en
Feedback
Defence Construction Enterprise

Defence Construction Enterprise

Open in Telegram

Defence Construction Enterprise (DCE) is a leading construction company in Ethiopia, distinguished by its ability to operate in the country's most remote and challenging regions. We are deeply committed to building the nation.

Show more
1 717
Subscribers
-124 hours
-67 days
-1230 days
Posts Archive
የፕሬስ መግለጫ እመርታ ለዘላቂ ከፍታ! እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡ እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡ እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን! ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዲስ አበባ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ለኢንተርፕራይዙ ሠራተኞች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ነሀሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ግልጽነትን ለማስፈን፣ ሙስናን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ ላይ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በዋናው መሥሪያ ቤት ለሚገኙ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ። በሥልጠናው ግልጽነትን ለማስፈን፣ ሙስናን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መመሪያው ወሳኝ መሆኑን የገለጹት የኢንተርፕራይዙ የስነምግባር መከታተያ ቡድን መሪ ሻለቃ ጌትነት አንዱዓለም ሲሆኑ ሥልጠናው በኢንተርፕራይዙ ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ ሕጎችና አሠራሮች ላይ በቂ እውቀት እንዲኖራቸው እና ምዝገባውን በሚፈለገው ጊዜ ውስጥ ማከናወን እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። በሥልጠናው ወቅት ሀብቱን በወቅቱ ያላስመዘገበ ሠራተኛም ሆነ አመራር አግባብነት ባለው ሕግ መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆን በጥብቅ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል የሀብት ምዝገባ መረጃ ትክክለኝነት ማረጋገጫ እና ለሕዝብ ተደራሽ የሚደረጉ የጥቆማ ሥርዓቶች መዘርጋታቸው ተገልጿል። ሠራተኞች የመንግሥት ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና ሠራተኞች የሀብትና የገቢ ምንጫቸውን በኢንተርኔት አማካኝነት በቀላሉ የሚያሳውቁበትና የሚያስመዘግቡበት ዘመናዊ የዲጂታል ሀብት ምዝገባ ሥርዓት (EARS) ላይ በቂ ግንዛቤ ይዘው በአግባቡ እንዲያስመዘግቡ፣ የማረጋገጫ ሰርተፍኬት እንዲይዙ እና የታደሰ ሰርተፍኬት ይዘው ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ ለማስቻል ሥልጠናው ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተመላክቷል። የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት፣ ሥልጠናው የሀብት ምዝገባን አሠራር እና ሕጋዊ ግዴታዎች በግልጽ እንዲረዱ ትልቅ እገዛ እንዳደረገላቸው ገልጸዋል። በተለይም ምን ዓይነት ንብረቶች መመዝገብ እንዳለባቸው፣ የቤተሰብ ሀብት ማካተትና አሞላል ሥርዓትን እና የዲጂታል (EARS) ሥርዓትን በአግባቡ መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ግንዛቤ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ በወቅቱ አለማስመዝገብ የሚያስከትለውን ሕጋዊ ተጠያቂነት እና ቅጣት አስቀድመው እንዲገነዘቡ በማድረግ ረገድ ጠቃሚ ግንዛቤ እንደጨበጡበት አንስተው፣ በቀጣይ ሀብታቸውን በታማኝነትና በግልጽነት ለማስመዝገብ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።

በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ለኢንተርፕራይዙ ሠራተኞች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ነሀሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ግልጽነትን ለማስፈን፣ ሙስናን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ ላይ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በዋናው መሥሪያ ቤት ለሚገኙ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ። በሥልጠናው ግልጽነትን ለማስፈን፣ ሙስናን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መመሪያው ወሳኝ መሆኑን የገለጹት የኢንተርፕራይዙ የስነምግባር መከታተያ ቡድን መሪ ሻለቃ ጌትነት አንዱዓለም ሲሆኑ ሥልጠናው በኢንተርፕራይዙ ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ ሕጎችና አሠራሮች ላይ በቂ እውቀት እንዲኖራቸው እና ምዝገባውን በሚፈለገው ጊዜ ውስጥ ማከናወን እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። በሥልጠናው ወቅት ሀብቱን በወቅቱ ያላስመዘገበ ሠራተኛም ሆነ አመራር አግባብነት ባለው ሕግ መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆን በጥብቅ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል የሀብት ምዝገባ መረጃ ትክክለኝነት ማረጋገጫ እና ለሕዝብ ተደራሽ የሚደረጉ የጥቆማ ሥርዓቶች መዘርጋታቸው ተገልጿል። ሠራተኞች የመንግሥት ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና ሠራተኞች የሀብትና የገቢ ምንጫቸውን በኢንተርኔት አማካኝነት በቀላሉ የሚያሳውቁበትና የሚያስመዘግቡበት ዘመናዊ የዲጂታል ሀብት ምዝገባ ሥርዓት (EARS) ላይ በቂ ግንዛቤ ይዘው በአግባቡ እንዲያስመዘግቡ፣ የማረጋገጫ ሰርተፍኬት እንዲይዙ እና የታደሰ ሰርተፍኬት ይዘው ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ ለማስቻል ሥልጠናው ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተመላክቷል። የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት፣ ሥልጠናው የሀብት ምዝገባን አሠራር እና ሕጋዊ ግዴታዎች በግልጽ እንዲረዱ ትልቅ እገዛ እንዳደረገላቸው ገልጸዋል። በተለይም ምን ዓይነት ንብረቶች መመዝገብ እንዳለባቸው፣ የቤተሰብ ሀብት ማካተትና አሞላል ሥርዓትን እና የዲጂታል (EARS) ሥርዓትን በአግባቡ መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ግንዛቤ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ በወቅቱ አለማስመዝገብ የሚያስከትለውን ሕጋዊ ተጠያቂነት እና ቅጣት አስቀድመው እንዲገነዘቡ በማድረግ ረገድ ጠቃሚ ግንዛቤ እንደጨበጡበት አንስተው፣ በቀጣይ ሀብታቸውን በታማኝነትና በግልጽነት ለማስመዝገብ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም፣ የቀጣይ 5 ዓመታት ስትራቴጂክ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅዶች ላይ ከሠራተኞች ጋር ተወያየ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከ2019 እስከ 2023 በጀት ዓመት የሚተገበረውን አዲስ ስትራቴጂክ ዕቅድ ለሠራተኞቹ ይፋ አድርጓል። ተቋሙ በዚህ አዲስ ስትራቴጂክ ዕቅድ 61.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት እና የፕሮጀክቶችን የጊዜ መዘግየት ምጣኔ ወደ ዜሮ የማውረድ ግብ ሰንቋል። ይህ ዕቅድ ተቋሙን ከዘመኑ የቴክኖሎጂ አቅጣጫ ጋር በማስተሳሰር ተወዳዳሪነቱን ለማረጋገጥ ያለመ ነው። ዕቅዱ የፕሮጀክት ክንውን ብቃትን ማሳደግ፣ የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ፣ የዲጂታል ሽግግርና የሰው ኃይል ልማትን ማፋጠን፣ እንዲሁም የአመራርና አስተዳደር ሥርዓትን ማጠናከር በሚሉ አራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የተመሰረተ ነው። የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የኮርፖሬት ሰርቪስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው በቀለ፤ ለስትራቴጂክ ዕቅዱ ስኬታማነት እያንዳንዱ የሥራ ክፍል ዕቅዱን ለሠራተኞች በማውረድ ሠራተኛን ከሥራው ጋር ማገናኘት፣ እንዲሁም የድጋፍና የቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት ተፈጻሚነቱን መከታተል እንደሚገባ ገልጸዋል። የስትራቴጂክ ዕቅዱን ዋና ዓላማ አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የኢንተርፕራይዙ የእቅድ ዝግጅት መምሪያ ተወካይ ኮሎኔል ምንውየለት አሰፋ፤ ኢንተርፕራይዙ ከመከላከያ ጋር የተቆራኘ የሠራዊት ልማት ድርጅት በመሆኑ፣ ከተሰጠው ተልዕኮ ጋር በሚስማማ መልኩ አጠቃላይ የተቋም ትራንስፎርሜሽን፣ የአሠራር አፈጻጸም፣ የፋይናንስ ሀብት እና የአስተዳደር ጥንካሬን ለመምራት የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መሆኑን አስረድተዋል። በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አዳዲስ ገልባጭ መኪኖችን ገዝቶ ወደ ሥራ አስገባ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ቅልጥፍናና
+2
መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አዳዲስ ገልባጭ መኪኖችን ገዝቶ ወደ ሥራ አስገባ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ቅልጥፍናና ዕድገት ማሽነሪዎች ያላቸው ሚና ከፍተኛ ነው። ይህንን ብሔራዊ ዓላማ በመከተል መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሥራ አገልግሎት የሚውሉ የ2024/2025 አዲስ ሞዴል 20 ዘመናዊ ገልባጭ መኪኖችን ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ገዝቶ ወደ ሥራ አስገብቷል። የኢንተርፕራይዙ የግንባታ መሳሪያዎችና ተሽከርካሪዎች አስተዳደር እና ጥገና መምሪያ ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ሀብታሙ ደሬሳ እንደገለጹት፦ •  በአሁኑ ወቅት የአንድ ገልባጭ መኪና ወርሃዊ ኪራይ እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ሲሆን፣ አዲሶቹ መኪኖች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ በዓመት ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን ያስችላሉ። •  ተሽከርካሪዎቹ በጂፒኤስ (GPS) የታገዘ የደህንነት ቁጥጥርና ክትትል የሚደረግላቸው በመሆኑ የብልሽት ቅነሳ እንዲኖር ያስችላሉ። ግዥው የኢንተርፕራይዙን የመፈጸም አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ ለሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ የደንበኞችን እርካታ እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል። በመጨረሻም ተሽከርካሪዎቹ የሀገር ሀብትም ጭምር በመሆናቸው፣ ምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታቸውን ሳይጨርሱ ለብልሽት እንዳይዳረጉ ሠራተኞችና የሥራ አመራሮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ዜና እረፍት በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የአምቦ ወሊሶ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሰራተኛ የነበሩት አቶ ተሾመ ደምሴ ዳዲ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋ
ዜና እረፍት በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የአምቦ ወሊሶ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሰራተኛ የነበሩት አቶ ተሾመ ደምሴ ዳዲ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች በአቶ ተሾመ ደምሴ ዳዲ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን፡፡ ፈጣሪ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን!

የአዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ ሐምሌ 27ቀን 2018ዓ.ም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሄደ። በምልከታው ላይ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዴር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ እና የኢንተርፕራይዙ የሕንጻ ግንባታ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸናፊ ሐሰን ተገኝተው የፕሮጀክቱ ሥራ አፈጻጸም በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳና በጥራት እየቀጠለ መሆኑን ተመልክተዋል። የኢንተርፕራይዙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቀሪዎቹን ሥራዎች በተያዘለት ጊዜ አጠናቀን ለባለቤቱ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በፍጥነት ጨርሶ ለማስረከብ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቁጥጥርና የማማከር ሥራውን የሚያከናውን ሲሆን፤ የግንባታው ባለቤት ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ነው። የአዋሽ 7 ኪሎ ማሰልጠኛ ማዕከል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ኢንጂነር እሸቱ ታደሰ፣ በግንባታው ሂደት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት፡ በአሁኑ ወቅት የጣሪያ፣ የበርና መስኮት ገጠማ፣ የኤሌክትሪክ፣ የሳኒተሪ እና የመንገድ ሥራዎችን ጨምሮ ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ። የግንባታ ፕሮጀክቱ የሚገኝበት አካባቢ ከፍተኛ ሙቀትና የዲዛይን ማስተካከያዎች ቢኖሩበትም፤ የሥራ ሰዓትን እንደየአየር ሁኔታው በማስተካከል፣ እንዲሁም የሰው ኃይልና ቁሳቁሶችን በማሟላት ሥራው ያለምንም ማቋረጥ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለ4,200 ሰልጣኞች የሚሆን መኖሪያ፣ ለ900 ሰልጣኞች የሚሆን መመገቢያና ዘመናዊ የምግብ ማዘጋጃ፣ 100 የአሰልጣኞች እና 10 የመኮንኖች መኖሪያዎች፣ 8 የቢሮ ሕንጻዎች፣ ሁለገብ መጋዘን፣ መጸዳጃ ቤቶች እና የጥበቃ ቢሮ፣ የግቢ አጥርና በር፣ ለሰልጣኞች የምረቃ አገልግሎት የሚሰጥ መድረክ እንዲሁም ከመሠረተ ልማት ጋር የተያያዙ መንገዶችን ያካትታል።

photo content
+3

የአዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ ሐምሌ 27ቀን 2018ዓ.ም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ። በምልከታው ላይ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዴር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ እና የኢንተርፕራይዙ የሕንጻ ግንባታ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸናፊ ሐሰን ተገኝተው የፕሮጀክቱ ሥራ አፈጻጸም በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳና በጥራት እየቀጠለ መሆኑን ተመልክተዋል። የኢንተርፕራይዙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቀሪዎቹን ሥራዎች በተያዘለት ጊዜ አጠናቀን ለባለቤቱ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በፍጥነት ጨርሶ ለማስረከብ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቁጥጥርና የማማከር ሥራውን የሚያከናውን ሲሆን፤ የግንባታው ባለቤት ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ነው። የአዋሽ 7 ኪሎ ማሰልጠኛ ማዕከል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ኢንጂነር እሸቱ ታደሰ፣ በግንባታው ሂደት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት፡ በአሁኑ ወቅት የጣሪያ፣ የበርና መስኮት ገጠማ፣ የኤሌክትሪክ፣ የሳኒተሪ እና የመንገድ ሥራዎችን ጨምሮ ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ። የግንባታ ፕሮጀክቱ የሚገኝበት አካባቢ ከፍተኛ ሙቀትና የዲዛይን ማስተካከያዎች ቢኖሩበትም፤ የሥራ ሰዓትን እንደየአየር ሁኔታው በማስተካከል፣ እንዲሁም የሰው ኃይልና ቁሳቁሶችን በማሟላት ሥራው ያለምንም ማቋረጥ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለ4,200 ሰልጣኞች የሚሆን መኖሪያ፣ ለ900 ሰልጣኞች የሚሆን መመገቢያና ዘመናዊ የምግብ ማዘጋጃ፣ 100 የአሰልጣኞች እና 10 የመኮንኖች መኖሪያዎች፣ 8 የቢሮ ሕንጻዎች፣ ሁለገብ መጋዘን፣ መጸዳጃ ቤቶች እና የጥበቃ ቢሮ፣ የግቢ አጥርና በር፣ ለሰልጣኞች የምረቃ አገልግሎት የሚሰጥ መድረክ እንዲሁም ከመሠረተ ልማት ጋር የተያያዙ መንገዶችን ያካትታል።

የአዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ ሐምሌ 27ቀን 2018ዓ.ም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አዋሽ ሰባት መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ። በምልከታው ላይ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዴር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ እና የኢንተርፕራይዙ የሕንጻ ግንባታ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸናፊ ሐሰን ተገኝተው የፕሮጀክቱ ሥራ አፈጻጸም በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳና በጥራት እየቀጠለ መሆኑን ተመልክተዋል። የኢንተርፕራይዙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቀሪዎቹን ሥራዎች በተያዘለት ጊዜ አጠናቀን ለባለቤቱ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በፍጥነት ጨርሶ ለማስረከብ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቁጥጥርና የማማከር ሥራውን የሚያከናውን ሲሆን፤ የግንባታው ባለቤት ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ነው። የአዋሽ 7 ኪሎ ማሰልጠኛ ማዕከል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ኢንጂነር እሸቱ ታደሰ፣ በግንባታው ሂደት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት፡ በአሁኑ ወቅት የጣሪያ፣ የበርና መስኮት ገጠማ፣ የኤሌክትሪክ፣ የሳኒተሪ እና የመንገድ ሥራዎችን ጨምሮ ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ። የግንባታ ፕሮጀክቱ የሚገኝበት አካባቢ ከፍተኛ ሙቀትና የዲዛይን ማስተካከያዎች ቢኖሩበትም፤ የሥራ ሰዓትን እንደየአየር ሁኔታው በማስተካከል፣ እንዲሁም የሰው ኃይልና ቁሳቁሶችን በማሟላት ሥራው ያለምንም ማቋረጥ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለ4,200 ሰልጣኞች የሚሆን መኖሪያ፣ ለ900 ሰልጣኞች የሚሆን መመገቢያና ዘመናዊ የምግብ ማዘጋጃ፣ 100 የአሰልጣኞች እና 10 የመኮንኖች መኖሪያዎች፣ 8 የቢሮ ሕንጻዎች፣ ሁለገብ መጋዘን፣ መጸዳጃ ቤቶች እና የጥበቃ ቢሮ፣ የግቢ አጥርና በር፣ ለሰልጣኞች የምረቃ አገልግሎት የሚሰጥ መድረክ እንዲሁም ከመሠረተ ልማት ጋር የተያያዙ መንገዶችን ያካትታል።

የመከላከያ ሠራዊት አባላት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር  የችግኝ ተከላ  አካሂደዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕና የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አመራሮችና ሠራተኞች በ8ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በመሳተፍ የተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞችን በመትከል ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ልማት ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል። ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው የዘንድሮው የክረምት አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መሥሪያ ቤትና የቢሾፍቱ ሞተር ቪሂክልስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ አመራሮችና ሠራተኞች በቢሾፍቱ በተዘጋጀው የችግኝ መትከያ ስፍራ በጋራ በመገኘት አከናውነዋል። በመርሃ ግብሩ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌታቸው ኃይለማሪያም፣ የቢሾፍቱ ሞተር ቪሂክልስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ተክሉ ፀጋዬና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል። በተመሳሳይ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አመራርና ሠራተኞች በዋና መሥሪያ ቤቱ እንዲሁም በተቋሙ በሚያከናውናቸው የግንባታ ፕሮጀክቶች ውስጥ ለአካባቢው የአየር ፀባይ ተስማሚ የሆኑና በረሃማነትን ለመከላከል የሚያግዙ የአትክልትና የፍራፍሬ ዝርያ ያላቸውን ችግኞች ተክለዋል። የተቋማቱ አመራርና ሰራተኞች እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የአካባቢ ጥበቃን ለማጠናከር፣ የደን ሽፋንን ለመጨመር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለመቋቋም እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልጸዋል። ዘገባው የክፍሎቹ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official