337
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ
በሀገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ለ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ እና ከተማ አቀፍ ፈተና ይቀመጣሉ።
ፈተናው በክልሎች እንዲሁም በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ሰኔ 26 እና ሰኔ 27 /2015 ዓ/ም እንደሚሰጥ ከየክልሉ ትምህርት ቢሮዎች ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
በዘንድሮው ዓመት በሚሊዮን ሚቆጠሩ ተማሪዎች ፈተናው ላይ የሚቀመጡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ግዙፎቹ የኢትዮጵያ ክልሎች ኦሮሚያ እና አማራ በድምሩ ከ830 ሺህ በናይ (አማራ 347,666 ፤ ኦሮሚያ 484,994) ተማሪዎችን ፈተና ላይ ያስቀምጣሉ።
በደቡብ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ፣ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ75 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተና ላይ የሚቀመጡ ሲሆን በሌሎች ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ በርካታ ሺዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
እንደ ክልል ትምህርት ቢሮዎች መረጃ በአጠቃላይ በመላው ሀገሪቱ ፈተናውን የሚወስዱት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ናቸው።
ነገ መሰጠት የሚጀምረው ፈተና ሙሉ ቀን (ጠዋት እና ከሰዓት) እንደሚሰጥ የታወቀ ሲሆን ተፈታኞች እርሳስ፣ ላጲስ እና ማስመሪያ ብቻ ወደ ፈተና ማዕከላት ይዘው መሔድ ይችላሉ።
ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ዲጂታል ሰዓት እንዲሁም ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ በፈተና ማዕከላት መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
ወላጆችም ልጆቻችሁ የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ይዘው ወደ መፈተኛ ጣቢያ እንዳይሄዱ ክትትል አድርጉ።
@tikvahethiopia
Today, the girls' 6th grade and 7th grade passed the soccer competition that was held in our school in a fun and educational manner that teaches students throughout the year, and the boys' 8th grade and 7th grade reached, and the girls' 6th grade won with a result of 3-0. The 8th grade was the winner of the penalty shootout in a very exciting contest among the boys.
ዛሬ በትምህርት ቤታችን አመቱን ሙሉ ተማሪዎችን በሚያስተምር በሚያዝናና እና ትምህርታዊ በሆነ መልኩ ሲካሄድ የነበረው የእግርኳስ ውድድር በሴቶች የ6ኛ ክፍል እና የ7 ኛ ክፍል ማለፍቸው እንዲሁም በወንዶች የ 8ተኛ ክፍል እና የ 7ተኛ ክፍል ደርሰው ነበር በዚህም የሴቶች የ 6ኛ ክፍል 3-0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ በወንዶች ጥሩ አጓጊ በሆነ ፍክክር በፍፁም ቅጣት ምት የ 8ተኛ ክፍል አሸናፊ ሆኗል።
ዛሬ በትምህርት ቤታችን የኦሮምያ ሞዴል ፈተና የ8ተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው።
በትምህርት ቤታችን በተካሄደው የጥሎ ማለፍ ውድድር ላይ በቀኑ ትምህርታዊና ልጆችን በሚያንፅ መልኩ ውድድሩ ሲካሄድ ነበረ በዚህም በ ሴቶችም በወንዶችም ውድድር ሲካሄድ የነበረ ሲሆን በሴቶች
8ኛ ክፍል ከ 6ኛ ክፍል ባደረጉት ግጥሚያ የ6ኛ ክፍል አሸናፊ ሲሆን በወንዶች የ 8ኛ ክፍል ከ 6ተኛ ክፍል ባደረጉት ግጥሚያ የ 8ኛ ክፍል አሸናፊ ሆኗል በዚህም የ ፍፃሜ ተፋላሚ የሚሆኑት
በሴቶች 7ኛ ክፍል Vs 6ኛ ክፍል
በወንዶች 8ኛ ክፍል Vs 7ኛ ክፍል የሚጋጠሙ ይሆናል።
