en
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Open in Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Show more
2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሰላም እንዴት ናችሁ "የስንኝ ቋጠሮ" members እንግዲህ ቻናላችን እንደሚታወቀው የ እናንት ድምፅ በመሆኑ የጥበብ ስራዎቻችሁን ላኩልን በፍጥነት ወደ እናንተ እናደርሳለን። በዚህ ቻናል ፖስት የሚደረጉ ግጥሞችን ያለ ፀሃፊው ፈቃድ ወይም ምንጭ ሳይጠቅሱ ለሌላ አላማ ማዋል በፍፁም የተከለከለ ነው‼️ ይቀላቀሉን👉 @gitmv Share ያድርጉ

sticker.webp0.15 KB

በ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ሁለተኛው ዙር ውድድር በድል ተጠናቅቋል። አንደኛ Blue Fish የ አስር በር ካርድ ሁለተኛ ጎሳዬ ፍቄ የ አምስት ብር ካርድ ሶስተኛ ቃለአብ መስፍን የ ሶስት ብር ካርድ ተሸልመዋል !! ይቅርላቀሉን @gitmv

አለቀ ሶስተኛ 🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆

ቀድሞ 25 ያመጣ ሶስተኛ ይወጣል!!

ሶስተኛ ማን ይወጣል ?? እናያለን

ሁለተኛ 😂🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆

አንደኛ 🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆 #1

👉👉👉የፍቅር አቡጊዳ👈👈 በለስላሳ ቆዳ በቀለመ ውበት ሲፃፍ ሲለቀለቅ በስንጥሩ እንጨት አቦይ ሲያስተምሩ ሲገፅፅ ሲመክሩ ድንቁርናን ከቶ ከኛ ሲያርቁ ሲያባርሩ ;;;;; በዛ ቀጭን በትር በቆዳው ፅሁፍ ላይ እየጠነቆሉ ሀ ግዕዝ ሁ ካእብ ብለው እያቀባበሉ ፈፅመን ስንለያይ አቡጊዳን አውቀን እኔ ግን ቅር አለኝ መለያየታችን ;;;;;;; በትልቁ ዋርካ ስር ፀሀይ በማይደርሰው ከጎጆ ቤታችን ሩቅ ላይ ካረፈው ጋራ ወንዛ ወንዙን አልፈን በምናየው ከዛ ሩቅ ዛፍ ስር ነዉ ሆነን ምንማረው ;;;;;;;; በእንጨት ቁራጭ ላይ በድርድር አለቶች በብዙ ፊደላት ከፍ ባሉ ቁጥሮች የንታን ስንጠብቅ የፊደል መምሬን በዝክረ በአሉ ዳቦ ቁርሱን አይተን የንታችን አገኙን ቦታ ቦታ ይዘን ;;;;; በአይኖቿ አይታኝ ሳያት ስንተያይ ት/ቱን ዘንግተን አንድ ፊደል ሳንቆጥር ሁሉም ሲበታተን ብቻችንን ቀርተን ;;;;;; የልብ ልባችን ሳንደብቅ ሳንሰስት እንቅጩን አወራን ይህ ነዉ አቡጊዳ የቅኔ ት/ት በፍቅር ወላፈን ተውጠን የተጠመድንበት ;;;;;;; አሁንማ ጊዜው ይሄው ተቀይሮ ፍፁም ተሻሽሎ የቆዳው ላይ ፅሁፍ በደብተር ተስሎ አሁንማ ጊዜው ውስጡ ተሸፋፍኖ የሞነጨርንበት ብዕር እስክርቢቶ ሆኖ ;;;;;;; አለት የነበረው በወንበር ታመነ ዋርካ የነበረው ድርብርብ ፎቅ ሆነ የአሁኑ ትምህርት ምንም ባይቀርብን በምንም ባይጎዳ የፍቅሩ ገበታ አይቅር አቡጊዳ ግጥም =በቃለአብ መስፍን @gitmv #code_12

ላንተ ተቀጣው😘 ✍Maki

ላንተ ተቀጣው😘 ✍Maki

❤በህልሜ ስትመጪ አንተ እያመንካት ~ጥላህ ለሄደች ሴት ምን ይሉት ~ቅብጠት ነው ምን ይሉት ~ህመም ነው ምን ይሉት ሰቆቃ ምን ይሉት ~ሀዘን ነው እያለ ቡረቃ ምንአይነት ሀዘን~ ነው ምን አይነት ሞኝነት የሄደን እያሰቡ~ ከራስ ጋር መጋጨት እያልኩኝ ለልቤ~ ስመክረው እቆይና በህልሜ ስትመጪ ~ያገረሽብኛል እነደገና😠😠😠 #blue fish @gitmv #code_10

ውበት የት አለ አፍንጫ ተበስቶ ጌጥ ካንጠለጠለ ጡት ተገላልጦ ሰውን ካማለለ አላማ ተረስቶ ለስሜት ብቻ እየተኖረ በብልጭልጭ ተታሎ ልብንካሳፈረ ፍቅርን አረስቶ ስሜትን አበርትቶ ውበት ካሉትማ ተገላልጦ መሄድን መኖር ካሉትማ ተቀባብቶ መውጣትን የራስን ባህል ረስቶ የሌላውንይዞ እዉነተኛ መልክ ተረስቶ የሌላውን ጉዞ ለነፍስ እንደሚኖር ተረስቶ ለስጋ እየተኖረ ቀጣዩ ትውልድ ማንነቱን እንዲረሳ እየተጣረ የባህል ቀሚስ ተረስቶ መገላለጥ ፋሽን ሆነ የኢትዮጵያ ባህል የትም ተበተነ ✍ብሌን አለማየሁ 👉 @gitmv #code_9

#እዚህ_እዛ ❤️ ፈልጌ አስፈልጌ አጣሁሽ እዚህ እዛ ምነው ጠፋሺብኝ እነደ ጠዋት ጠዛ። ✍በቶላዋቅ ኢተፋ 👉 @gitmv #code_8

#ተውኩሽ እንጂ ገና ከጅምሩ በግድ አስጀምረሽ የኔ ነው ለማለት ጥሎሽ ሁሉ ጥለሽ እኔ ተውኩሽ እንጂ ማን አባቱ ቀማኝ ከኔ ለባሰበት ሰጠሁሽ ለ ለማኝ Endalk ye adelw✍✍ #code_7 👉 @gitmv

ቄስ ይጥራው ትዝ ይልሻል ውዴ አስታወሽ፣ የሞተው አካሌን ሬሳዬን የለወሽ። ስምሽን ስጠራው ስምህን ቄስ ይጥራው ያልሽኝ፣ አፍ አውጥተሽ እንዲያ የረገምሽኝ። ይኸው ዛሬ እርግማንሽ ደርሶ፣ በድኔን ሆኛለሁ ሰውነቴ ፈርሶ። ሆዴ የተናገርሽው ጠብ አላለም፣ ከምላስሽም ፀጉር ከቶ አልተነቀለም። ይሰማኛል ቄሱ ክርስትና ስሜን ሲጠይቁ፣ ዲያቆኖቹም ሁላ በፀሎት ሲደምቁ። አንቺ ታውቂው የለ ንገሪያቸው፣ ክንፈ ገብርኤል ነው በያቸው። ከንፈር ቀዳዳ አለው ነውና ወንፊት፣ የማይደርስ መስሎሻል ሲቀርብ ከሰው ፊት። ✍Mekonnen yoseph(babi) 👉 @gitmv #code_6

#ይብላኝለት በዚህች ብኩን አለም በሰቀቀን መንደር መረጋጋት የለም ከመቸኮል በቀር የረጋ በሙሉ ከእሳት ላይ ተጥዷል ስለረጋ ብቻ እንደ ሰም ቀላልጧል አንኮራፍቶ አዳሪ ዧ ብሎ ሚተኛ እንደምን ይቻላል ካልተሆነ ቤተኛ እንጂማ አሁን ላይ ሰው ካልታለለ በዚህ ዘመን ላይ ማንቀላፋት እንጂ መተኛት የታለ እንዳዞ በአንድ አይኔ እያንቀላፋውኝ በአንድ አይኔ ፈጥጬ ስንቴ አነጋሁኝ ይብላኝ ካለኝ ፀጋ እንቅልፌን ለነሳኝ መኝታዬን ወስዶ ፀሐፊ አርጎ ላነሳኝ ✍ Mike #code_5 👉 @gitmv

👉ፍትሕ ለተማሪ😢😢😢 ሀ ብለን ጀምረን ብዙ ተምረናል ቤተ ዘመዶችን ብዙ አስቸግረናል ለሀገር ለመጥቀም እዚህ ደርሰናል እናም ወገኖ ፍትህ ይገባናል። የዩኒቨርሲቲ ላይፍ እናያለን ብለን ብዙ ተሰቃየን በኮረና ስምም አንድ አመት ተቀጣን 2ኛ ደገምን ተምረን ተምረን ወና ላይ እንዳንቀር አንድ ነገር በሉን ለሚመለከተዉ መልእክት አድርሱልን። የተማረ አይዎድቅም ሲሉ ሰማሁና መማሬን ጀመርኩኝ ከፊደል ሀ አልኩና ለካ ዉሸት ኖሯል የሰማሁት ወሬ ይኸው ባዶ ሆንኩኝ ተምሬ ተምሬ ፍትህን ፈልገን በአንድነት ቆመናል እኛ ተማሪዎች ፍትህ ይገባናል። (የ2012ተፈታኞች ድምፅ) ✍ ፍስሃ #code_4 👉 @gitmv

ለፅዷ እኔ የምልሽ አንቺ ፅድ..ውብ ተክል መሆንሽ ሳያንስሽ በአለም ውበት ቁንጅናሽን ሊጨምር ይመስል ጫፍሽን ሲከረክም ተንከባካቢሽ ሊያጠፋሽ ነው መሰል መቀስ ይዟል ዛሬም 🤔🤔 አኬ አዶሌ #code_3 👉 @gitmv

ጥፋቴ ምንድነዉ????? መሄድሽ ላማይቀር ፍቅር አስዘሽኝ፣ መተዉሽ ላይቀር ስለምን ቀረብሽኝ፣ እኔ ተጎደሁኝ ባንች ፍቅር ዉዴ፣ መተሽ ካላደንሽኝ መሞቴ ነዉ እኔ። ጥፋቴን ሳላዉቀዉ ጥለሽኝ ሄደሻል፣ ልቤን ወስደሽ ሄደሽ ባዶ አስቀርተሻል፣ እሱም አልጠላዉም እኔ አልተቃወምኩም፣ ግን የመጥፍትሽ ነገር ምንም አላወኩም። ''በጣም ጎደተህኛል እንድህ አርገህኛል፣ ሰላም አሰጥተህ አሰምመህኛል'' ብለሽ ሳትይኝ ጥፋቴን ሳትነግርኝ፣ እንድዉ በደፈና ዝም ብለሽ መጥፋትሽ፣ እንኳን ለኔ ቀርቶ ለሰምም ግራ ነዉ፣ መህድሽን ሳስብ ምቀደመኝ እንባ ነዉ። እባክስ ንገርኝ ጥፋቴ ምንድነዉ?????? ++ ግጥም በጎሣዬ ፊቄ ሰኔ 28 /10/2012 #code_2 👉 @gitmv