሰጠኝ። ከሦስት ወር በኋላ ተመልሼ በዚያው አየር መንገድ ማለፍ ነበረብኝና በዚያ አየር መንገድ ሳልፍ አሁንም አጋጣሚ ሆነና ያንን ጋዜጣ አዟሪ ጥቁር ልጅ አገኘሁት። አሁንም በነፃ ጋዜጣ ሰጠኝ። እኔም በነፃ አልቀበልህም አልኩት እርሱም ግድየለም ከትርፌ ላይ እቀንሳለሁ ውሰድ አለኝና በነጻ ሰጠኝ። ከ19 አመትም በኋላ ባለጠጋ ከሆንኩ በኋላ ያንን ልጅ ፈልጌ ለማግኘት ወሰንኩና ፈለኩት ከአንድ ወር ከሁለት ሳምንት ፍለጋም በኋላ አገኘሁት። ከዚያም አወቅከኝ ብዬ ጠየኩት። ፈገግ አለና አንተን የማያውቅ አለ እንዴት አዎ አውቅሃለሁ ዝነኛው ቢልጌት አይደለህም አለኝ በሙሉ ፈገግታ። ከብዙ አመት በፊት ሁለት ጊዜ ጋዜጣ በነጻ ሰጥተኸኛል፡፡ ያንን ውለታህን አካክሼ መመለስ እፈልጋለሁና የፈለከውን የትኛውንም ነገር እሰጥሃለሁ ጠይቀኝ አልኩት፡፡ ያም ጥቁር ሰው በምንም መካካሻ ልትሰጠኝ አትችልም አለኝ። እኔም ለምን አልኩት እኔ የሰጠውህ ደሃ በነበርኩ ጊዜ ከድህነቴ ነው። አንተ ግን ልትሰጠኝ የመጣኸው ባለፀጋ በሆንክበት ጊዜ ነው። እነዚህን ሁለቱን እንዴት አካክሰህ ልትሰጠኝ ትችላለህ? ቢልጌትም ያ ጥቁር ወጣት በርግጥም ከእኔ የሚበልጥ ባለፀጋ ነው። ለመስጠት ባለጠጋ መሆንህን ወይም ባለጠጋ እስክትሆን ድረስ አትጠብቅ። መስጠት የልብ ጉዳይ ነው እንጂ የአቅም ጉዳይ አይደለም!!! ቼር ሌሊት🙏🙏🙏 #ከወደዱት_ለወዳጅ_ዘመድዎ #share Join&share 👉 @Academic_learn

ከ 16 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የመፅሀፍት ድጋፍ ተደረገ -------------------------------------- በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉልደ ኢትዮጵያዊያን ም
+6
ከ 16 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የመፅሀፍት ድጋፍ ተደረገ -------------------------------------- በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉልደ ኢትዮጵያዊያን ምሁራን ከ 16 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የመፀሀፍት ድጋፍ አደረጉ። በድጋፉ ርክክብ ወቅትም የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተገኝተዋል። ምሁራኑ ድጋፉን ያደረጉት ለአብርሆት ቤተ መፅሀፍትና ለሶስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው። ከ አብርሆት ቤተመፅሀፍት በተጨማሪ ድጋፍ የተደረገላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወሎ ፣ ወልዲያ እና መዳወላቡ ዩኒቨርስቲዎች ናቸው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ዲያስፖራው በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚያደርገውን ድጋፉ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። የአብርሆት ቤተ መፅሀፍት እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ሃላፊዎች ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው ድጋፉን ተረክበዋል።

ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ይጀምራል❗️ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ በሚጀምረው አዲሱ ስርአተ ትምህርት ( ካሪኩለም) መሰረት ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናቀቂያ ፈተና መውሰድ የሚጀምሩ ይሆናል። ለሁሉም ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች ከተላከ ፋይል እንደተረዳነው የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ካላንደር የተገለጸ ሲሆን ከሰኔ 12 እስከ ሰኔ 16 /2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ ሁሉም ተማሪዎች የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ሲወስዱ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ በልዩ ሁኔታ የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መውሰድ ይጀምራሉ። በ2009 ዓ.ም የመጨረሻው የ10ኛ ልፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከተሰጠ እና የ10ኛ ክፍል መልቀቂይ ብሔራዊ ፈተና ( ማትሪክ) መሰጠት ካቆመና ተማሪዎች በክፍል ውጤታቸው ብቻ ማለፍ ከጀመሩ ወዲህ ጥቂት ጊዜያት በኋላ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት እንደሚጀምር ሲገለጽ ቆይቶ ነበር። ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ @Academic_learn @Academic_learn

12ኛ ክፍል መረጃ‼️ የ 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ መስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጥ ሲሆን 👉 ተማሪዎች ከክልላቸዉ ዉጭ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ይፈተናሉ።( በጣም ከባድ ውሳኔ ነው) 👉 ፈታኞች ከሌላ ክልል (ብሄር) ይሆናሉ። 👉 ተማሪዎች ፈተናውን በራሳቸው ለመስራት ካሁኑ በደንብ ማጥናት ይኖርባቸዋል። ፈተናው ከስርቆት ና ከኩረጃ የፀዳ እንዲሆን ዝግጅት እየተደረገ ነው። 👉 የፈተናው አወጣጥ ከ 9-12 በተማሩት የትምህርት አይነቶች ስሆን በዋናነት የ 11ኛ እና 12ኛ ክፍልን ያካትታል። 👉በፈተናው ወቅት ዩኒቨርስቲወች እና አከባቢው ላይ የ #internet አገልግሎት ልቋረጥ ይችላል። ስለዚህ ፈተናው ብሰረቅ እንኳን ተማሪዎች ጋር አይደርስም። 👉 ትክክለኛው የፈተናው ቀን ወደፊት ይነገራል። ለሁሉም ተማሪዎች የት ዩኒቨርስቲ እንደሚፈተኑ አስቀድሞ ይነገራል። ይህን መሰረት አድርጎ ተማሪዎችን ማዘጋጀትና በስነ ልቦና መገንባት ያስፈልጋል። @Academic_learn

Document 4.pdf

#NationalExam የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል። የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
#NationalExam የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል። የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። ፈተናው ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ተብሏል። የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ከቀናት በፊት መገለፁ ይታወሳል። የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም። ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው። Via Tikvah ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ https://t.me/Tmhrt_Minister https://t.me/Tmhrt_Minister

#Reminder 🛎 #National_Exit_Exam በመጪው 2015 ዓ/ም መጨረሻ ላይ የመውጫ ፈተና መሰጠት ይጀምራል። በ2015 ዓ.ም መጨረሻ መተግበር በሚጀምረው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ከሰሞኑን የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለአዲስ ዘመን ማብራሪያ ሰጥተው ነበር። ሚኒስትር ዴኤታው ካነሳሷቸው ሃሳቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው • የመውጫ ፈተና ምዘና የሚሰጠው ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ብቻ ነው። • በግልም ሆነ በመንግስት የትምህርት ተቋም የሚማር ተማሪ ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ሲያልፍ ብቻ ነው፡፡ • የመውጫ ፈተናው የሚዘጋጅበት፣ የሚያዝበት እና የሚሰራጭበት ስርዓት ከሰው ንክኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ ነው። • በየዓመቱ ከ150 እስከ 180 ሺህ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚመረቁ ተማሪዎችን ምዘና ለመስጠት የሚያስችል አቅም አለ፡፡ • የሙያ ማኅበራት አቅማቸው ሲጎለብት የሙያ ፈተና ይሰጣሉ፤ የመውጫ ፈተና ሥራን ከመንግስት ይረከባሉ። • ፈተናውን የሚያሰናዱ ተቋማትና መምህራን ዝግጅት ሥራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ፡፡ • የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጸኝነቱ የተጠበቀ ለማድረግ እየተሰራበት ነው። @Academic_learn

የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችና አመራሮች በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ችግኝ ተከሉ። .............................................. የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋ
+5
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችና አመራሮች በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ችግኝ ተከሉ። .............................................. የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአረንጓዴ አሻራ የማኖር እና የ3 አቅመ ደካማ ቤቶችን እድሳት ስራ ጀምረዋል። ሀምሌ 29/2014 ዓም. በተከናወነው ፕሮግራም ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ ( ዶ/ር ) ዩኒቨርስቲዎች ችግኝ እየተከሉ የአቅመ ደካሞችንም ቤት እያደሱ ነው ብለዋል። ጽዱ አረንጓዴ እና ምቹ ከባቢ ለመፍጠር ተግቶ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን በበጋውም መንከባከብ እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል። በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ብቻ 36 ችግኞችን የተከሉት ዶ/ር ሳሙኤል በ8 ዩኒቨርስቲዎች 100 ችግኞችን ለመትከል አቅደው ከእጥፍ በላይ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል። በመርሃ ግብላይ የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትና የከተማው አስተዳደር ተወካዮች ተገኝተዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ እንደሚተገበር በሚጠበቀው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ የዩኒቨርስቲ መዉጫ ፈተና ምንድነዉ? •ብቁ የሰው ሃይል በማዘጋጀት ወደ ኢኮኖሚ መግባቱን ማረጋገጫው አንደኛው መንገድ ነዉ:: •ተመራቂዎች በተማሩበት ሙያ፤ ዘመኑ የሚጠይቀውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ገንብተው ስለመውጣታቸው የሚመዝን ነዉ፡፡ •ዲግሪ በያዙ ተመራቂዎች መካከል በብቃት የሙያውን ምሉዕነት ተላብሶ የተመረቀው የትኛው እንደሆነ ይመዝናል ምዘናዉ ለማን ይሰጣል? •ምዘናው የሚሰጠው በመጀመሪያ ዲግሪ ላይ ብቻ ነዉ •ትግበራው አገራዊ ፖሊሲ እንደመሆኑ በግል፣ በመንግስትም በየትኛውም ተቋም የሚማር ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ካለፈ ነዉ፡፡ ምዘናዉ ለምን እና በማን ይሰጣል? •ተማሪዎች ሲገቡ እንጂ ለምን ወውጫ ላይ ይፈተናሉ የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ቢሆንም ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡት የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ተፈትነው መሆኑን መዘንጋት አይገባም •የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ 1152/2011 የመውጫ ፈተና ሊሰጥ እንደሚችል በግልጽ አስቀምጧል፡፡ የሪፎም አካል ነው፣ •የሪፎም አጀንዳን መንግስት የሚመራው እንደመሆኑ ሂደቱን ትምህርት ሚኒስቴር መንግስትን ወክሎ የሚሰራዉ ነዉ፡፡ ምዘናዉን ለማካሄድ ምን እየተሰራ ነዉ ? •ትምህርቶቹን የሚያዘጋጁ ተቋማትና መምህራን የዝግጅት ስራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ :: @Academic_learn @Academic_learn

👩🏼‍🦰Caligynephobia is the fear of beautiful women. 🤔The more often you see someone, the more attractive you think that person is. This is called the mere-exposure effect. 😎One way to tell that someone is lying online is their underuse of personal pronouns and overuse of adjectives. 😘When two people kiss, they exchange between 10 million and 1 billion bacteria.

#National_Exit_Exam በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም መጨረሻ መተግበር በሚጀምረው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ
#National_Exit_Exam በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም መጨረሻ መተግበር በሚጀምረው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ለአዲስ ዘመን ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ካነሳሷቸው ሃሳቦች የሚከተሉት ይገኙበታል፦ • የመውጫ ፈተና ምዘናው የሚሰጠው ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ብቻ ነው። • በግልም ሆነ በመንግስት የትምህርት ተቋም የሚማር ተማሪ ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ሲያልፍ ብቻ ነው፡፡ • የመውጫ ፈተናው የሚዘጋጅበት፣ የሚያዝበት እና የሚሰራጭበት ስርዓት ከሰው ንክኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ ነው። • በየዓመቱ ከ150 እስከ 180 ሺህ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚመረቁ ተማሪዎችን ምዘና ለመስጠት የሚያስችል አቅም አለ፡፡ • የሙያ ማኅበራት አቅማቸው ሲጎለብት የሙያ ፈተና ይሰጣሉ፣ የመውጫ ፈተና ሥራን ከመንግስት ይረከባሉ። • ፈተናውን የሚያሰናዱ ተቋማት እና መምህራን ዝግጅት ሥራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ፡፡ • ሂደቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጸኝነቱ የተጠበቀ ለማድረግ እየተሰራበት ነው። @Academic_learn

#ትምህርት_ሚኒስቴር የ2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚገልፁት ፕ/ር ብርሃኑ ጎን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ፈተናው በዩኒቨርሲቲዎችና በፌዴራል ተቋማት እንደሚሰጥም ገልፀዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢፕድ የሰጡት ቃል፦ " ...የክልል ባለሟሎች፣ የክልል ኃላፊዎችን ከፈተና ጉዳይ ጋር እንለያቸው ፤ ፈተናው እራሱ የፌዴራል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ስለሆነ በፌዴራል ተቋማት ውስጥ ብቻ እንስጥ ብለን አሁን በሙሉ ተማሪዎቹን አጓጉዘን ቢቻል ሁሉንም ከክልላቸው ውጭ በሆኑ ክልሎች ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እና የፌዴራል ተቋማት ውስጥ ለመስጠት ነው እየተዘጋጀን ያለነው። ያ የሚያደርገው ሁለት ነገር ነው። አንደኛ በመንገድ ላይ ሊኖር የሚችለውን የመሰረቅ አደጋ ይቀንሰዋል። ሁለተኛ ክፍል ውስጥ ከተገባ በኃላ ለመስረቅ የሚቻልበትን አደጋ ይቀንሰዋል። ከዛም በላይ ፈተናዎቹን በማዘጋጀት ደረጃ በፊት በ4 የተለያዩ ፈተናዎች ነበር የምናዘጋጀው እስከ 12 አድርገን Completely scrambled እንዲሆኑና ማንም ጎኑ ያለው ተማሪ የሚፈተነው ፈተና አንተ ከምትፈተነው ፈተና order ጋር በፍፁም ያልተገናኘ እንዲሆን አድርገን እየሰራን ነው። ይሄ በጣም በብዙ ደረጃ የፈተና ስርቆትን ይቀንሰዋል ብለን ነው ተስፋ የምናደርገው። "             Share share🙏🙏 ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇 ╔═══════════╗ ♨️ ♦️ @Academic_learn

‼️Point የ 2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ጥቅምት ወይም ህዳር ይሰጣል። የ 2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በጥቅምት ወይም ህዳር ወር እንደሚሰጥ ታውቋል። ትምህርት የ ፈተናውን ቀን በትክክል ባይነገርም አካሄዱን አስቀምጧል። ፈተናው በዩኒቨርስቲዎች እና በመንግሥት ተቋሟት ውስጥ ስለሚሰጥ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን እስከ ጥቅምት ድረስ እንድሸኙ እየተደረገ ይገኛል። ስለዚህ ሁሉም የአምና ተፈታኞች እስከ ጥቅምት ወይም ህዳር ድረስ 1ኛ አመታቸውን ይጨርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የ 12ኛ ክፈል ፈተና በምን ይሰጣል የሚለው እስካሁን አልተወሰነም። ብሆንም ታብሌቶች እስካሁን ስላልገቡ ፈተናው በወረቀት የመሰጠት እድሉ በጣም ሰፊ ነው። ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ @Academic_learn @Academic_learn