en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 277
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+2930 days
Posts Archive
◈24ቱ ካህናተ ሰማይ 🙏 ◈ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ መታሰቢያ በዓላቸው ነው ህዳር 24። አንዚህንም እግዚአብሔር ከሠራዊተ ሩፋኤል ሃያ አራት ሊቃናትን መርጦ በመንበረ ስብሐት በመጋረጃዋ ውስጥ ዙሪያዋን ክንፍ ለክንፍ ገጥሞ አስቀምጧቸዋል። ስማቸውንም ካህናተ ሰማይ አላቸው። የእሳት፣ የወርቅ ጽንሐ አስያዛቸው። የብርሀን አክሊል ጳዝዮን ከሚባል የብርሀን ዘውድ ደፋላቸው። የብርሀን ዘንግ ማኅተሙ መስቀል የሆነ አስያዛቸው። የብርሀን ካባ ላንቅ ኅብሩ መብረቅ የመሰለ አለበሳቸው። እነዚህም በአንድ ላይ በዓጠኑ ጊዜ ከማዕጠንታቸው የሚወጣው ጢስ መልኩ መብረቅ፤ ድምጹ ነጎድጓድ፤ መዓዛው መልካም የሆነ ነው። (መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሁድ) ◈ "በዙፋኑም ዙሪያ ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ። በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም ላይ የወርቅ እክሊል ደፍተው ሃያ አራት ካህናት ተቀምጠው ነበር።" (ራዕ.4፥4-5) ◈ "ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጽንሐ ይዞ በመሠዊያው አጠገብ ቆመ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሠዊያ ላይ ለቅዱሣን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው፤ የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሣን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።" (ራዕ 8፥3-5) 24ቱ ካህናተ ሰማይ 1.አካኤል 2.ፋኑኤል 3.ጋኑኤል 4.ታድኤል 5.አፍድኤል 6.ዘራኤል 7.ኤልኤል 8.ተዳኤል 9.ዮአኬል 10.ገርድኤል 11.ልፍድኤል 12.መርዋኤል 13.ኑራኤል 14.ክስልቱኤል 15.ኡራኤል 16.ባቱኤል 17.ሩአኤል 18.ሰላትኤል 19.ጣውርኤል 20.እምኑኤል 21.ፔላልኤል 22.ታልዲኤል 23.ፐሰልዱኤል 24.አሌቲኤል። ምንጭ:-ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው ገጽ 149 በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ። ◈ ዳግመኛም በዚህ ዕለት ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለሐይማኖት ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ሆነው የሥላሴን መንበር ያጠኑበት መታሰቢያ በዓላቸው ነው። የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሐይማኖት አንዲሁም የካህናተ ሰማይ ረድኤት በረከታቸው በአማላጅነታቸው ከምናምን ከሁላችን ጋር ይሁን። #ሠዓሊ_ቀሲስ_አማረ_ክብረት #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

3.48 MB

🙏 ይሄው ምርቃታችሁን ተቀበሉ በዚህ የበረከት ሥራ የተሳተፋችሁ ቤተሰቦቼ በሙሉ በእውነት እንዲህ መተጋገዝ ለሁላችንም ያስፈልጋል። እህታችንን በአካል አግኝቼያት ብዙ ነገሮችን ተመካክረን ተለያይተናል። በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለባት ተወያይተን አቅጣጫ አስቀምጠን ማለት ነው። ውድ ቤተሰቦቼ በዚህ በመናፍስቱ ዓለም ከገዛ ቤተሰቦቻችን የሚመጡ ፈተናዎች እጅጉን ከባድ ናቸውና ሁላችንም እርስ በእርሳችን መተጋገዝ፣ መጀጋገፍ ያስፈልጋል እና በርቱልኝ። ቤተሰቦቼ አሁንም በበረከት ሥራ መሳተፍ የሚትፈልጉ በእውነት አናግሩኝ ዛሬ እንደውም ማምሻውን አከባቢ አንድ ኤርትራዊት እናት አግኝቸያት ብዙ ነገር አወራን እና ከገረመኝ ነገር ለእምነቷ፣ ለእምዬ ተዋህዶ ያላትን ቁርጥ አቋም ያየሁበት ቀን ነበር። ነገር ግን ያለችበት ሁኔታ በጣም ከባድ ነውና በእውነት ይሄን መልእክት ያያችሁ ሁላችሁም እናግዛት እላለሁኝ። በርቱ፣ ጠንክሩ እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን። 🙏🙏

◈ ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ
◈ ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል። 🙏🙏🙏 #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

"በተጠመቁ ሕፃናት ላይ መናፍስት እንዴት ይዋረሳሉ? እንዴት ይይዛል የሁሉም ጥያቄ? ◈ ብዙ ሰዎች በርዕሱ በተጠቀሰው ጉዳይ ላይ ግራ ይጋባሉ፡፡ በ40 እና በ80 ቀን ተጠምቀን የሥላሴ ልጅነትን በማየ ጥምቀት አግኝተን፤ ክቡር ሥጋውን ቅዱስ ደሙን በመውሰድ በሰማያዊ ማኅተም ታትመን ሳለ፤ መናፍስት በምን ሥልጣናቸው ከዘር ወደ ዘር (ከአባት ከእናት) ሊዋረሱ ይችላሉ? የሚለው ጥያቄ ብዙዎች ዘንድ ያለ ነው፡፡ በእርግጥም ዳግማዊው አዳም ክርስቶስ በመስቀል ባንቀላፋ ጊዜ ከጎኑ የወጣቺው (ደምና ውኃ) ስብዕናይቱ ቤተክርስቲያን ሰማያዊት ሔዋን ሆና ከጌታ ጋር በምትፈጽመው ረቂቅ ጋብቻ ምዕመናንን ዳግም ወልዳ ከማይጠፋው ዘር ትቀላቅላቸዋለች፡፡ ◈ ዳግም የመወለድ ሕግም ያስፈለገው፤ በመጀመሪያይቱ ሔዋን ፊት የቆመው እባብ የሰውን ልጅ በልቶ፤ በሕይወቱ፣ በእውቀቱ፣ በትውልዱና በባሕሪይው እየገባ የራሱ ያደርገው የነበረበትን ውድቀት ለመሻር ነው፡፡ በአጭር አነጋገር ዲያቢሎስ በዘራችን እየዘለቀ እያጠፋ የመጣበትን የሥጋ አወላለድ ለመለወጥ ነው፡፡ ◈ ችግሩ ግን እኛ ነን፡፡ ይህንን መንፈሳዊ ኃይልና አንድምታ በሙሉ ክብሩና እውነቱ አላስተናገድነውም፡፡ ባሕል፣ ይስሙላ፣ የግዴታ ውዴታ አደረግነው፡፡ የትኛው ወላጅ ነው በእውን ልጄ ከእግዚአብሔር አብራክ ይወለድልኛል በሚል የዋህ እምነት ክርስትና የሚያስነሣው? ግዴለም ይህንን እንተወው፡፡ ጌታ ገር ነውና፥ አለማመናችንን እየረዳ ልጆቻችንን በመንፈሱ ይወልዳቸዋል፡፡ መናፍስቱ ግን በዘር መወራረሳቸውን እንዳያቆሙ ያደረጋቸውን ምክንያቶች ግን አላስወገድንም፡፡ ማለትም ከመውለዳችን በፊት ንስሐ አልገባንም፤ በቅዱስ ቁርባን አልተቀደስንም (ስለዚህ በኛ ውስጥ ያሉት መንፈሶች ለምን ይሽሹ?) ◈ በቤተሰብ ታሪክ ሲመለክ፣ ሲገበርለት የቆየውን ባዕድ አምልኮት አልተላቀቅንም፣ አልሰበርንም፣ አልጣልንም፣ አላስቆምንም፣ አልተዋጋንም (ስለዚህ ዘሬ ናቸው ብሎ በኩራት ዙፋኑን አስፍቶ የተቀመጠው የጣዖት መንፈስ ለምን ይራቅ)። ስለምንወልደው ልጅ አልጸለይንም፣ ሱባዔ አልጠየቅንም፣ ምንም መንፈሳዊ ቅደመ ዝግጅት አላደረግንም (ጨርቃ ጨረቁን፣ አልጋውን፣ የቤት ዕቃውን እንጂ የሃይማኖት ቀልብ አልገዛንም፡፡ ◈ የምንወልደው ልጅ ነፍስ ያለው የሰው ፍጡር እንደሆነ ዘንግተን ለሥጋ ለሥጋው ብቻ የሚያስፈልገውን ነው አሟልተን የምንጠብቀው፡፡ ስለዚህ "ከአንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" የሚለው የሐዲስ ኪዳን ቃልኪዳን እንዴት አድርጎ ወደኛ ይድረስ ቤተሰቦቼ) ◈ እግዚአብሔር ይማረን የተባረከ ትዳር፣ የተባረከ ልጅ እግዚአብሔር እንድሰጠን እኛ ታዲያ ቀድሜን #ንስሐ ገብተን #በቅዱስ #ሥጋውና #ደሙ ታትመን ለመንግስተ ሰማያት እንድንበቃ የዓለማት ሁሉ ፈጣር የድንግል ማሪያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን። በርቱ፣ ጠንክሩ 🙏🙏 #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

20231202_131738.aac2.58 KB

🙏 ዛሬም በድጋሚ የበረከት ሥራችን ቀጥሏል። እህታችን ሁለት ልጆችን በዚህ ሥራ እየተሯሯጠች ታሳድጋለች። ባለበቷም በህመም ምክንያት ብዙ ይፈተናል ቢሆንም ግን ተስፋ ሳይቆርጡ ይታገላሉ። ወንድማችን
🙏 ዛሬም በድጋሚ የበረከት ሥራችን ቀጥሏል። እህታችን ሁለት ልጆችን በዚህ ሥራ እየተሯሯጠች ታሳድጋለች። ባለበቷም በህመም ምክንያት ብዙ ይፈተናል ቢሆንም ግን ተስፋ ሳይቆርጡ ይታገላሉ። ወንድማችን ተስፋ ከሜሪላንድ በላከው ገንዘብ ይህችን እህታችንን የቤት ኪራይና የቤት ወጭዎችን ችለናል። እግዚአብሔር በወጣ ይተካልህ። መላው ቤተሰብህንም እግዚአብሔር ይጎብኝልህ። ብያለሁ። 🙏🙏🙏

◈ ለሰዎች ከልቡ ራርቶ የሚጸልይን ሰው እግዚአብሔር ይበልጡኑ ይከተለዋል፡፡ ለምን ሲባል፤ የራሱ የክርስቶስን ሥራ፣ የጻድቃንን ሥራ፣ የመልአክትን ሥራ የሚሠራ ሰው ስለሆነ፤ መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ላይ
◈ ለሰዎች ከልቡ ራርቶ የሚጸልይን ሰው እግዚአብሔር ይበልጡኑ ይከተለዋል፡፡ ለምን ሲባል፤ የራሱ የክርስቶስን ሥራ፣ የጻድቃንን ሥራ፣ የመልአክትን ሥራ የሚሠራ ሰው ስለሆነ፤ መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ላይ በኃይል ለመገለጥ ፈቃደኛ ነው፡፡ ለወገኖቻችን እንጸልይ! የበረከት ሥራ እንሥራ! የወደቁትን በምንችለው ልክ እንደግፍ! እዚህኛው ጋራ ሰዎች በምትችሉት ልክ እርዱ ሲባሉ ካላቸው ላይ ትንሹን ይሰጣሉ፡፡ መስጠቱ በራሱ ምንም ያህል ይሁን መልካም ቢሆንም፤ ወደን በእግዚአብሔር ፊት ስንሰጥ ግን በእውነተኛው አቅም ልክ ልንሰጥ ይገባል፡፡ ከምትችለው አቅም አሳንሰህ አትስጥ፡፡ መስጠትን ቃየንም አቤልም እንደሰጡ አስብ፡፡ ግን አቤል ካለው ላይ በአቅሙ ልክ መርጦ ሰጠ፡፡ ዐሥራት በኩራት አወጣ ማለት ነው፡፡ ቃየን ከሚችለው አሳንሶ አስረከበ፡፡ ዐሥራት አወጣ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ስንሰጥ፤ እውነት ከልባችንና ከጥጋችን ልክ የሰውን ችግር ለመቅረፍ ዓላማ አድርገን እንስጥ ብቻ .. የቀረውን ጎዶሎ ጥበበኛው አባት ይሞላል፡፡ በርቱ፣ ጠንክሩ 🙏 ◈ በቤረከት ሥራ ለመሳተፍ በዚህ ያናግሩኝ Telegram: @haile_gebriel_tube_bot #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑በዲያብሎስ እስራት ተይዞ በደመነፍስ የሚጓዘው ትውልድ አያሳዝንም? ከእውነታው እስከመቼ እንሸሻለን ወገን? ታመናል በእውነት በጽኑ ታመናል 🙏😭😰 https://youtu.be/rnsWZlds8is

"የአምላክ እናት መሆን ትልቅ ሥራ ነው" ◈ የማርያም ጸሎት (ጸሎተ ማርያም) ሁልጊዜም፣ በሁሉም ሥፍራ፣ ለሁሉ የሚጸለይ ታላቅ ጸሎት ነው፡፡ ለመንገደኛው፣ ለሚሾመው፣ በአልጋ ላይ ላለው ሁሉ የሚጸለየው ጸሎት ይህ የማርያም ጸሎት ነው፡፡ ሹማምንት ፊት አይተው እንዳያደሉ፣ ጉቦ ተቀብለው ፍርድ እንዳያጣምሙ የሚጸለይላቸው ጸሎት ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም ነው፡፡ ሰዎች ለሰዎች እንዲያዝኑና እንዲራሩ የሚደገምላቸው ይኼ ጸሎት ነው፡፡ ዛሬ በዓለም ያሉ መሪዎች ክፉዎችና ጨካኞች የሚሆኑት ጸሎተ ማርያም ስለማይደገምላቸው ነው፡፡ ◈ ለተሾመውና ለተሻረው፤ ለሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ለሆነው ሰው ጸሎተ ማርያም የምስክር ወረቀት ዲፕሎማ ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎትዋ እግዚአብሔርን ነው ያመሰገነችው፡፡ ደስታዬ እግዚአብሔር ነው አለች፡፡ ደስታ በኃይል ወይም በጉልበት አይገኝም፤ ከእግዚአብሔር እንጂ፡፡ ደስታ ከሁሉ ነገር ስለሚበልጥ ሁሉ ሰው ሊደሰት ይፈልጋል፡፡ ሊደሰት የሚችለው ግን በእግዚአብሔር ሲያምን ነው፡፡ በዓለም ውስጥ ብዙ ብልጭልጭ ነገሮች አሉ፡፡ የሚያመጡት ጣጣ ግን ብዙ ነው፡፡ ◈ ሰው ከሀብት የተነሣ የገዛ ወገኑንና ዘመዱን ሁሉ ይጠላል፡፡ መደሰት የሚቻለው አንድዬን ሲወዱና እርሱን ሲያምኑ ነው፡፡ እናታችን ነፍሴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል አለች፡፡ እኛስ በምንድን ነው ደስ የሚለን? በሀብት፣ በሥልጣን፣ በዕውቀት፣ በወገን መመካት ነው ደስ የሚለን ወይንስ በእግዚአብሔር? ደስታ፣ ተድላ፣ ፍስሓ እርሱ ነው፡፡ የእመቤታችን ጸሎት ታላቅ ጸሎት ነው፡፡ ከእንግዲህ በኋላ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ ማኅደረ መለኮት ሆናለችና ትውልድ ሁሉ ብፅዕት፣ ንዕድ፣ ክብርት ይሉኛል አለች፡፡ ‘ታላቅ ሥራን ሠርቶልኛልና’ ነው ያለችው፡፡ የአምላክ እናት መሆን፤ ወላዲተ አምላክ መሆን ታላቅ ሥራ ነው፡፡ ሁሉ በረከሰበት፣ ሁሉ በተዳደፈበት፣ ሁሉ በተላለፈበት ሰዓት የአምላክ እናት መሆን በእርግጥም ታላቅ ሥራ ነው፡፡ ◈ የአዳም ዘር በሙሉ ያመሰግኑኛል ነው ያለችው፡፡ ዛሬ እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን ብዙ ሥራዎችን ይሠራልናል፡፡ ነገር ግን ሠርቶልናል፣ ሠርቶልኛል አንልም፡፡ እንደ እመቤታችን አናመሰግነውም፡፡ ቆመን እንድንሔድ ማድረጉና ጤናን ማደሉ በራሱ ትልቅ ነገር፣ ትልቅ ሥራ ነው፡፡ ስለዚህ እናመስግነው፡፡ እግዚአብሔር ትሑት ስለሆነ ትሑታንን ይወዳል አለች፡፡ እግር ማጠቡን ታውቃለችና ትሑታንን ከፍ ከፍ ያደርጋል አለች፡፡ እነ ፈርዖንን እንዳሰጠመ ታውቃለችና ትዕቢተኞችን ያዋርዳል አለች፡፡ ◈ ትዕቢተኛ ሰው የሰይጣን ፈረስ ነው የሚሆነው፡፡ ገደል ገብቶ፣ ተሰባብሮ ነው የሚሞተው ስለዚህ ትሕትናን የመጀመሪያ ሥራችን እናድርግ፡፡ የክርስትና ልዩ ምልክት ትሕትና ነው፡፡ የሰይጣን ምልክት ግን ትዕቢት ነው፡፡ ዛሬ ሁላችንም የምንታመም፣ የምንወድቅ አይመስለንም፡፡ ስለዚህ ሰማይ ሰማይ እናያለን፡፡ ደኃውን ግን እንጸየፋለን፡፡ ዛሬ ምልክታችን ትሕትና ሊሆን ይገባል፡፡ ◈ በኪሩቤልና በሱራፌል ላይ የነገሠው አምላክ በመስቀል ላይ ነገሠ፡፡ ስለ እኛ በአህያ ላይ ነገሠ፡፡ ተቀመጠ፡፡ ይህ ሁሉ ትሕትና ነው፡፡ ስለዚህ መታወቂያ እናውጣ፤ መታወቂያ ይኑረን፡፡ መታወቂያችን የክፋት፣ የተንኮል፣ የጭካኔ፣ የዘረኝነት፣ የመለያየት አይሁን፡፡ የእኛ መታወቂያ የፍቅር፣ የሰላም፣ የይቅርታና የአንድነት መታወቂያ ይሁን፡፡ ይህን መታወቂያ ሁላችንም እንያዝ፡፡ በዚህም ደስ ይበለን፡፡ ግንቦት 27 1985 ዓ.ም. እንዳስተማሩት ማስታወሻ:- በረከታቸው ይደርብንና ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በድንቅ ስብከቶቻቸው እና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሠረቷቸው ገዳማትና ትምህርት ቤቶች፣ ባፈሯቸው መምህራንና መነኮሳት ለዘላለም የሚታወሱ ሊቀ ጳጳስ ናቸው። #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑በተለያየ ሰበብ የገቡ እና ያደፈጡ መናፍስቶች ያልተዋጋ አያሸንፍም፤ ያላሸነፈ ደግሞ አይሸለምም የርኩሳን መናፍስት ፈተና || ተሞክሮ ክፍል 28 🙏🙏 https://youtu.be/q90ATy6b4AM

+ ህዳር ጽዮን ማሪያም (21) ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤ በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ አዳራሽዋን አስቡ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ። (መዝ 48፥12) እንድን
+ ህዳር ጽዮን ማሪያም (21) ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤ በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ አዳራሽዋን አስቡ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ። (መዝ 48፥12) እንድንከባት፣ እንድናቅፋት፣ በዙሪያዋ ተሰብስበን እንድንመካባት፣ በብርታቶቿ ተማምነን ልባችንን እንድናሳርፍባት፣ ጽዮን አንባችንን፣ ጽዮን መታመኛችንን፣ ጽዮን መመኪያችንን የሰጠን አምላክ ይክበር ይመስገን!!! 🙏 ለአመቱ በሰላም በጤና ያድርሰን #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

"ልብ መልሱ፣ ልቡን ልቀቁ!" ◈ ርኩሳን መናፍስት የጋረዱት፣ እንደ ሀሳባቸው የወሰዱት ሰው ነፃ እንዲወጣ "ልብ መልሱ፣ ልቡን ልቀቁ!" ይባላል፡፡ በስሜቶች፣ በተጽዕኖዎች ስር ወድቆ ከውስጡ የራቀ እ
"ልብ መልሱ፣ ልቡን ልቀቁ!" ◈ ርኩሳን መናፍስት የጋረዱት፣ እንደ ሀሳባቸው የወሰዱት ሰው ነፃ እንዲወጣ "ልብ መልሱ፣ ልቡን ልቀቁ!" ይባላል፡፡ በስሜቶች፣ በተጽዕኖዎች ስር ወድቆ ከውስጡ የራቀ እንዲሰክን፣ እንዲሰበሰብ "ወደ ልብህ ሁን፣ ከልቦናህ ተመለስ" ይባላል፡፡ የሚያስተውል፣ በቋንቋ ከተሰደረው በላይ ያለውን የሚደርስበት፣ "ልቦናው የበራ፣ በልቡ የሚያይ" ይባላል፡፡ ሌላም ሌላም፡፡ ◈ ሰው ልቡን እስኪያገኝ፣ ከእውነት ውስጣዊ ሀሳቡ መመላለሻ ጋራ እስኪሆን ይመስለዋል እንጂ አካሄዱ ከራሱ አይደለም፡፡ በመጽሀፍ ቅኔ ትንሹ ልጅ ወደ ልቡ እስኪመለስ ከራሱ አልነበረም፡፡ ሰው ሆኖ፣ ከእሪያዎች ጋራ እንደ እሪያዎች ነበረ፡፡ ◈ በነገራችን ሰዎች የየራሳቸው ልብ እንዳላቸው ሁሉ፣ በውህደት ራሱን ወደቻለ ህልውነት ሲመጡም የጋራ የሆነ አንድ ልብ ይኖራቸዋል፡፡ በአንድ ልብ መካሪ በአንድ ቃል ተናገሪ እንደሚባል፡፡ ለምሳሌ የቤተሰብ ልብ አለ፡፡ የሀገርም ልብ አለ፡፡ በዚህ መሰረት፣ እስከ አሁን እንደሚሆነው የኢትዮጵያችን ልብ ጠፍቷል፡፡ ከራሷ አይደለችምና፡፡ ይሁንና እንመለሳለን (ሁሉም ሀገራት ልብ አላቸው ማለት አይደለም፤ ጥቂቶች ናቸው፤)፡፡ .. እንደገናም የሰው ልጆች ሁሉ የጋራ ልብ አለ፡፡ ከርሱም ከፍ ሲል፣ ፍጥረታት እስከ ተፈጥሮ ሥርዓታቸው የታሰቡበት ጠቅላይ ልብ አለ፡፡ "ልብ ይስጥህ/ሽ!" ቀላል ምርቃት አይደለም፡፡ #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑የሀሳብ፣ የምኞት፣ የልማድ ኃጢአቶችና መፍትሔዎቻቸው || ከ20 ዓመታት የጥላቻ አሳብ ወጥተው የታረቁ ቤተሰቦች | ቀዳሽና ዘፋኝ | የልማድ ኃጢአት ምንድነው? https://youtu.be/trQjU2JM-xU

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ - Statistics & analytics of Telegram channel @hailegebriel2021