en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 267
Subscribers
+124 hours
+57 days
+2230 days
Posts Archive
ጥያቄ 5፡ ምስጢረ ንስሐ "ለመናፍስት ውጊያ" ያለው ፋይዳ ምንድነው? ሀ) አጋንንት በእኛ ላይ ያላቸውን "የከሳሽነት" መብት ያሳጣቸዋል ለ) ለሰዎች ጥሩ እንድንመስል ያደርጋል ሐ) ወደፊት ኃጢአት እንዳንሠራ ይከላከላል መ) መልሱ አልተጠቀሰም

ጥያቄ 4፡ በጸሎት ጊዜ የሚመጡ ክፉ ሃሳቦችን (ሕዝብረ ሕሊና) ለማሸነፍ የተመረጠው መንገድ ምንድነው? ሀ) ከሃሳቡ ጋር መከራከር ለ) ለምን መጣ ብሎ መጨነቅ ሐ) ሃሳቡን ችላ በማለት (Ignoring) በጸሎት መቀጠል መ) ጸሎቱን አቁሞ መተኛት

ጥያቄ 3፡ አጋንንት ከምንም በላይ የሚፈሩትና ሊመስሉት የማይችሉት መንፈሳዊ ጠባይ የትኛው ነው? ሀ) ጾም ለ) ስግደት ሐ) ትሕትና መ) ጸሎት

ጥያቄ 2፡ ሰይጣን ሰውን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ትልቁና አደገኛው መሣሪያ የትኛው ነው? ሀ) በሽታና ድህነት ለ) ተስፋ መቁረጥ ሐ) ስደትና መከራ መ) ሰዎች እንዲጠሉን ማድረግ

ጥያቄ 1፡ አጋንንት የሰውን የልብ ምስጢርና ሃሳብ በቀጥታ ማወቅ ይችላሉ? ሀ) አዎ፣ ሁሉንም ያውቃሉ ለ) አይ፣ ሃሳብን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው ሐ) የሚያውቁት ሰውየው ሲፈቅድላቸው ብቻ ነው መ) ግማሹን ያውቃሉ ግማሹን አያውቁም

ርኩሳን መናፍስት ውስጣችንንና ዕቅዳችንን እንዳያነቡ ይኼንን አሁኑኑ አድርጉ!! አደገኛው ደብተራና ጠንቋይ ተጋለጠ ጉዱን ተመልከቱ!! https://youtu.be/MZ7v9LC6QxY

ይኼንን ሳታውቁ በጭራሽ በተክሊልና በቁርባን እንዳታገቡ አደራ እላለሁ!! አቡነ ጴጥሮስ ያስተላለፉት ልብ የሚነካ መልዕክት! የቁራአን መምህሩ ወደ ኦርቶዶክስ! https://youtu.be/A28iFcGJ21o

#ይኼንን_ምስክርነት_አንብቡ! => ወንድሜ እኔማ ከ3 አመት በላይ ሆኖኛል ከዚያን በፊት ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ነበርኩ ከሀጥያቴ ብዛት የተነሳ ከዚህ በኋላ ሰው አልሆንም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ሞቴን ስጠብቅ የነበርኩ ሰው ነበርኩ እግዚአብሔር እንዴት አድርጎ ካንተና ከናትናኤል ሰሎሞን በማለዳ ንቁ ቴሌግራም ቻይናል ላይ እንደከተተኝ አላውቅም ብቻ ግን ከአመት በላይ ያንቴን የናቲን የመምህር ግርማን ትምህርት ስከታተል ጨለማው እየተገፈፈ እተዋለሁ ብዬ ያላሰብኩትን ሀጥያት እየተውኩ እሞታለሁ ብዬ ለሁለት ጓደኞቼ ሁሉ የተናገርኩትን ሞት እየረሳሁ። ብቻ አዲስ የሆነ ነገር በውስጤ በቀለ በማለዳ ንቁ ላይ የቅዱስ ቁርባን ዘመቻ የሚል ፅሑፍ ሲለቀቅ ደጋግሜ በጥሞና አነበብኩት ከፍቅር ይጀምርና ንሰሃ ከዚያም ቅዱስ ቁርባን ላይ ያበቃል። እሱን እያነበብኩ ንሰሃ ላይ ስደርስ ንሰሃ መግባት እንዳለብኝ ገባኝ ግን እንዴት አድርጌ? አንደኛ ሰው ሀገር ነው ያለሁት ሁለተኛ ያንን ሁሉ በደል እንዴት አድርጌ እናገራለሁ፡ ሶስተኛ እግዚአብሔርስ ይቅር ይለኛል ብዬ ኡኡ ማለት ጀመርኩ። ምክንያቱም ወንድሜ እንደኔ ወንበዴ በዓለም ላይ የለም በቃ እኔ ነጠላ ለብሼ ከቤተክርስቲያን የማልቀር ሰው ሁሉ እንደሷ ነው እንጂ ጨዋነት እያለ የሚመሰክርልኝ ግን በእግዚአብሔር ፊት እርቃኔን የቆምኩ ወንበዴ!! => በነጠላዬ ስር ዝሙትና ግለ ወሲብን ሸፍኜ እሹሩሩ የምል ወንበዴ ስለሰው ክፉ በማውራት የራሴን ነውር የምሸፍን ወንበዴ! እና እንዴት ሀጥያቴን ልናዘዝ አሁን እንደ ድሮ ግማሽ ተናግሬ ግማሽ መደበቅ የለም ምክንያቱም አሁን በእናንተ ትምህርት ውስጥ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር ተፋጥቻለሁ የበደልኩት እሱን ነው። እራስሽን ለካህን አሳይ ብሎኛል ስለዚህ ምን ላድርግ? የሚገርመው በፊት በሰራሁት ሀጥያት አለቅስ ነበር አሁን ደግሞ እንዴት ልናዘዘው እያልኩ እንባዬ እንደጎርፍ ይወርድ ነበር። እንድህ እየተጨነኩ ሳለሁ የሆነ ፅሑፍ ስለ ንሰሃ ለቀቅህ ፅሑፉን በውል ባላስታውስም ፆም እየገባ ስለ ነበር ንሰሃ ከልገባችሁ ፆማችሁም ጸሎታችሁም ስግደታችሁም ጥቅም አልባ ነው የሚል ይዘት ያለው ነበር። ከዛ ነው እንግድህ ኮመንት ስር ንሳሃ መግባት ፈልጋለሁ ስልህ በውስጥ አውሪኝ ብለህ ንሳሃ አባት ቁጥር የሰጠህኝ ሀጥያቴ እኮ ብዙ የሚነገር አይደለም ስልህ በዛ ላይ የረሳሁትስ ስልህ በወረቀት ፃፊው ደግሞ ከመናገር መስራት ይከብዳልና ተናገሪው አልከኝ። እኔም እንደምንም ብዬ ሀጥያቴን ከተናዘዝኩ በኋለ ውስጤ ጸጥ አለልኝ በፊት አባታችን ሆይ ስል አታፊሪም እንዴ ደግሞ እግዚአብሔርንም እንደ ሰው ልትሸውጂ ነው? ደግሞ አባቴ ትለዋለች እንዴ እያለ ይሟገተኝ የነበረው ውስጤ ሰላም ሆነ ቀኖናዬን ጨረስኩ ወንድሜ ስልህ ብያንስ አንዴ እንኳን ቁረቢ እህቴ አልከኝ ነገር ያለሁበት ቤተክርስቲያን ስላልነበር ኢትዮጵያ ገብቼ ቆረብኩ ይሀው ከ3 አመት በላይ ሆነኝ ብዙ ፈተና ቢኖርም ሁሉም እያለፈ እኔ ግን ሀጥያተኛ ወንበዴን የማይንቅ እውነተኛ ወዳጅነቱ እያስደመመኝ እስከ ዛሬ አለው ለዚህ ጽናት ደግሞ ያበቃኝ ያንተ የናቲና የመምህር ግርማ ትምህርት ነው። አሁን ያሉት መንፈሳዊ ውጊያ ላይ የሚሰሩ ወንድሞች ሳይመጡ በፊት እናንተ ነበራችሁ የሚገርመው እስካሁን ከናንተ ውጪ የማንንም አልከታተልም ትምህርታችሁ ፍሬ አለው ወንድሜ እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ። ክብር ለኢየሱስ ክርስቶስ ለአማኑኤል ይሁን በእውነት።

"እንዲህም አለ ወገን! ንቁ" ልጁ እንደ ነገረኝ ከሆነ ለመቁረብ ካሰበ ቆይቷል ልብስ ሁሉ ገዝቶ እራሱን አዘጋጅቶ ነው ያለው ለትንሳኤ ትቆርባለህ ብለው ደስ ብሎኝ አልተፈቀደም ብለው ከለከሉኝ አለኝ ከዛም ለዳግመ ትንሳኤ አሉኝ አሁንም አልተፈቀደም አሉኝ አሁን ስደውልላቸው ቆይ ሌሎች የሚቆርቡ ሰዎች ጠብቀህ ትቆርባለህ ይሉኛል አረ እኔ ከሌሎች ሰዎች ህይወት ጋር ምን አገናኘኝ እኔ ልቁረብ ስላቸው የማይሆኑ ነገሮችን ያወሩልኛል አለኝ። እኔ ደግሞ አንተ አታስታውሳውም ይሆናል ግን አንተ ነበርክ ንሰሃ አባት ሰጥተህ ንሰሃ እንድገባ አድርገህ ለቁዱስ ስጋውና ደሙ ያበቃህኝ ወንድሜ ለዚህ ነው ወዳንተ የመጣሁት አሁንም ቢያንስ እዛ ምታውቀው ሰው ካለህ ቢተዋወቁ ቢዬ አስባለሁ። አሁንም አንዳንድ አባቶች ሰዎች እንዳይቆርቡ የተለያዩ ነገሮችን በማቅረብ ሰዎችን ከሥጋውና ደሙ ያርቃሉ ብቻ እግዚአብሔር ይርዳን። አሁን ምን ይባላል? አሳባችሁን በኮሜን ጻፉልኝ!

=> ይህ ጥያቄ በወንጌል ቃልና በቤተክርስቲያን ትምህርት መሠረት ጥልቅ ምላሽ የሚያስፈልገው ነው። በምስሉ ላይ ላለው ጥያቄ ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ እንደሚከተለው ይቀርባል፦ በመጀመሪያ፣ አንድ መሠረታዊ ነጥብ ማረም ያስፈልጋል፦ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ "መለኮት" አይደለም፤ መለኮትነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው እግዚአብሔር (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ብቻ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ ግን ከሰው ልጆች መካከል የተመረጠ ሰው፣ ነቢይ እና ሐዋርያ ነው። ጥያቄውን "ዮሐንስ መጥምቅ ይህን የመሰለ ታላቅ ብርሃንና ቃል ከየት አገኘው?" በሚል መልኩ ለጠየቀው ሰው የሚከተሉት ነጥቦች ምላሽ ይሆናሉ፦ => ምንጩ እግዚአብሔር ነው (መለኮታዊ ተልእኮ)፦ ዮሐንስ መጥምቅ ቃሉንና ስልጣኑን ያገኘው ከራሱ ሳይሆን ከላከው ከእግዚአብሔር ነው። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ይላል፦ "ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ" (ዮሐ 1፡6)። ስለዚህ የዮሐንስ ብርሃን "የባሕርይ" ሳይሆን "የጸጋ" ብርሃን ነው፤ ምንጩም እግዚአብሔር ነው። => ከመጸነሱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ነው፦ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለአባቱ ለዘካርያስ ሲያበስረው፦ "ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል" ብሎ ነበር (ሉቃ 1፡15)። ዮሐንስ ወንጌልን የሰበከውና ዓለምን ያበራው በውስጡ በነበረው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንጂ በራሱ ጥበብ አይደለም። => እርሱ "ለብርሃኑ" ምስክር እንጂ ብርሃኑ አይደለም፦ መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር፦ "ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ እርሱ ብርሃን አልነበረም" ይላል (ዮሐ 1፡8)። ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ "የእግዚአብሔር በግ" የተባለውን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለዓለም ለማስተዋወቅ የመጣ "አዋጅ ነጋሪ" ነው። ጌታችንም ስለ ዮሐንስ ሲመሰክር "እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ" ብሎታል (ዮሐ 5፡35)። => የመንገድ ጠራጊነት (የቀዳሚነት) ጸጋ፦ ዮሐንስ መጥምቅ ከእግዚአብሔር የተሰጠው ልዩ ስልጣን "መንገዱን ማስተካከል" ነው። ነቢዩ ኢሳይያስ "የአዋጅ ነጋሪ ቃል" (ኢሳ 40፡3) እንዳለው፣ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን መጨረሻና የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ በመሆን የክርስቶስን ወንጌል መንገድ ጠርጓል። => ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓለምን ያበራው፦ ከእግዚአብሔር ስለተላከ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስለተመራ፣ ለእውነተኛው ብርሃን (ለክርስቶስ) ምስክር በመሆኑ ነው። ዮሐንስ ራሱ እንደተናገረው "እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ይገባኛል" (ዮሐ 3፡30) በማለት የክብር ምንጩ ክርስቶስ መሆኑን መስክሯል። ስለዚህ ዮሐንስ መጥምቅ የብርሃን ምንጭ ሳይሆን፣ የብርሃን ምንጭ የሆነውን አምላክ ያሳየ መለኮታዊ "መብራት" ነው።

ችግሮቻችሁ በጠንቋይና በጸበል ካልተፈታ እኛ ሳይኮሎጂስቶች እንፈታላችኋለን!! ከአጋንንትና እስራትና ከደዌ ለመፈወስ የሚረዳ ጬሌና አቴቴ! ሱፍ የለበሱ እብዶች! https://youtu.be/dKTt4WiCXmc?si=oUvt4DiVSo1XH_K1

መምህር ግርማ ወንድሙ ያስተማሩን እጅግ አስገራሚ ትምህርት!! መንፈሳዊ ቤት ለመሆን እንዴት እንሰራ? የዲያብሎስን ሴራ በመረዳት መንፈሳዊ ህይወትን መገንባት!! https://youtu.be/3mTnavPH6UE

የሰሎሞን ጥበብ እያላችሁ የተጃጃላችሁ ይኼንን ጉድ ተመልከቱ!! ማንያዘዋል እሸቱ ዛሬም ደገመው የመተቱ ጉዳይ!! እግዚአብሔር አጥብቆ የሚጠላቸው 6 ነገሮች!! https://youtu.be/GOhPL-Z9bbA

ጥያቄ፡ በበዓለ ኀምሳ ስግደት እንደማይፈቀድ ያዝዛል። የጸሎት ስግደትንም ጨምሮ ነው? ጸሎት አድረስን መስገድ አይቻልም? መልስ፦ የጸሎት ስግደት በማንኛውም ቀን የሚሰገድ ነው። እሑድ ቀንም ወደ ቤተክርስቲያን ስንገባ ሦስት ጊዜ ሰግደን እንገባለን። ጸሎት ስንጀምርም ሦስት ጊዜ ሰግደን እንገባለን። የተከለከለው ንስሓ ተቀብለን የምንሰግደው የቀኖና ስግደት ነው።

ጥያቄ፡ ከትንሣኤ በኋላ በበዓለ ኀምሳ ጊዜ አርብም፣ ረቡዕም በማንኛውም ጊዜ የፍስክ ምግቦች ይበላሉ። ምክንያቱ ምንድን ነው? መልስ፦ ዘመነ ትንሣኤ (በዓለ ኀምሳ) በመንግሥተ ሰማያት ለምንኖረው ኑሮ ምሳሌ ነው። በመንግሥተ ሰማያት ደግሞ ድካም፣ ኀዘንና የመሳሰሉት ነገሮች የሉም። ፍጹም ዕረፍት፣ ፍጹም ደስታ አለ እንጂ። ፋሲካ ደግሞ በግ አርዶ ከመብላት ጋር የተያያዘ ነው (ዘፀ.12፥21)። ይህም በሀገራችን የደስታ መግለጫ ሆኖ የኋላውን ፍጹም ዕረፍት እናስብበት ዘንድ ይደረጋል።

ጥያቄ፡ እንደየ አካባቢው የተለያየ ባህል ይኖራል። በመሆኑም ባህሉን እንደ ሃይማኖት በመቁጠር የሚከናወን ድርጊት ስለሚኖር መለኪያችን ምን ይሁን? መልስ፦ የባህል መለኪያው ሃይማኖት (ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ) ነው። አንድ ባህል ሃይማኖታዊ አስተምህሮን እስካልተቃወመ ድረስ ሊነቀፍ አይችልም። በሀገራችን ያሉ ባህሎች ብዙዎች ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ጋር የሚመሳሰሉ ደጎች ናቸው። አንዳንድ ባህሎች ግን ከሃይማኖት የሚቃረኑ ሆነው ሲገኙ መቃወም ይገባል።

ጥያቄ፡ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ ነው እንላለን። ነጻነት ራሱ ምንድን ነው ከምርጫ በምን ይለያል? ፍጹም ነጻነትስ አለወይ? እና እንደዚህ ከሆነ ሰው በነጻነቱ ውጤት ለምን ይጠየቃል? መልስ፦ ነጻነት ማለት አንድን ነገር የማድረግና ያለማድረግ ሙሉ ሥልጣን መኖር ማለት ነው። ይህ ሲሆን ግን በማድረጉና ባለማድረጉ ምክንያት የሚገኘው ውጤት ኀላፊነትንም ያካተተ ነው። አንድ ሰው የመብላት ነጻነት አለኝ ብሎ አብዝቶ ቢበላና ቁንጣን ቢይዘው ተጠያቂው ራሱ ነው። "ጽጋብ ያመጽእ ግብረ ድንጻዌ፣ ወድንጻዌ ያፈደፍድ ደዌ" እንዳለ ባለቅኔ። የሰው የነጻነቱ ውጤት ባለቤቱ ራሱ ስለሆነ መጥጠየቁ አግባብ ነው። ሰው የፈለገውን የማድረግ ሙሉ ነጻነት አለው። ሁሉንም ለማድረግ የሚያስችል ባሕርይ ግን የለውም። በተፈጥሮው ወሰን ያለበት ነውና።

ጥያቄ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሳትን ሲያወጣ በሲኦል የቀሩ ነፍሳት አሉ ወይስ የሉም? እነ ፈርኦን እና እነ ሄሮድስ የት ናቸው? ገነት ወይስ ሲኦል? መልስ፦ በዚህ ዙሪያ ሁለት እይታዎች ይነገራሉ። እነዚህ ሰዎች አልወጡም የሚሉ አሉ። መነሻቸው በመቅድመ ወንጌል ወኀደጎሙ ለእኩያን የሚለው ቃል ነው። በብዙዎች ዘንድ የሚታመነው ግን ማንም ሰው አልቀረም ሁሉም ሰው ከሲኦል ወደገነት ተመልሷል የሚለው ነው። ወኀደጎሙ ለእኩያን የሚለውንም በስመ ኀዳሪ ይጼዋዕ ማኅደር በሚለው አግባብ በነፈርዖን አድረው ክፉ ያሠሯቸው አጋንንት አልወጡም ለማለት እንጂ ራሳቸው እነፈርዖን አልወጡም ማለት አይደለም ብለዋል።

ጥያቄ፡ ንስሐ ድንግል ያልሆነችውን ወደ ድንግልና ትመልሳለች ተብሎ ተጽፏል። ስለዚህ አንድ ካህን ቢሳሳት እንዴት በንስሓ ወደ ክብሩ አይመለስም? መልስ፦ ንስሓ ድንግል ያልሆነውን ወደ ድንግልና ትመልሳለች የሚለው ስለነፍስ ድንግልና የተነገረ ነው እንጂ ስለሥጋ ድንግልና የተነገረ አይደለም። ነፍስ ኃጢአት ስትሠራ ድንግልናዋን አጣች ትባላለች። ንስሓ ስትገባ ደግሞ ድንግልናዋ ተመለሰ ይባላል። አንድ ካህን ከሌላ ሴት ቢደርስ ክህነቱ ይፈርሳል። ንስሓ ገብቶ ኃጢአቱ ይቅር ስለሚባል ነፍሳዊ ክብሩን መመለስ ይችላል። ክህነታዊ ክብሩ ግን በንስሓ አይመለስም።