HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Open in Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Show more2 269
Subscribers
+224 hours
+97 days
+2130 days
Posts Archive
መናፍስት በቶሎ እንድታሰሩ ይኼንን ሦስት መንገድ ዘወትር ተግብሩ!! የቤተሰብን መንፈስ በጭራሽ ወደራሳችሁ አትሳቡ!! 3ቱ ርኩሳን መናፍስትን ማሠሪያ መንገዶች! https://youtu.be/MoL9CmdkO9w
መምህር ግርማ ደብተራ ናቸው እያልኩ እንዳትኼድ እከለክላትና አጠራጥራት ነበር!! በወገብ ህመምና በዲስክ መንሸራተት የምትሰቃዬ ሰዎች ይኼንን አዳምጡ!! #ጸሎት https://youtu.be/y84_aKUv3O0
=> የእህታችን ጥያቄ! በህይወቴ በጣም የተወሳሰበ ነገር አለ እባክህን አማክረኝ፡፡ አንዳንዴ ግራ ይገባኛል እና የምትችል ከሆነ በመፍትሄ ሀሳብ እርዳኝ፡፡ ባለቤቴ በጣም እየረበሸኝ ነው። ለምን ትጸልያለሽ ይለኛል፡፡ ለምን ትቆርቢያለሽ ይለኛል፡፡ እኔን መስማት ያመዋል፡፡ ብቻ ምኑ ቅጡ ግራ ገባኝ አሁን። ምን ላድርግ?
=> እህታችን እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ፈታኝ ወቅት ብርታቱንና ትዕግሥቱን ይስጥሽ። ባለቤትሽ በጸሎትሽና በቍርባንሽ ላይ የሚያሳየው ተቃውሞ በመንፈሳዊው ዓለም "የፈተና ውጊያ" ተብሎ ይታወቃል። ሰይጣን አንቺ ወደ ፈጣሪሽ ስትቀርቢና ስትቀደሺ ስለሚቀና፣ የሚወጂውን ሰው በመጠቀም ሰላምሽን ሊነጥቅሽና ከመንፈሳዊ መንገድሽ ሊያስቆምሽ ይጥራል። ከዚህ በታች ያሉትን 5 ነጥቦች በጸሎትና በጥበብ ተግብሪያቸው፦
፩. ውጊያው ከመንፈስ ጋር መሆኑን ተረጂ፦ ባለቤትሽ እንዲህ የሚያደርገው በውስጡ ባለ ድካም ወይም በጠላት ውጊያ እንጂ እርሱ ክፉ ስለሆነ አይደለም። ስለዚህ በእርሱ ላይ አትቆጪ፣ አትጣዪውም፤ ይልቁንም በውስጡ ያለውን ያንን አስቸጋሪ መንፈስ በጸሎት ተዋጊው። ቅዱስ ጳውሎስ "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለም" (ኤፌ ፮:፲፪) እንዳለው አስቢ።
፪. በምስጢርና በጥበብ ጸልዪ፦ ጸሎትሽ በእርሱ ፊት ጠብ የሚያጭር ከሆነ፣ ጌታችን በወንጌል እንዳዘዘን "ወደ እልፍኝሽ ግቢና መዝጊያሽን ዝጊ" (ማቴ ፮:፮)። እርሱ በሌለበት፣ ተኝቶ እያለ ወይም በልብሽ በስውር ጸልዪ። አምላክ በስውር የምታደርጊውን ጸሎት ይሰማል፤ በመካከላችሁ ያለውንም ግድግዳ ያፈርሰዋል።
፫. በምግባርሽ መስክሪለት፦ ጸሎትና ቍርባን በውስጥሽ ሰላምን፣ ትሕትናንና ፍቅርን ሊያሳድጉ ይገባል። እርሱ ሲቆጣሽ አንቺ በትሕትና ዝም ስትዪ፣ ይበልጥ ስትንከባከቢውና ፍቅር ስታሳዪው "ይህቺ ሴት የምትጸልየው ጸሎት ለውጥ አምጥቶባታል" ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል። ቅዱስ ጴጥሮስ "ያለ ቃል በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲረቱ" (፩ኛ ጴጥ ፫:፩) እንዳለው፣ ያንቺ ዝምታና ትዕግሥት ትልቁ ስብከት ነው።
፬. የንስሐ አባትሽን አማክሪ፦ ይህንን ሁኔታ ለንስሐ አባትሽ በግልጽ ንገሪያቸው። አባቶች ምስጢራዊ በሆነ መንገድ (በጸሎትና በምክር) የሚረዱበት መንገድ ይኖራል። ምናልባትም በመካከላችሁ ያለውን የጠላት ውጊያ የሚሰብር ልዩ ጸሎት ሊያደርጉላችሁ ይችላሉ።
፭. ስሙን በመቁጠሪያ ጥሪ፦ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ለባለቤቴ ልቦና ስጠው፣ ቤታችንን በሰላም አብራልን" እያልሽ በመቁጠሪያሽ ለምኚ። የፈጣሪ እጅ የሰውን ልብ የማለስለስ ኃይል አለው።
በመጨረሻም እህቴ ሆይ፤ አትሸበሪ፣ ተስፋም አትቁረጪ። ቅዱስ ቍርባን የሕይወት መድኃኒት ነውና ከንስሐ አባትሽ ጋር በመመካከር በንጽሕና መቀበልሽን አታቋርጪ። ጠላት አንቺን ለማስቆም ቢሞክርም፣ አንቺ ግን በትዕግሥት ከጸናሽ ባለቤትሽንም ጭምር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይዘሽው ትገባለሽ።
"ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል።" (ያዕቆብ ፬:፯)
እግዚአብሔር ሰላሙን በቤትሽ ያውርድ! አሜን።
=> የአባታችን መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ መንፈሳዊ አገልግሎት ቀጥሏል!! ጉባኤው በቀጣይ ቅዳሜና እሁድ በ26 እና በ27 /07/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አያት ቅዱስ ፋኑኤልና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት እና የፀበል አገልግሎት ይከናወናል ሥለ አገልግሎቱ ፈጣን መረጃዎችና አዳዲስ ትምህርቶች እንዲደርሳችሁ ቻናሉን አሁኑኑ #የዩቱብ ቻናላችንን #ሰብስክራይና #ላይክ በማድረግ ቤተሰብ ሁኑ። ለሁሉም እንዲዳረስ #ሸር ማድረጋችሁን እንዳትረሱ!!
ይኼንን ጉዳይ እንደቀልድ የምታስቡ ሰዎች እራሳችሁን በደንብ ፈትሹ!! በዕዳ የተያዘ ትውልድ መከራው ብዙ ነው!! ለዘላለሙ ሰዓት የምትዘጋጀው ቤተክርስቲያን!! https://youtu.be/XxQh4ZSkneM
"ምስጋና ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን! ውድ የ'በማለዳ ንቁ' ቤተሰቦች፤ ስለ ፍቅራችሁና ስለማይለየው ድጋፋችሁ ከልብ አመሰግናለሁ። በዩቱብ ቆይታችን በጋራ 40,000 (40 ሺህ) ቤተሰብ ደርሰናል። ይህ ጉዞ የእኔ ብቻ ሳይሆን የሁላችንም ነው። ወደፊትም አብረን እየነቃንና እየተማርን እንድንቀጥል አምላከ ቅዱሳን ይርዳን። ክበሩልኝ!"
🙏 ዛቲ ይእቲ አክሊለ ወርቅ እንተ ታንጸበርቅ ዲበ ርእሶሙ ለቅዱሳን ነቢያት ዘበዕንቊ ክቡር ሥርጋዌሃ፤ ✨🍂
🙏 ጌጧ ከከበረ ዕንቁ የሆነ በነቢያት ራስ ላይ የምንታጸባርቅ የወርቅ አክሊል ይኽቺ ናት፤ በተመረጡ ሐዋርያት ራስ ላይ የምታበራ የብርሃን አክሊል ይኽቺ ናት፤ ከልጇ ጠላቶች በሚጋደሉ ሰማእታት ራስ የምታበራ ያበበ የድል አድራጊነት አክሊል ይኽቺ ናት፤
🙏 በዝሙት በደል ክህነታቸውን ባላሳደፉ ካህናት ራስ ላይ የምትቀመጥ ዋጋው የሆነ ከዕንቊ የተሠራ የመመኪያ አክሊል ይኽቺ ናት፤ በመላእክት ሥርአት ሥጋቸውን ከመተዳደፍ በጠበቁ በንጹሐን ደናግል ራስ ላይ የምታንጸባርቅ ይጽሐና አክሊል ይኽቺ ናት፤
🙏 በሰማያት የሚደረገው ሰርግን መርጠው በምድር የሚደረግ ከብካብን በተው መነኮሳት ራስ ላይ ከፀሐይ ይልቅ የምታበራ የቅድስና አክሊል ይኽቺ ናት፤
🙏 የዚህ ዓለም መተዳደፍ ያልነካት የሙሽርነት አክሊል ይኽቺ ናት፤
የጒስቁልና ያይደለች የክብር አክሊል ይኽቺ ናት፤ በልጇ ስም ለልተጠመቁት የማትደርሳቸው የምእመናን ጌጥ የምትሆን የጽድቅ አክሊል ይኽቺ ናት፤
የመለኮት ዕንቊ ማኖሪያ ሣጥን ይኺቺ ናት፤ የነዳያን ብልጥግናቸው የምትሆን የወርቅ ሙዳይ ይኽቺ ናት፤
እንኳን ለእመቤታችን ወርሀዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
( አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ : / አርጋኖን ዘሐሙስ / )
የአሾክሻኪ መንፈስን ሴራና ተንኮል ተረድታችሁ አሁኑኑ እራሳችሁን ፈትሹ!! ለረጅም ዓመት ቅምና ጥርስ የምትነክሱ ሰዎች አባካችሁ ተጠንቀቁ!! #ማዕተብ #ጸሎት https://youtu.be/1kEVImyPzwA
ክፉ መንፈስ አልጋለጥ ብሎ ካስቸገራችሁ አሁኑኑ ይኼንን አድርጉ!! ተፈውሳችሁ ከአጋንንት እስራት ነጻ ሆናችሁ መመስከር ለምን ፈራችሁ!? #አጋንንት #ጸሎት https://youtu.be/Cbvegpr82YY
መምህር ምትኩ የመናፍስትን ሴራ ላለማውራት የሄደበት ርቀት እጅግ ያሳዝናል!! የመምህሩ ግራ የገባው መልስ ለተጨነቀች ነፍስ!! መምህር ተስፋዬ ያጋለጠው መረጃ! https://youtu.be/Kup6IjYHQxQ
#ይኼንን_ምስክርነት_አንብቡ!!
=> እሁድ ለት በነበረው አገልግሎት በጣም የምያስገርም እና የሚደንቅ ነገር ነበር የሆነው እኔ ዱባይ ነኝ አንድ ወንድሜ በጣም ተጨንቆ በቴሌግራም እህቱ 13 አመት ሙሉ በኩላሊት በሽታ እንደተሰቃየችና አሁን ግን ዶክተሮች ተስፋ የለሽም እንዳሏት ነገረኝ እኔም በጊዜው ተረበሽኩና ስለሱ ውጊያ ከጀመረ ምን ያህል ጊዜ እንደሆነ ጠየኩት እሱም ገና አዲስ እንደሆነ ነገረኝ እኔም የአምልኮ ስግደቶቹን ላኩለትና እሷ መንቀሳቀስ አትችልም ስላለኝ ክርስትና ስሟን እጅህ ላይ ፅፈህ ስገድ አልኩት ወዲያው ግን እግዚአብሔር ድንቅ ነውና በዚሁ fb ላይ አንድ የመምህር ግርማ ተማሪ የሆነና የጸሎት ማህበር ያላቸውን ሰው ተዋወኩ እሱ ስለ ማህበሩ ሲነግረኝ ቶሎ ብዬ ስለ ኩላሊት ታማሚዋ ልጅ ነበር የነገርኩት እሱም ወንድሟ እንደምንም ብሎ ማህበር ላይ ይዟት ይምጣ ይለኛል እኔም ለወንድሟ እንደምንም ብለህ እዚህ ማህበር ላይ ይዘሃት ህድ ብዬ አድራሻቸውን ሰጠሁት ይዟት ሄደ እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው የ13 አመት በሽታ መተት ሆኖ ተገኘ ከዚያ መንፈሱ ሲያዝላት እሷም ጸሎቱንም ስግደቱንም ጀመረች ይህ የሆነው ቢየንስ ከሁለት ወር በፊት ነው አሁን እሁድ ለት በመምህር ግርማ እጅ ተሸኘላት ለአባታችን እድሜና ጤና ይስጥልኝ ውሻ በማያውቀው ሰው ላይ ነውና የሚጮሀው ስለሚጮሁት ሰዎች አንጨነቅም ይህ በረከት እንዳያልፋችሁ ግን እላለሁ።
#ሸር አድርጉ!
አብዝቶ ሰግዶ መተኛት በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነትና ግዴታ ማወቅ ያለባችሁ ነገር!! ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ ከመምህር ተስፋዬ የሚፈልገው ምንድነው? ከግለ ወሲብ ለመላቀቅ የሚረዱ 5 ወሳኝ መፍትሔዎች! የማይቆረብበት ትዳር በጭራሽ አያጸድቅም!! https://youtu.be/8ezVygzgDl4
ከስግደት ጋር በተገናኘ ሁሉም ኦሮቶዶክሳዊ ማወቅ የሚገባው 4 ወሳኝ ነጥቦች!! ሱባኤ ለመያዝ ጊዜ የሌላችሁ አሁኑኑ ይኼንን አድርጉ ብዙ ታተርፋላችሁ!! #ጸሎት https://youtu.be/8Voxv8XvaUA
✨ የጌታዬ እናት ማርያም
የበረከት ምንጭ የሰላም
መከራ በዝቶ ተጨንቀናል
ድንግል ነይልን ተማፅነናል
🙏 የኪዳነ ምሕረት ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ!
=> "ይህ የሕይወት እንጀራ ነው፤ የበላውም አይሞትም።" ቍርባን ዝም ብሎ ሥርዓት ሳይሆን የነፍሳችን መድኃኒት ነው። ሥጋችን ሲታመም ወደ ሐኪም እንደምንሮጥ ሁሉ፣ ነፍሳችን በኃጢአት ቁስል እንዳትሞት በቍርባን መድኃኒትነት ልታክሟት ይገባል። መድኃኒቱ በደጃችሁ እያለ በበሽታ (በኃጢአት) አትሙቱ። "ሁለት የሰም ሻማዎች ቀልጠው ሲዋሐዱ አንድ እንደሚሆኑ ሁሉ፣ የክርስቶስን ሥጋና ደም የሚቀበል ሰውም ከክርስቶስ ጋር አንድ ይሆናል።" የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከጌታ ጋር ካልተዋሐድን እንዴት ሕይወት ሊኖረን ይችላል? ቍርባን የፈጣሪን ባሕርይ ገንዘብ የምናደርግበትና በጸጋ የምንከብርበት ብቸኛው መንገድ ነው።
=> አባቶቻችን እንዲህ ብለው ይገሥጹናል፦ "ዛሬ በቁመትህ ሳለህ በንስሐ ታጥበህ ካልቆረብክ፣ ነገ በሬሳ ሳጥን ውስጥ ሆነህ ቢቀድሱብህ ምን ይጠቅምሃል?" ሞት ቀጠሮ የለውምና "አረጅቼ እቆርባለሁ" የሚለው የሰይጣን ማታለያ እንዳያታልላችሁ። አሁኑኑ ወደ ንስሐ አባታችሁ ቅረቡ፤ ለሰማያዊው ማዕድ ራሳችሁን አዘጋጁ። ወንድሜ ሆይ! እኅቴ ሆይ! ጌታችን በወንጌል "ሥጋዬን ካልበላችሁ ደሜንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም" (ዮሐ ፮፥፶፫) ብሎናል። ስለዚህ ሕይወት እንዲኖራችሁ፣ ጠላትን ድል እንድታደርጉና ከፈጣሪ ጋር አንድ እንድትሆኑ በንስሐ ታጥባችሁ ይህንን የከበረ ሥጋና ደም ለመቀበል አሁኑኑ ተነሡ።
"እግዚአብሔርን ቅመሱትና ቸር እንደ ሆነ እዩ።" (መዝ. ፴፫፥፰)
=> የአባታችን የመምህር ግርማ ወንድሙ ቀጣይ አገልግሎት በመጋቢት 20/07/2018 በእለተ እሁደ ስለሆነ ሁላችሁም ላልሰማ በማሰማት የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ መረጃውን አጋራለሁ። ብዙዎች ስትጠይቁ ስለነበረ ይኼው ተጠቀሙ ውዶች።
=> አድራሻ፦ ከመገናኛ በጎሮ ለሚ ኢንዱስትሪ ከሰሚት ኮንዶሚኒየም በ3ኛ በር ለሚ እንዱስትሪ ብለው ብመጡ ቤተክርስቲያኑን በቀላሉ ያገኛሉ።
መልካም ምሽት ለሁላችሁ ይሁን!
ሸር አድርጉ ላልሰሙ አሰሙ!
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
