en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 280
Subscribers
-124 hours
+107 days
+3530 days
Posts Archive
አጋንንት ሲያወሩ ማዳመጥ እውነት ስህተት ነው? || አንደበትን እንዴት መግራት ይቻላል? || ለክርስቶስ ብለን መተው || አጋንንት በደሞዛችን ሲያደቡ 💥🔥😭🚩 https://youtu.be/oUXYnEfLPVM

«ጠቃሚ ምክር» ◈ በህይወት ጉዞ ላይ አንዳንድ ያላሰብካቸዉ ነገሮች ሊገጥሙህ ይችላሉ፤ ቢያጋጥሙህም ግን እሩጫህን እንዲያደናቅፍብህ አትፈቀድላቸዉ፤ እንደዉም ሀይልና ብርታት እንደሚጨምርልህ አርገህ ቁጠረው። ምን ግዜም "ነገር ሁሉ ለበጎ ነዉ" የሚለዉን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አስብ፤ ይሄን እዉነት መተግበር ስጀምር ምንም አይነት ነገር በህይወትህ ላይ ቢገጥሙህ፤ የብረታት እንጂ ተስፋ የመቁረጥ ስሜትን ከህይወትህ ላይ ጠርገህ ታጠፋለህ፤ ስለዚህ ነገር ሁሉ ለበጎ ነዉ ብለህ አስብ። ◈ ራስህን አትጣል የሚያነሣህ የለምና፤ ጥንካሬህንና አቋምህን አስተካክል በዙሪያህ ዉድቀትህን የሚመኙ አይጠፉምና፤ ለራስህ ቦታ ስጠዉ ያንተዉ ነህና፤ ለራስህ ክብር ስሰጥ ነዉ የሌሎች ክብር የሚገባህ። በህይወትህ ዘመን ታላቅ ሠዉ መሆን ከፈለክ ሞራልህን ጠብቅ ሞራልህን ሊያሣጣህ የሚችሉትን የአሉታዊ ሰዎች ንግግር አታዳምጥ አንተ የምትወድቀዉ ገንዘብ ሣይኖርህ ሲቀር ሳይሆን ሞራልህ ሲወድቅ ነዉና ሞራልህን ሳታስነካ ጠብቅ፤ ሞራልህ የወደቀ ቀን ጉልበት ይከዳሀል፣ ማገናዘብ ይሳንሀል፣ መራመድ ያቅትሀል በመጨረሻም ትወድቃለህ። ◈ አስተዉል! አንዳንዴ ችግሮች ለመጣል ወይም ወድቀን እንድንቀር ብቻ ሳይሆን ያላየነዉን የስኬት ጉዞ ሊያሳየን፤ ከድክመት ይልቅ ጥንካሬን ሊያስተምሩን ነዉና ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ እራሣችንን አጠንክረን ወደ ፊት እንጓዝ። ፍፃሜህ እንዲያምር ራስህን አታመፃድቅ ሁሌም ከስህተትህ ለመማር ፍቃደኛ ሁን ጥፋትህን አሜን ብለህ መቀበልህ ክብርህን የሚጎዳብህ አይምሰልህ። ◈ ሰንደል ሲያቃጥሉት ነዉ የሚሸተዉ ስለዚህ አንተም እኔም አንቺም በችግር ብንፈተንም ያ ማለፊያችን ነዉና ታግሰን እናሳልፈዉ ከዛ ጥንካሪያችንን አጠንክረን ወደ ፊት እንጓዝ ያኔ ራዕያችን እዉን ይሆንና መአዛችን አለምን ያዉዳል። አስተዉል! ህይወት እንዲ ነዉ፤ በቃ! ሁሉንም የኛ ልናደርግ አንችልም! ነፋስን አባሮ እንደ መያዝ ነዉና ሁሉም ነገር የራስህ እንዲሆን ከመድከም ይልቅ ባለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን ሞክር፤ ከአንዱ ምዕራፍ ወደ ሌላዉ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረህም በፈጣሪህም ታመን ከዛም በአምላክህ ደስ ይበልህ በእምነት ኑር። እንድናስተውል ልዑል እግዚአብሔር ዓይነ ልቦናችን፤ ያብራልን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ትርፍ አንጀት፣ የማህፀን ካንሰር እያልኩ ሆዷን አስተለተልኳት ፀሎትና የአጋንንት ውጊያ ከደብተራዎች ጋር ትንቅንቅ #ethiopia #ebs #ንቁ 🔥🚩💥 https://youtu.be/CNvLThhzytI

🔥 የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏🙏🙏 #like #share #Ethiopia
🔥 የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏🙏🙏 #like #share #Ethiopia

ጥይት የማያስመታ ድግምትና መዘዙ || ጸሎትን አቁሞ አጋንንትን መዋጋት | ካልጸለዩ ጵጵስናም አያድንም | የቤተሰብ መተት ሲኖርብን | ቡዳ ዛር ምንድነው? 🚩🔥 https://youtu.be/iLHv2UzTv4w?si=mxUdozaB51YKhAcG

«ካልሰራህ ደሞዝህ እንደሚቆረጥ ሁሉ ካልጸለይክ የበረከት ደሞዝህ ይቆረጣል!» ◈ ሰው በየትኛውም የስራ መስክ ካላጭበረበረ በስተቀር የልፋቱን ዋጋ ነው የሚያገኘው፤ በመንግስትም ይሁን በግል መስሪያ ቤት የተቀጠረ ሰው ከስራው ገበታ ያለ ምክንያት ከቀረ ደሞዙ ይቆረጣል፤ ሲደጋገም ደግሞ ይቀጣል፤ በመጨረሻም ከስራው ይባረራል፡፡ በመንፈሳዊ ዓለምም እኛ የእግዚአብሔር የመንግስቱ ቅጥረኛ ነን፤ ሕጉን እያከበርን በጎ እየሰራን እየጸለይን የምንኖር ከሆነ ከእግዚአብሔር ዘንድ የበረከትና የጸጋ ደሞዝ ይከፈለናል፡፡ ◈ አንድ መንፈሳዊ ሰው በየቀኑ ያለመታከት ጸሎትን እንደ አንድ ስራው በመቁጠር የሚጸልይ ከሆነ በየቀኑ የጸጋ ደሞዙን ከእግዚአብሔር በስውር ይቀበላል፤ ግን ዛሬ ሲመቸው ጸልዮ ነገ ሳይመቸው ሳይጸልይ ከቀረ፤ ጸሎት ያስታጎለበትን እንደምክንያት ቢያቀርብ ያልሰራበትን ደሞዝ ለመቀበል የሚሞክር ሰነፍ ሰራተኛን ይመስላል፡፡ ብዙዎቻችን ጸሎትን እንደ ሁለተኛ ስራ ነው የምናየው፤ ግን ጸሎት ከስራችን በፊት የሚቀድም የውዴታ ሳይሆን የግዴታ መንፈሳዊ ስራችን ነው፡፡ ◈ ዛሬ እንኳን ጸሎት ትተን ተግተን ጸልየንም ችግራችን አልፈታ፣ የመከራችን ማዕበል አልገታ ብሎናል፡፡ ጸሎታችን እንደ ማብራት ዛሬ የሚበራ ነገ የሚጠፋ እየሆነ በረከት አልባ እያደረገን ነው፤ እግዚአብሔር ጸሎትን እንደ ሥራው አድርጎ ለሚቆጥር፤ ቆጥሮም ተግቶ ለሚጸልይ የጸጋ ደሞዙን በእለቱ ነው የሚከፍለው፡፡ ስንቶቻችን ለአንድ ወቅት ጸሎተኛ ሆነን አሁን ጥሩ ሰነፍ ወጥቶን ጸሎት ትተን ከእግዚአብሔር ዘንድ የበረከት የጸጋ ደሞዝ ተቆርጦብናል፡፡ ◈ አንዳንድ ሰነፎች ድክመታቸውን ለመሸፈን ‹‹ለምን እንዳልጸለይኩ እርሱ ያውቃል፤ እርሱ እንደ ሰው አይደለም ችግሬን ይረዳል›› በማለት ከራሳቸው ለማምለጥ ይሞክራሉ፡፡ ጸሎት ባልተመቸ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ መጸለይ በራሱ ጥልቅ ዋጋ አለው፤ አባቶች ‹‹በደህናና በደጉ ጊዜ ሁሉም ጻድቅ ነው›› ይላሉ፡፡ ጻድቅና ጸሎተኛ ሆኖ መገኘት ባልተመቸን ሰዓት ነው፤ በተመቸን በሞላልን ጊዜማ እንኳን ለጸሎት ስመ እግዚአብሔር ለመጥራትም ላይመቸን ይችላል፡፡ ◈ ጌታችን ሰው በመንግስተ ሰማያት ስለሚያገኘው ዋጋ በአትክልት ሠራተኛ ቅጥረኛ መስሎ አስተምሯል፤ የአትክልቱ ባለቤት ሠራተኞችን በአንድ ዲናር ከቀጠረ በኃላ በሦስት ሰዓት ወጥቶ ሲሄድ በአደባባይ ‹‹ሥራ የፈቱ›› በማለት ሌሎች ሰዎችን እንዳገኘ ተናግሯል፡፡ (ማቴ 20÷3) "ሥራ የፈቱ የተባሉት ጸሎት የተዉ ከጽድቅ ስራ የራቁ፣ ንስሐ ያልገቡ ናቸው፤ ባለቤቱም በአደባባይ ያገኛቸውን ‹‹እናንተ ደግሞ ወደ ወይኔ አትክልት ቦታ ሂዱ የሚገባውንም እሰጣቹኃለሁ አላቸው›› በማለት አሰማራቸው፡፡ ◈ በስድስትና በዘጠኝ ሰዓትም ሌሎችን ቀጠረ፤ የማታ ማታ የመጡት የሚቀጥረን አጣን በማለት አቢቱታ ቢያሰሙትም በአስራ አንደኛው ሰዓት ቀጠራቸው፤ ለሁሉም እንደሚገባቸው ደሞዛቸው እንደሰጣቸው ማቴዎስ ይተርክልናል፡፡ (ማቴ 20÷1-16) ዛሬም ክርስቶስ የመንግስቱ ሰማያዊ ሠራተኛ አድርጎ ቀጥሮናል፤ ግን ተቀጥረን የበረከት የጸጋ ደሞዝ መቀበል ስንችል ‹‹ሥራ የፈቱ›› ተብለን ያለ ደሞዝ እንዳንቀር መጸለይ፣ መልካም መስራት፣ በንስሐ ለመንግስቱ መዘጋጀት አለብን፡፡ ◈ በተቃራኒው ጸሎትን ከተውን፣ ንስሐ መግባቱን ቸል ካልን፣ በዓለማዊና በስጋዊ ህይወት ተዘናግተን ከጸጋው ከራቅን ልክ የመንግስት ሠራተኛ ሥራውን በአግባቡ ካልሰራ፤ በተደጋጋሚ ከስራው ገበታ ከቀረ፤ ማስጠንቀቅያውን ካልሰማ፤ ከስራው እንደሞባረር ሁሉ እኛም መንፈሳዊ ሥራችንን ከተውን፤ ከሰማያዊው መንግስት እንባረራለን፤ ስለዚህ ለክርስቶስ ትጉህ የጸሎት፣ የመንፈሳዊ ምግባራት ሠራተኛ እንሁን፤ እግዚአብሔርም ይርዳን፤ የእናቱ የድንግል ማርያም ምልጃ ጸሎቱ ይርዳን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

❖ ጸሎት ኃይል አለው፤ የተቋረጠውን ግንኙነት ያድሳል፤ በበደለኝነት ስሜት ለሚሰቃየው ዕረፍትና እንቅልፍ ይሰጣል፤ ሽፍታው ጭምት፣ ሌባው መጽዋች፣ ዘማዊው የንጽሕና ወዳጅ የሚሆነው በጸሎት መንገድ ተጠቅሞ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል በመቀዳጀት ነው። "ስለዚህ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ" (ኤፌ 6፥18) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

◈ (ሰኔ 4) ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ ሰላምታ ይገባሃል፤ የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጅ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ አቡቀለምሲስ የተባልክ ክቡር ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ የሐዲስ ሥ
◈ (ሰኔ 4) ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ ሰላምታ ይገባሃል፤ የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጅ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ አቡቀለምሲስ የተባልክ ክቡር ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ የሐዲስ ሥርዓት ሐዋርያ ዮሐንስ ሆይ! በቤተ ምንዳድ ለደረሰብህ መከራ ሰላምታ ይገባሀል፤ በትዕግስትህ የሮምንና ቁጣ ችለህ የሞተውንም ያስነሳህ ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ መከራን የምትታገስ ዮሐንስ ሆይ! እንዳንተ ያለ በምድር ላይ ማነው፤ ክብርን የተሞላህ ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ለአንተ ይሁን እያልኩ በምስጋናና በእምቢልታ የቤተክርስቲያን የጉባኤዋ መሪ እነሆ አደንቅሀለሁ፤ በምስጋና እና በማህሌት የመላእክት ወዳጅ የሆንክ እውነተኛ ዮሐንስ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን፤ ዮሐንስ ሆይ! ለሚልህ የመልክህ ደምግባት ምን ያምር፤ የስምህስ አጠራር ምን ይጣፍጥ፤ አራተኛውን ወንጌል የጻፍክ ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ ኮል የተባለ የምስጋናህ መዓዛ በሰው ሁሉ አፍንጫ በጎ በጎ ሸተተ፤ ንስር የተሰኘህ ወንጌላዊው ዮሐንስ ሆይ! ልዑል ከሆነ ከሰማይ ተዋሕዶ ቃል ሥጋ ሆነ፤ በእኛም አደረ እያልክ በረህ ና ና። (መልክአ ቅዱስ ዮሐንስ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

◈ "እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፤ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፤ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፤ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፤ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እን
◈ "እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፤ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፤ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፤ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፤ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እንጂ አይደሰትም፤ እንዲህ ካልሆነ ግን አባቱ ሌላ ነው፤ ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ምስጋና በጊዜውም ያለ ጊዜውም ሊሆን ይገባል፤ ባገኘን ጊዜ ብቻ ሳይሆን ባጣንም ጊዜ፤ ባለጤና በሆንን ጊዜ ብቻ ሳይሆን በታመምንም ጊዜ፤ ሲሳካልን ብቻ ሳይሆን ባልተሳካልንም ጊዜ ማመስገን መለማመድ አለብን፤ የምስጋናችን ምንጭ የሁኔታዎች መለዋወጥ ሳይሆን ስለ አምላካችን ብቻ ሊሆን ይገባዋል፤ ይህን ማድረግ ስንለማመድ በክብር ላይ ክብር ይጨመርልናል፤ እንደ አባታችን ኢዮብ የዲያብሎስን አፍ እንዘጋለን፤ ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፤ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፤ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፤ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፤ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፤ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

መምህር ግርማ ጋር ከሄዳችሁ ትጮሃላችሁ ይላሉ! || በመማር በመንቃት ዲያብሎስን መቃወም || አጋንንት አራት ቦታ በብዛት ያደፍጣል || ተስፋዬ አበራ 😭💥🚩🔥 https://youtu.be/zFhV22X3htc

«ገንዘብ ቦታው የት ነው?» ◈ ወደ ሐዋርያት የአንድነት ማኅበር ይገቡ የነበሩ ሰዎችን በተመለከተ "መሬት ወይም ቤት ያላቸው ሁሉ እየሸጡ የተሸጠውን ዋጋ ያመጡ ነበርና በሐዋርያትም እግር አጠገብ ያኖሩ ነበር" ተብሎ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል። (የሐዋ 4፥34-35) ገንዘቡን ያስቀምጡ የነበረው በሐዋርያት እግር ስር አጠገብ ነበር፣ ምክንያቱም #ገንዘብ #አገልጋይ ስለሆነ ከእግር አጠገብ ሊቀመጥ እንጂ ከጎን አብሮ ሊቀመጥ አይገባውምና፤ ገንዘብ  እንደ አገልጋይነቱ ሊሆን ከሚገባው ከእግር ሥር መሆኑ ቀርቶ ከጎን አብሮ እኩል ካስቀመጡት፣ ከዚያም አልፎ ራስ ላይ ካወጡት፣ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር አምላክነት ጋር የሚገዳደር ጠላት ይሆናል፤ ስለዚህም ገንዘብን በአግባቡ መጠቀም እንጂ ራሱን መውደድ አደገኛ ስለሆነ => "አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለመውደድ ይሁን" ተብለናል። (ዕብ 13፣5) መድሎተ ፅድቅ (ቅፅ 3) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

◈ "ከፊትህ አንድ መመሪያ አስቀምጥ፤ ይህም በመንፈሳዊ ሕይወታህ ውስጥ የምትዋጋው ታላቁ ውጊያ፣ ከራስህ ጋር የምታደርገው ውጊያ ነው፤ ወደ ኅሊናህ የሚገባውን ማንኛውንም ዓይነት ክፉ ፍላጎት ተሸክመኸው አትዙር፤ ልትቆጠብ የማትችል ከኾነ ጉዳዩን ለጊዜው አራዝመው፤ ከዚህ በኋላ ጉዳዩን መላልሰህ ለማራዘም ራስህን አስገድደው፤ በማራዘም ውስጥ የእግዚአብሔር ጸጋ ስለሚጎበኝህ እርሱ ያጽናናሃል... በመንፈሳዊ ትጋትህ ውስጥ ቸልተኝነትህን፣ ግዴለሽነትህን እና ቁም ነገር ማጣትህን የሚገልጹ የተለያዩ ነገሮችን ወደ አንተ እንዲመጡ አትፍቀድ።" (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

መምህር ተስፋዬ ምን ገጠመው? መንፈሳዊ ሰው ማን ነው? አጋንንት ውስጣችን ሲገባ የሚያሳዩት ባሕሪይ ኦርቶዶክሳዊ የጊዜ አጠቃቀም #ethiopia 💥🚩😭 https://youtu.be/DraTiiRuLZw

በወንዶች መለከፍ እወዳለሁ መልፋት ብቻውን አያድንም ኦርቶዶክሳዊ ጊዜ አጠቃቀም እፀ መሰውር ድግምቶች ከአይን የምነሱ የቡዳ መንፈሶች 😱💥😭🚩 https://youtu.be/nfErJ2iXuhA

◈ "ወዳጄ ሆይ መመኘትህ የሥራህ ምትክ አይሁን፤ ስታገኝ ስስታም አትሁን ያለህን በሥርዓት ተጠቀም፣ ከሌለህ አትቆጥብምና እግዚአብሔር እንዲሠራ ከፈለግህ መንገዱን አታስረዳው፤ ሰውነት ሲዋረድ ሁሉም ነ
◈ "ወዳጄ ሆይ መመኘትህ የሥራህ ምትክ አይሁን፤ ስታገኝ ስስታም አትሁን ያለህን በሥርዓት ተጠቀም፣ ከሌለህ አትቆጥብምና እግዚአብሔር እንዲሠራ ከፈለግህ መንገዱን አታስረዳው፤ ሰውነት ሲዋረድ ሁሉም ነገር ክብሩን ያጣል፤ የመሸባቸውን ስታይ ያንተ ምሽት እንደዚህ እንዳይሆን አልቅሰህ ጸልይ የእርዳታ ጸሎት ወደ ፈጣሪህ ስታቀርብ ምጽዋት እየመጸወትህ ይሁን፤ ክፋት ድንበር ካጣ የሚቆመው በሲኦል እሳት ውስጥ ነው ሌላው እንዲኖር ካላደረግህ መኖርህ አጠራጣሪ ነው፤ ስትሰስት አዳምን፣ ስትሰጥ ክርስቶስን ትመስላለህ፤ ገንዘብ የሰጠ ደግ ቢባልም እንደ ዮናታን ዙፋንን የሰጠ ደግ ግን አላየንም፤ የአሁኑ የመጨረሻው ነው ብለህ አታስብ፣ እውነተኛው መጨረሻ በዕለተ ምጽአት ነው።" መልካም ዕለተ ቅዳሜ ይሁንልን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239

◈ ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፤ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፤ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡ ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የግብጻዊው መነኩሴን ምክር ላካፍላችሁ!» ◈ ብዙ ጊዜ በእግረ ስጋው ወደ ቤተክርስቲያን ይመላለስ የነበረ አንድ አማኝ ወደ አንድ አባት ሄዶ ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን መመላለሱ ስሜት አልባ እና ትርጉም የሌለው ነገር እንደሆነበት እየተማረረ እንዲህ አላቸው። “ለ 30 አመታት ያህል ቤተክርስቲያን ተመላልሻለሁ፣ በእነዚህ አመታት ብዙ ጉባኤያትን ተካፍያለሁ፣ ቅዳሴ አስቀድሻለሁ፣ ንስሀ ገብቻለሁ. . . . . . ግን ትርጉም ያለው ነገር የለኝም፣ ካሳለፍኳቸው አገልግሎቶች ውስጥ ትዝ የሚሉኝ ብዙም የሉም፣ እንደ ትዝታ የሚታወሰኝም የለኝም፣ እንደ ብክነት አየዋለሁ . . . .ካህናቱና ሰባክያኑም ያለ ምንም ትርፍ ጊዜያቸውን እያባከኑ ያለ ይመስለኛል. . . . .” ◈ ካህኑ በጥንቃቄ አዳመጡት፤ የብዙ አማኝ ችግርም እንደሆነ አስረዱት፣ ሰይጣን ሆነ ብሎ የቀየሰው ወጥመድ እንደሆነ አስታወሱትና ያለፈውን የህይወት ተሞክሯቸውን እያነሱለት እሱ እንደ ብክነት መስሎት የተመለከተው ነገር ጥቅሙ እንደነበር ነግረውት የእሱ ችግር ሰይጣን ቤተክርስቲያን ባሳለፋቸው 30 አመታት የተጠቀመውን እንዳይመለከት አይኑን ዘግቶት ጉድለቱን ብቻ እያሳየው ተስፋ እያስቆረጠው እንደሆነ ነግረውት የራሳቸውን ተሞክሮ በዘይቤ እንዲህ አሉት። ◈ "ትዳር የያዝኩት የዛሬ 30 አመት ነው፣ ካገባሁ 30 አመት ሞልቶኛል፤ በእነዚህ 30 አመታት ውስጥ ባለቤቴ ከ 32,000 በላይ የምግብ አይነት ሰርታ መግባኛለች፤ ሆኖም ግን አንድም ቀን እነዚህን የምግብ ዝርዝሮች ለአንድ ጊዜም ቢሆን አስታውሻቸው አላውቅም፣ የማውቀው ነገር ቢኖር ግን ይህንን ነው፤ እነዚህ ምግቦች ተንከባክበውኛል፣ በሽታ እንዳያጠቃኝ ተከላክለውልኛል፣ ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ ጥንካሬ ሰጥተውኛል፣ የነቃ አእምሮ እንዲኖረኝ አንቅተውኛል፡፡ ◈ ባለቤቴ ዛሬ በዚህ ጤንነት እንድቆም ያደረገኝን ምግብ ባትመግበኝ ኖሮ በህይወት ባልኖርኩና በሞትኩ ነበር፣ አይነታቸው ትዝ ስላላለኝ ጥቅም የላቸውም ልል ይገባኛልን? ለዛሬ መኖሬ ምክንያት ባለፈው 30 አመታት የተመገብኳቸው ግን አሁን ትዝ የማይሉኝ ምግቦች ናቸው፣ ምግብ ሁሌም አዲስ ነው፣ የምንመገበውም እንደ አዲስ ነውና፤ ባልሞት እንኳን ንቁ ሆኜ ሰው የሚጠቀምበትን አገልግሎት ባላገለገልኩ እንደ አንተ አይነት ያሉትን ባልመከርኩ ነበር።" ◈ ልክ እንዲሁ ላለፉት ብዙ ጊዜያት ወደ ቤተክርስቲያን ሄጄ ባይሆን ኖሮ በመንፈሴ ሞቼ በኖርኩ ነበር፡፡ ዛሬ ቤተክርስቲያንን ተጠግቼ ህይወቴን እንድመለከት ባልሆንኩ ነበር፤ ሌላው ቢቀር እንኳን "ያሳለፍኩት አመታት ብክነት ይሆኑ እንዴ" ያስባለኝ ቤተክርስቲያን መመላለሴ ነው፤ የሰማኋቸው፣ ያነበብኳቸው የቃል ምግቦቹ በዝተው ዛሬ እንድቆም አድርገውኛል፡፡ ◈ ጥቅሜን ማየት ተስኖኝ እንጂ ለካ ዛሬ በመንፈሴ ጤናማ ሆኜ የቆምኩት ባለፉት 30 አመታት የተመገብኳቸው አገልግሎቶች ናቸው፤ የዛሬ 20 እና 25 ዓመታት የተማርናቸውን ትምህርቶች ላናስታውሳቸው እንችል ይሆናል፡፡ ዛሬ መልካም አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት፣ ኃጢአት ስንሰራ የሚገስፅ አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት እዚህ በመመላለሳችን ያገኘናቸው ሀብቶች ናቸው። ◈ ለምንም ወደታች ስትወርድ እግዚአብሔር ለአንድ ነገር ወደ ላይ ያወጣሃል፤ የወረድክ ቢመስልህም አትመን ጌታ ወደ ላይ ለጥቅም ያወጣሃልና፡፡ በቤቱ ያለ ትርፍ እየተመላለስክ ያለህ አይምሰልህ ሽልማት ላይ ደርሰሃልና፤ እምነት የማይታየውን ያያል፣ የማይታመነውን ያምናል፣ የማይቻለውን ይቀበላል፡፡ ◈ ሰይጣን ከቤተክርስቲያን እንድንቀር፣ ፀሎት እርግፍ አድርገን እንድንተው ሲፈልግ ነው ያንን ማድረጋችን ምንም ጥቅም እንደሌለው ደጋግሞ ያሳስበናል፤ በቤቱ መመላለሳችን ግን ጥቅም አለው በረከት አለው፤ ማንም የአንድ ባለፀጋ ቤት ተጋብዞ ሄዶ ሳይበላ ሳይጠጣ ሚመጣ የለም፣ እኛም ከሁሉ የሚበልጠው ባለፀጋው የመድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት (ቤተክርስቲያን) ኑ ብሎ ጠርቶን ሄደን ባዶ እጃችንን ፍፅም አንመለስም፤ ለእኛ አሁን ጥቅሙ ባይታየንም የመንፈስ ቅዱስ በረከት ግን እያደረብን ይሄዳል። በቤቱ ፀንተን ለዘለዓለም እንድንኖር እግዚአብሔር  ይርዳን፤ የእናቱ ምልጃና ጸሎት አይለየን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ሁለት ልጅ (ጽንስ) አጨናግፈያለሁ || ልጆቹን በቡዳ የበላ አባት || ፖርኖግራፍ ያመጣው ጣጣ || የድግምት መጽሐፍ ሲቃጠል | በጸጋው ድነናልና አጋንንት 😭💥 https://youtu.be/UkN0A9-UofQ

«ያልተሰጠህን አትሻ» ◈ የተሰጠህን ጸጋ እንዳታጣ ያልተሰጠህን አትሻ፤ ወደ ጸጋ ወደ ክብር ለመድረስ እግዚአብሔር ቢያበቃህ ያሳየህን እይ ያላሰየህን አያለሁ አትበል፤ አንድም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፣ በተሰጠህ ጸጋ ለእግዚአብሔር ተገዛ፤ ማር አብዝቶ መመገብ እንዳይመች እንደዚህም ሁሉ ያልተሰጠውን መሻት አይገባም አያስመስግንም፡፡ ነፍስ ያልተሰጣትን ጸጋ በመሻት እንዳትደክም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፤ የምታየው ማየት ቢኖር እውነተኛውን ምትሐት ሆኖ ታየዋለህ፤ ሕሊና ያልሰጡትን ጸጋ በመሻት በማውጣት፣ በማውረድ የተሰጠውን ያጣል፡፡ ◈ ሰሎሞን መልካም ነገር ተናገረ ‹‹በሰጡት ጸጋ የማይኖር ሰው ቅጽር የሌላትን አገር ይመስላል›› ብሎ ያን ማንም እየገባ እንዲዘረፈው እሱም የተሰጠውን ጸጋ ያጣል፤ አንተ ብሩህ አእምሮ ሰውነትህን ያልተሰጣትን ጸጋ እንዳትሻ ከልክላት፡፡ ከቁመተ ሥጋ የወጣ አብዝቶ መገበርን ከአንተ አርቅ ያልተሰጠህን መሻት ከአንተ አርቅ፤ ባልተሰጠህና በተሰጠህ ጸጋ መካከል ትሕትናህን፣ ንጽሕናህን መጋረጃ አርጋቸው፤ አንድም በተሰጠህ ጸጋ ላይ ያልተሰጠህን ጋርደው በንጽሕና፣ በትሕትና፣ በልቡናህ የምታስበውን መንፈሳዊ ክብር ታገኛለህ። (ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube