የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
👉👉👉የፍቅር አቡጊዳ👈👈
በለስላሳ ቆዳ በቀለመ ውበት
ሲፃፍ ሲለቀለቅ በስንጥሩ እንጨት
አቦይ ሲያስተምሩ ሲገፅፅ ሲመክሩ
ድንቁርናን ከቶ ከኛ ሲያርቁ ሲያባርሩ
;;;;;
በዛ ቀጭን በትር በቆዳው ፅሁፍ ላይ እየጠነቆሉ
ሀ ግዕዝ ሁ ካእብ ብለው እያቀባበሉ
ፈፅመን ስንለያይ አቡጊዳን አውቀን
እኔ ግን ቅር አለኝ መለያየታችን
;;;;;;;
በትልቁ ዋርካ ስር ፀሀይ በማይደርሰው
ከጎጆ ቤታችን ሩቅ ላይ ካረፈው
ጋራ ወንዛ ወንዙን አልፈን በምናየው
ከዛ ሩቅ ዛፍ ስር ነዉ ሆነን ምንማረው
;;;;;;;;
በእንጨት ቁራጭ ላይ በድርድር አለቶች
በብዙ ፊደላት ከፍ ባሉ ቁጥሮች
የንታን ስንጠብቅ የፊደል መምሬን
በዝክረ በአሉ ዳቦ ቁርሱን አይተን
የንታችን አገኙን ቦታ ቦታ ይዘን
;;;;;
በአይኖቿ አይታኝ ሳያት ስንተያይ
ት/ቱን ዘንግተን
አንድ ፊደል ሳንቆጥር ሁሉም
ሲበታተን ብቻችንን ቀርተን
;;;;;;
የልብ ልባችን ሳንደብቅ ሳንሰስት እንቅጩን አወራን
ይህ ነዉ አቡጊዳ የቅኔ ት/ት
በፍቅር ወላፈን ተውጠን የተጠመድንበት
;;;;;;;
አሁንማ ጊዜው ይሄው ተቀይሮ ፍፁም ተሻሽሎ
የቆዳው ላይ ፅሁፍ በደብተር ተስሎ
አሁንማ ጊዜው ውስጡ ተሸፋፍኖ
የሞነጨርንበት ብዕር እስክርቢቶ ሆኖ
;;;;;;;
አለት የነበረው በወንበር ታመነ
ዋርካ የነበረው ድርብርብ ፎቅ ሆነ
የአሁኑ ትምህርት ምንም ባይቀርብን በምንም ባይጎዳ
የፍቅሩ ገበታ አይቅር አቡጊዳ
ግጥም =በቃለአብ መስፍን
@gitmv #code_12
2 046
ውበት የት አለ
አፍንጫ ተበስቶ ጌጥ ካንጠለጠለ
ጡት ተገላልጦ ሰውን ካማለለ
አላማ ተረስቶ ለስሜት ብቻ እየተኖረ
በብልጭልጭ ተታሎ ልብንካሳፈረ
ፍቅርን አረስቶ ስሜትን አበርትቶ
ውበት ካሉትማ ተገላልጦ መሄድን
መኖር ካሉትማ ተቀባብቶ መውጣትን
የራስን ባህል ረስቶ የሌላውንይዞ
እዉነተኛ መልክ ተረስቶ የሌላውን ጉዞ
ለነፍስ እንደሚኖር ተረስቶ ለስጋ እየተኖረ
ቀጣዩ ትውልድ ማንነቱን እንዲረሳ እየተጣረ
የባህል ቀሚስ ተረስቶ መገላለጥ ፋሽን ሆነ
የኢትዮጵያ ባህል የትም ተበተነ
✍ብሌን አለማየሁ
👉 @gitmv #code_9
2 046
ቄስ ይጥራው
ትዝ ይልሻል ውዴ አስታወሽ፣
የሞተው አካሌን ሬሳዬን የለወሽ።
ስምሽን ስጠራው ስምህን ቄስ ይጥራው ያልሽኝ፣
አፍ አውጥተሽ እንዲያ የረገምሽኝ።
ይኸው ዛሬ እርግማንሽ ደርሶ፣
በድኔን ሆኛለሁ ሰውነቴ ፈርሶ።
ሆዴ የተናገርሽው ጠብ አላለም፣
ከምላስሽም ፀጉር ከቶ አልተነቀለም።
ይሰማኛል ቄሱ ክርስትና ስሜን ሲጠይቁ፣
ዲያቆኖቹም ሁላ በፀሎት ሲደምቁ።
አንቺ ታውቂው የለ ንገሪያቸው፣
ክንፈ ገብርኤል ነው በያቸው።
ከንፈር ቀዳዳ አለው ነውና ወንፊት፣
የማይደርስ መስሎሻል ሲቀርብ ከሰው ፊት።
✍Mekonnen yoseph(babi)
👉 @gitmv #code_6
2 046
#ይብላኝለት
በዚህች ብኩን አለም
በሰቀቀን መንደር
መረጋጋት የለም ከመቸኮል በቀር
የረጋ በሙሉ ከእሳት ላይ ተጥዷል
ስለረጋ ብቻ እንደ ሰም ቀላልጧል
አንኮራፍቶ አዳሪ ዧ ብሎ ሚተኛ
እንደምን ይቻላል ካልተሆነ ቤተኛ
እንጂማ አሁን ላይ ሰው ካልታለለ
በዚህ ዘመን ላይ ማንቀላፋት እንጂ መተኛት የታለ
እንዳዞ በአንድ አይኔ እያንቀላፋውኝ
በአንድ አይኔ ፈጥጬ ስንቴ አነጋሁኝ
ይብላኝ ካለኝ ፀጋ እንቅልፌን ለነሳኝ
መኝታዬን ወስዶ ፀሐፊ አርጎ ላነሳኝ
✍ Mike #code_5
👉 @gitmv
2 046
👉ፍትሕ ለተማሪ😢😢😢
ሀ ብለን ጀምረን ብዙ ተምረናል
ቤተ ዘመዶችን ብዙ አስቸግረናል
ለሀገር ለመጥቀም እዚህ ደርሰናል
እናም ወገኖ ፍትህ ይገባናል።
የዩኒቨርሲቲ ላይፍ እናያለን ብለን ብዙ ተሰቃየን
በኮረና ስምም አንድ አመት ተቀጣን 2ኛ ደገምን
ተምረን ተምረን ወና ላይ እንዳንቀር አንድ ነገር በሉን
ለሚመለከተዉ መልእክት አድርሱልን።
የተማረ አይዎድቅም ሲሉ ሰማሁና
መማሬን ጀመርኩኝ ከፊደል ሀ አልኩና
ለካ ዉሸት ኖሯል የሰማሁት ወሬ
ይኸው ባዶ ሆንኩኝ ተምሬ ተምሬ
ፍትህን ፈልገን በአንድነት ቆመናል
እኛ ተማሪዎች ፍትህ ይገባናል።
(የ2012ተፈታኞች ድምፅ)
✍ ፍስሃ #code_4
👉 @gitmv
2 046
ጥፋቴ ምንድነዉ?????
መሄድሽ ላማይቀር ፍቅር አስዘሽኝ፣
መተዉሽ ላይቀር ስለምን ቀረብሽኝ፣
እኔ ተጎደሁኝ ባንች ፍቅር ዉዴ፣
መተሽ ካላደንሽኝ መሞቴ ነዉ እኔ።
ጥፋቴን ሳላዉቀዉ ጥለሽኝ ሄደሻል፣
ልቤን ወስደሽ ሄደሽ ባዶ አስቀርተሻል፣
እሱም አልጠላዉም እኔ አልተቃወምኩም፣
ግን የመጥፍትሽ ነገር ምንም አላወኩም።
''በጣም ጎደተህኛል እንድህ አርገህኛል፣
ሰላም አሰጥተህ አሰምመህኛል''
ብለሽ ሳትይኝ ጥፋቴን ሳትነግርኝ፣
እንድዉ በደፈና ዝም ብለሽ መጥፋትሽ፣
እንኳን ለኔ ቀርቶ ለሰምም ግራ ነዉ፣
መህድሽን ሳስብ ምቀደመኝ እንባ ነዉ።
እባክስ ንገርኝ ጥፋቴ ምንድነዉ??????
++ ግጥም በጎሣዬ ፊቄ
ሰኔ 28 /10/2012 #code_2
👉 @gitmv
