en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 277
Subscribers
+224 hours
+97 days
+3830 days
Posts Archive
=> ሰላም የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! ቀጣይ ፕሮግራማችን አስደናቂው የቅድስት ሥላሴ ኃይል በሚገለጥበት እና በፈውስ በሚታይበት በቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ይካሄዳል። ፕሮግራማችን ዘወትር እሮብ፣ ሀሙስ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ጠዋት የሚቀጥል መሆኑን እንገልፃለን።  => አድራሻ፡ ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን። ከጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር ወንገላዊት ህንጻ ጀርባ ወይም ከዘንባባ ሆስፒታል ጀርባ => "በዚያን ጊዜ አፋችን በሳቅ፥ አንደበታችንም በዝማሬ ሞላ። ከዚያም በአሕዛብ መካከል፥ "እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገላቸው" አሉ። እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን ደስም ይለናል። (መዝሙረ ዳዊት 126:2-3) => እባኮትን ይህን መንፈሳዊ መልእክት ለሌሎች ያካፍሉ። የጌታችን በረከት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ። => Greetings dear beloved children of God! Our next program will be held at Holy Trinity and St Arsema Church, where the wonderful power of the Holy Trinity is being manifested and healing is taking place. We would like to inform you that our program will continue every Wednesday, Thursday, Saturday and Sunday on the morning.  => Address: Holy Trinity and St Arsema Church. On the way from Gotera to Wolo Sefer behind Wengelawit Building or behind Zenbaba Hospital => "Then our mouth was filled with laughter, And our tongue with singing. Then they said among the nations, “The LORD has done great things for them.” The LORD has done great things for us, And we are glad. Psalms 126:2-3 => Please share this spiritual message with others. May Our Lord blessing be with you all. Melake Hiwot Kesis Henok Tefera. #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

እኔ በግልጽ ነው አስማትን የማስተምረው || ስግደት አጋንንት ቶሎ እንዲጋለጡ ያደርጋል || በቀን 287 የምትሰግደው ሕጻን መምህር ግርማ | ተስፋዬ አበራ 😱🔥 https://youtu.be/P8QuzHA3h4s

ነሐሴ ፯ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል ማርያም.... "መላእክት በሰማያት እኅትነ ይብልዋ ፤ ሰማዕት ይኤምኅዋ እኅትነ ይብልዋ ፤ ጻድቃን በበነገዶሙ ይኤምኅዋ ፤ በሩካቤ ዘበሕግ እለ ወለድዋ እ
ነሐሴ ፯ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል ማርያም.... "መላእክት በሰማያት እኅትነ ይብልዋ ፤ ሰማዕት ይኤምኅዋ እኅትነ ይብልዋ ፤ ጻድቃን በበነገዶሙ ይኤምኅዋ ፤ በሩካቤ ዘበሕግ እለ ወለድዋ እምቤተ ክህነት ወመንግሥት ዘኀረይዋ ፤ ይእቲኬ ማርያም ይእቲ" ቅዱስ ያሬድ እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ! እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይባርክ ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ኑ አርጋኖን ዘሠሉስን አብረን እንጸልይ | አርጋኖን የማክሰኛ ጸሎት | የእመቤታችን የምስጋና Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://youtube.com/live/z8_cWY1grYk?feature=share

🚩ሴቶች እህቶቼ ልታዳምጡት ይገባል! || ብርቱ ጸሎትና ሱባኤ || ወርሃዊ ግደታና የሴቶች ፈተና || አባ ገብረኪዳን መምህር ኢዮብ ይመኑ ግርማ ወንድሙ 🔥😱😭💥 https://youtu.be/ZzmPiXOtmfs

በሦስት ቀን ዘጠኝ ሴቶችን የተገናኘው ደብተራ || የዘመኑ የጉስቁልና መንፈስ || ዝሙትና ጥጋብ ሀገር ያፈርሳሉ! ምን አይነት ጉድ ነው! #ethiopia 💥🚩🔥 https://youtu.be/CR_m7ZT3aXM

ሰዎችን የሚያስሩ ሰዎች ሲፈቱ ወሸት የሚያወሩ... የአባታችን ቀሲስ ሄኖክ ወልደማሪያም አገልግሎት በለንደን ይሄን ይመስል ነበር! ዕድሜ ይስጥልን በእውነት ለተቸገረው የሚራሩ አባቶችን ያብዛልን! ያታ
+5
ሰዎችን የሚያስሩ ሰዎች ሲፈቱ ወሸት የሚያወሩ... የአባታችን ቀሲስ ሄኖክ ወልደማሪያም አገልግሎት በለንደን ይሄን ይመስል ነበር! ዕድሜ ይስጥልን በእውነት ለተቸገረው የሚራሩ አባቶችን ያብዛልን! ያታሰሩትን የሚፈቱ፣ የሚያግዙና የሚረዱ አባቶችን ያብዛልን። ተመስገን ነው! ሰውን በመተት ማሠር፣ ዕድላቸውን መጠፈር የለመደ ሰው፤ ሰው ከክፉ መናፍስት ሲላቀቅ የታሰረው ዕድሉ ሲፈታ ውሸት ይመስለዋል። ማሰር የለመደ መፍታት ውሸት ይመስለዋል። ጌታችን በዮሐ 11፥44 ላይ "ፍቱትና ይሂድ ተዉት" ብሏል። እኛ ደግሞ ሰው በሕይወቱና በዕድሉ እንዳይጠቀም አስረን፣ እንዳይሄድ ጠፍረን ለሰው ስቃይ ሆነናል። ሰውን በመተት የምታስሩ፣ የሰውን ሕይወት የምታመሰቃቅሉ ሰዎች ያሰራችሁትን መፍታት ባትችሉም ጌታችን "ተዉት" እንዳለ ተዋቸው! አገልግሎቱ አሁን ቀጥሏል በነገው ዕለት ደግሞ ለአንድ ቀን ብቻ የሚሆን አገልግሎት አላቸው ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። አድራሻው White Hart lane, London N22 5QW ጠዋት 9 AM ሰዓት #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የዛሬው ቅዳሴ ከማርቆስ ወንጌል የተነበበው => ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሣ ጊዜ፥ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ። እርስዋ ሄዳ ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው፤ እነርሱም ሕያው እንደ ሆነ ለእርስዋም እንደ ታያት ሲሰሙ አላመኑም። ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤ እነርሱም ሄደው ለሌሎቹ አወሩ፤ እነዚያንም ደግሞ አላመኑአቸውም። => ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ። እንዲህም አላቸው። ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። => ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። እነርሱም ወጥተው በየስፍራው ሁሉ ሰበኩ፥ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፥ በሚከተሉትም ምልክቶች ቃሉን ያጸና ነበር። (የማርቆስ ወንጌል 16፡9-20) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የዘመኑ መንፈስ በትምህርት ቤቶቻችን የሴቶች ጥፍርና አጋንንታዊ ሴራው ዘወትር የሚያስፈልጉን ወሳኝ ነገሮች || ለሙስሊሟ የተደረገ ተዓምር #ebs 🔥🚩 https://youtu.be/8dUP4KKCHjY

ኑ አርጋኖን ዘቀዳሚትን አብረን እንጸልይ | Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://www.youtube.com/live/icwY0qoVLis?si=ZrdDcKSbYGl1yxV7

ኑ አርጋኖን ዘእሁድን አብረን እንጸልይ | የእሁድ የአርጋኖን ጸሎት የእመቤታችን ምስጋና | Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://www.youtube.com/live/tdpsGKpLF8U?si=ekysNbrMrejUAq9o

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ ነሐሴ 4 እና 5 ይካሄዳል። የፍልሰታ ጉባኤ በመሆኑ በ44ቱ ጸበል ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴ
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ ነሐሴ 4 እና 5 ይካሄዳል። የፍልሰታ ጉባኤ በመሆኑ በ44ቱ ጸበል ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን በመምጣት ጸበል ተጠምቃችሁ ቅብዐ ቅዱስ ተቀብታችሁ ፈውስና በረከትን እንድታገኙ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን። አድራሻ፦ከጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር መሄጃ ወንጌላዊት ሕንጻ ጀርባ ወይንም ዘንባባ ሆስፒታል ጀርባ 44ቱ ጸበል ፈለገ ዮርዳኖስ ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን። የቤተክርስቲያኑ አድራሻ Google map https://maps.app.goo.gl/Bgfd3G8QiRErw8k86 አንተ ግን ሂድ፥ ከአፌም የጻፍኸውን የእግዚአብሔርን ቃል በጾም ቀን በእግዚአብሔር ቤት በሕዝቡ ጆሮ በክርታሱ አንብብ፤ ኤር 36፥6። በሕመም በጭንቀት ውስጥ ላሉት በክፉ መንፈስ ለሚሰቃዩ እንዲሁም የመዳን መንገድ ጠፍቶባት ለምትባዝን ነፍስ ሁሉ ይሄንን መልእክት በማካፈል "ሼር" በማድረግ ያስተላልፉ። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን። © መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ።

=> ሰላም ሰላም ውድ ቤተሰቦቼ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ነገ ማለትም ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 12:00 ሰዓት ላይ እንደ ተለመደው በዩቱብ (YouTube) የላይቭ (Live) መርሐግብራችን ይቀጥላል። ወሳኝ ወሳኝ የሆኑ ጥያቄዎች ባለፈው የተጠየቅነውን እንመልሳለን አዳዲስ ጥያቄዎችንም እንቀበላለን። አስገራሚ ተዓምራቶችንና ገጠመኞች እንቃኛለን እንወያያለን። ሁላችሁም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ጥያቄዎቻችሁን መላክ ትችላላችሁ። ይሄን ቻናል ለብዙ ሰዎች እንዲደርስ ላይክ፣ ሸር እና ሰብስክራይብ ማድረጋችሁን አትርሱ። በርቱ፣ ጠንክሩ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በረኼኛው ቃሎ የቃልቻና የአውሊያ የዜማ አጋንንቶች || እያስቀደሴ እየቆረበ ሥራውን የሚሰራ ታድሏል || የቡዳ መንፈስ ያለባቸው መናፍቃን | እሸቱ መለሰ 🔥💥🚩 https://youtu.be/yuM1PZ01QOM

«ንጹህ ፍቅር» => ፍጹም ራስ ወዳድ አይደለም። ለፍቅር መስዋዕትነት ይከፍላል፣ ይንከባከባል፣ ይጸልያል ከራሱ ያስቀድማል። ነገሮችን አስተውሎ ጊዜ ወስዶ ከወራት ከዓመታት በኋላ በተረጋጋ ሥሜት ፍቅር ይጀምራል። ሊማርከው የሚችለው አጠቃላይ ስብዕናና መንፈሳዊነት እንጂ ከሰውነት ክፍል አንዱ ብቻ አይደለም። => በመልካም ሥነ-ምግባር የታረመ ከቀድሞ የተሻለ ሰው ያደርጋል በነገር ሁሉ ታማኝነት ያስገኛል። ያፈቀረውን ሰው ጉድለት በግልጽ ይመለከታል፣ ከስህተት እንዲታረም ይመክራል፣ አስፈላጊ በሆነው ነገር ሁሉ ከጎኑ ሆኖ ይረዳል። አለመግባባት ሲያጋጥም በውይይት ይፈታል። ለቁጣ አይቸኩልም ይታገሳል፣ ለነገር ፈንታ አይሰጥም ምንም አይነት ክፋት አያውቅም። አይታበይም፣ ይቅርታ ይጠይቃል፣ ይቅርታ ያደርጋል። => ሁሉን በሚያደርግ በእግዚአብሔር ፊት ይጠነቀቃል። ከሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር፣ ተካፍሎ ለመብላትና በማህበረሰቡ መካከል አርአያ ለመሆን ይጥራል ከሁሉ ጋር ደስ ይለዋል። ለምንም ነገር አይወድቅም እስከ ሞት ድረስ የታመነ ነው። እስከመጨረሻውም ይጸናል። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ራስን ድል መንሳት» የስጋ ምኞትንና ፍላጎትን አስመልክቶ ጾምና ድንግልናን ራስን ድል የመንሳት መንገዶች ናቸው፤ ነፍስን አስመልክቶ የሚጠቀስም ሌላ መንገድ አለ፤ ራሱን የሚገዛና እርሱነቱን ወደ ዓለማዊ ደስታ ከማዘንበል የሚያግድ ሰው ብጹዕ ነው። ማንነት ልታይ ልታይ ሲል ጉራውን ሊገልጥ ሊታበይ ይችላል፤ በዚህ ሁሉ ግን ልንቃወመው ይገባናል፤ ለእኛ ከእግዚአብሔር ጋር መደሰትና መልካም የሆነው ነገር ለመጪው ህይወት ብናቆይ የሚሻለን መሆኑን ራሳችንን ልናሳምነው ይገባናል፤ በዚህ ዓለም ድስታን ለማግኘት በሚፈልጉ ሰዎች ላይ የመድኋኒ ዓለም ቃል ይመሰክርባቸዋል። እውነት እላችኋለው፡- ዋጋቸውን ተቀብለዋል።" (ማቴ 6፥5) ስለዚህ በምድር ላይ ያሉ መብቶችህን ሁሉ ለማግኘት አትሞክር እግዚአብሔር እያንዳንዱ ዕንባህን ከዓይኖችህ ላይ የሚጠርግበት በወድያኛው ዓለም ቢሆንልህ ይሻልሃልና። ማንነትህ ወይም ስጋህ አሁን ላለህበት ዓለም ደስታ የሚያዘም ከሆነ በርትተህ ተከላከላቸው፤ በራስህ ወይም በስጋህ ላይ የምይወስደው ይህ እርምጃ ጭካኔ አደለም፤ለእነርሱ ዘላለማዊ ሕይወትን ማረጋገጫ እንጂ። ራሱን በዚህ ዓለም ሳለ የሚንከባከባት ያጠፋታል፤ ራሱን በጥብቅ ከመቆጣጠር ችላ የሚል ሰው በእርሱ ላይ ኋይል እንዲኖረው ያደርጋል፤ ስለሆነም ራሱን ለጽድቅ ከሚያለማምደውና የእግዚአብሔር መንገድ ከሚተገብረው ሰው በተለየ ሁኔታ በመንፈሳዊ ጠባዩ ላይ እንዲያምጽ ያደርገዋል። ራስን ድል መንሳት የሚሰጠው መንፈሳዊ ደስታ ከስጋ ደስታ ጋር እንደማይነጻጸር እርግጠኛ ሁን፤ ከሁሉ በጣም የሚያስደንቀው የራስ ጉራ ሙሉ ለሙሉ መጥፋት በሚገባው በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ ከፍ ከፍ ማለቱ ነው። አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በቲክቶክ ተሳዳቢውና ተቃዋሚው የመናፍስት ውጊያ ሲገባው መተትን ለመላቀቅ መንገዱ ለግሮሰሪ አሟቅዎች አድርሱልኝ || ኦርቶዶክስን የማዳከም ሴራ 😭🚩💥🔥 https://youtu.be/_uibMuDkonI?si=6HQhG0jXirBiGtg7

"ዛሬ በቅዳሴ ከተነበበው" እንግዲህ ወንዶች በስፍራ ሁሉ አለ ቍጣና አለ ክፉ አሳብ የተቀደሱትን እጆች እያነሱ እንዲጸልዩ እፈቅዳለሁ። እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸልሙ፤ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉት ሴቶች እንደሚገባ፥ መልካም በማድረግ እንጂ በሽሩባና በወርቅ ወይም በዕንቍ ወይም ዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ አይሸለሙ። ሴት በነገር ሁሉ እየተገዛች በዝግታ ትማር፤ ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ ልታስተምር ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም። አዳም ቀድሞ ተፈጥሮአልና፥ በኋላም ሔዋን ተፈጠረች። የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች፤ ነገር ግን በእምነትና በፍቅር በቅድስናም ራሳቸውን እየገዙ ቢኖሩ በመውለድ ትድናለች። (1ኛ.ጢሞ.2፡8-15) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239