መጽሐፈ ግጻዌ
Open in Telegram
ይህ ቻናል በየዕለቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚባሉትን ምስባክና የሚነበቡትን የወንጌል ንባባት የሚያስተላልፍ ነው።
Show more9 587
Subscribers
No data24 hours
+977 days
+28630 days
Posts Archive
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 24:33-45፡ "ወተንሥኡ ሶቤሃ" - "በዚያችም፡ሰዓት፡ተነሥተው፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ተመለሱ፥ዐሥራ፡አንዱና፡ከነርሱ፡ጋራ፡የነበሩትም፦ጌታ፡በእውነት፡ተነሥቷል፡ለስምዖንም፡ታይቷል፡እያሉ፡በአንድነት፡ተሰብስበው፡አገኟቸው። እነርሱም፡በመንገድ፡የኾነውን፡እንጀራውንም፡በቈረሰ፡ጊዜ፡እንዴት፡እንደ፡ታወቀላቸው፡ተረኩላቸው። ይህንም፡ሲነጋገሩ፡ኢየሱስ፡ራሱ፡በመካከላቸው፡ቆሞ፦ሰላም፡ለእናንተ፡ይኹን፡አላቸው። ነገር፡ግን፥ደነገጡና፡ፈሩ፡መንፈስም፡ያዩ፡መሰላቸው። ርሱም፦ስለ፡ምን፡ትደነግጣላችኹ፧ስለ፡ምንስ፡ዐሳብ፡በልባችኹ፡ይነሣል፧ እኔ፡ራሴ፡እንደ፡ኾንኹ፡እጆቼንና፡እግሮቼን፡እዩ፤በእኔ፡እንደምታዩት፥መንፈስ፡ሥጋና፡ዐጥንት፡የለውምና፡እኔን፡ዳስሳችኹ፡እዩ፡አላቸው። ይህንም፡ብሎ፡እጆቹንና፡እግሮቹን፡አሳያቸው። እነርሱም፡ከደስታ፡የተነሣ፡ገና፡ስላላመኑ፡ሲደነቁ፡ሳሉ፦በዚህ፡አንዳች፡የሚበላ፡አላችኹን፧አላቸው። እነርሱም፡ከተጠበሰ፡ዓሣ፡አንድ፡ቍራጭ፥ከማር፡ወለላም፡ሰጡት፤ ተቀብሎም፡በፊታቸው፡በላ። ርሱም፦ከእናንተ፡ጋራ፡ሳለኹ፡በሙሴ፡ሕግና፡በነቢያት፡በመዝሙራትም፡ስለ፡እኔ፡የተጻፈው፡ዅሉ፡
ይፈጸም፡ዘንድ፡ይገ፟ባ፟ል፡ብዬ፡የነገርዃችኹ፡ቃሌ፡ይህ፡ነው፡አላቸው። በዚያን፡ጊዜም፡መጻሕፍትን፡ያስተውሉ፡ዘንድ፡አእምሯቸውን፡ከፈተላቸው፤"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
፬ኛ ሳምንት እምድኅረ ትንሳኤ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ።
ወተንሣእኩ እስመ እግዚአብሔር አንሥአኒ።
ኢይፈርህ እም አእላፍ አሕዛብ። መዝ 3÷5
🕯 ትርጉም
እኔ፡ተኛኹ፡አንቀላፋኹም፤
እግዚአብሔርም፡ደግፎኛልና፥ነቃኹ።
ከሚከቡ፟ኝ፡ከአእላፍ፡ሕዝብ፡አልፈራም።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 26፥69-ፍ፡ም፡ "ወጴጥሮስ ይነብር" - "ጴጥሮስም፡ከቤት፡ውጭ፡በዐጥሩ፡ግቢ፡ተቀምጦ፡ነበር፤አንዲት፡ገረድም፡ወደ፡ርሱ፡ቀርባ፦አንተ፡ደግሞ፡ከገሊላው፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበርኽ፡አለችው። ርሱ፡ግን፦የምትዪውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡በዅሉ፡ፊት፡ካደ። ወደ፡በሩም፡ሲወጣ፡ሌላዪቱ፡አየችውና፡በዚያ፡ላሉት፦ይህ፡ደግሞ፡ከናዝሬቱ፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበረ፡አለች። ዳግመኛም፡ሲምል። ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ካደ። ጥቂትም፡ቈይተው፡በዚያ፡ቆመው፡የነበሩ፡ቀርበው፡ጴጥሮስን፦አነጋገርኽ፡ይገልጥኻልና፥በእውነት፡አንተ፡ደግሞ፡ከነርሱ፡ወገን፡ነኽ፡አሉት። በዚያን፡ጊዜ፦ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ሊራገምና፡ሊምል፡ዠመረ።ወዲያውም፡ዶሮ፡ጮኸ። ጴጥሮስም፦ዶሮ፡ሳይጮኽ፡ሦስት፡ጊዜ፡ትክደኛለኽ፡ያለው፡የኢየሱስ፡ቃል፡ትዝ፡አለው፤ወደ፡
ውጭም፡ወጥቶ፡መራራ፡ልቅሶ፡አለቀሰ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
24/8/2018 ዓ.ም (፳፬/፰/፳፻፲፰ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በዕለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወደንገፀኒ ልብየ በላዕልዬ።
ወመጽአኒ ድንጋፄ ሞት።
ፍርሃት ወረዐድ አኀዘኒ ውደፈነኒ ጽልመት። መዝ. 54፥4
🕯 ትርጉም
ልቤ፡በላዬ፡ተናወጠብኝ፥
የሞት፡ድንጋጤም፡ወደቀብኝ።
ፍርሀትና፡እንቅጥቅጥ፡መጡብኝ፥
ጨለማም፡ሸፈነኝ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 21:28-33፡ "ወምንት ትብሉ ብእሲ" - "አንድ፡ሰው፡ኹለት፡ልጆች፡ነበሩት፤ወደ፡አንደኛው፡ቀርቦ፦ልጄ፡ሆይ፥ዛሬ፡ኺድና፡በወይኔ፡አትክልት፡ሥራ፡አለው። ርሱም፡መልሶ፦ አልወድም፡አለ፤ዃላ፡ግን፡ተጸጸተና፡ኼደ። ወደ፡ኹለተኛውም፡ቀርቦ፡እንዲሁ፡አለው፡ርሱም፡መልሶ፦ዕሺ፡ጌታዬ፡አለ፤ነገር፡ግን፥አልኼደም። ከኹለቱ፡የአባቱን፡ፈቃድ፡ያደረገ፡ማን፡ነው፧ ፊተኛው፡አሉት።ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦ እውነት፡እላችዃለኹ፥ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ወደእግዚአብሔር፡መንግሥት፡በመግባት፡ይቀድሟችዃል። ዮሐንስ፡በጽድቅ፡መንገድ፡መጥቶላችኹ፡ነበርና፥ አላመናችኹበትም፤ ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ግን፡አመኑበት፤ እናንተም፡ይህን፡አይታችኹ፡ታምኑበት፡ዘንድ፡በዃላ፡ንስሓ፡አልገባችኹም። ሌላ፡ምሳሌ፡ስሙ።የወይን፡አትክልት፡የተከለ፡ባለቤት፡ሰው፡ነበረ፤ቅጥርም፡ቀጠረለት፥መጥመቂያም፡
ማሰለት፥ግንብም፡ሠራና፡ለገበሬዎች፡አከራይቶ፡ወደ፡ሌላ፡አገር፡ኼደ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ቅዳሴ ዘባስልዮስ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
24/8/2018 ዓ.ም (፳፬/፰/፳፻፲፰ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ።
ከመ ያምስጡ እምገጸ ቀስት።
ወይድኀኑ ፍቁራኒከ። መዝ 59:3
🕯 ትርጉም
ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ።
ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው።
ወዳጆችህ እንዲድኑ፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🕯ዕብራ. 12፥1-12 - "ወበእንተ ዝንቱ ንሕነኒ እለ ብነ።"
🕯2ኛ ጴጥ. 3፥16-ፍ፡ም፡ - "ወዘሰ ነበቡ እሙንቱ ሰብእ።"
🕯ግብ: ሐዋ: 16፥27-ፍ፡ም፡ -"ወሶበ ነቅሀ ዐቃቤ ሞቅሕ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማር. 16፥1-9፡ "ወሶበ ኀለፈት ሰንበት ማርያም" - "ሰንበትም፡ካለፈ፡በዃላ፡መግደላዊት፡ማርያም፡የያዕቆብም፡እናት፡ማርያም፡ሰሎሜም፡መጥተው፡ሊቀቡት፡ሽቱ፡ገዙ። ከሳምንቱም፡በፊተኛው፡ቀን፡እጅግ፡በማለዳ፡ፀሓይ፡ከወጣ፡በዃላ፡ወደ፡መቃብር፡መጡ። ርስ፡በርሳቸውም፦ድንጋዩን፡ከመቃብር፡ደጃፍ፡ማን፡ያንከባልልልናል፧ይባባሉ፡ነበር፤ ድንጋዩ፡እጅግ፡ትልቅ፡ነበርና፤አሻቅበውም፡አይተው፡ድንጋዩ፡ተንከባሎ፡እንደ፡ነበር፡ተመለከቱ። ወደ፡መቃብሩም፡ገብተው፡ነጭ፡ልብስ፡የተጐናጸፈ፡ጕልማሳ፡በቀኝ፡በኩል፡ተቀምጦ፡አዩና፡ደነገጡ። ርሱ፡ግን፦ አትደንግጡ፤ የተሰቀለውን፡የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡ትፈልጋላችኹ፤ተነሥቷል፥በዚህ፡የለም፤ እንሆ፥ ርሱን፡ያኖሩበት፡ስፍራ። ነገር፡ግን፥ኼዳችኹ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ለጴጥሮስም፦ወደ፡ገሊላ፡ይቀድማችዃል፤እንደ፡ነገራችኹ፡በዚያ፡ታዩታላችኹ፡ብላችኹ፡ንገሯቸው፡አላቸው። መንቀጥቀጥና፡መደንገጥ፡ይዟቸው፡ነበርና፥ ወጥተው፡ከመቃብር፡ሸሹ፤ይፈሩ፡ነበርና፥ ለማንም፡አንዳች፡አልነገሩም። እነርሱም፡ያዘዛቸውን፡ዅሉ፡ለጴጥሮስና፡ከርሱ፡ጋራ፡ላሉት፡በዐጪሩ፡ተናገሩ።ከዚህም፡በዃላ፡ኢየሱስ፡ራሱ፡ለዘለዓለም፡ድኅነት፡የኾነውን፡የማይለወጠውን፡ቅዱስ፡ወንጌል፡ከፀሓይ፡መውጫ፡እስከ፡መጥለቂያው፡ድረስ፡በእጃቸው፡ላከው። ከሳምንቱም፡በመዠመሪያው፡ቀን፡ማልዶ፡በተነሣ፡ጊዜ፥አስቀድሞ፡ሰባት፡አጋንንት፡ላወጣላት፡ለመግደላዊት፡ማርያም፡ታየ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
24/8/2018 ዓ.ም (፳፬/፰/፳፻፲፰ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በዕለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወእምዕብን አልዐልከኒ።
ወመራህከኒ እስመ ተስፋየ ኮንከኒ።
ማኅፈድ ጽኑዕ ቅድመ ገጸ ጸላዒ። መዝ. 60፥2
🕯 ትርጉም
በድንጋይ፡ላይ፡ከፍ፡ከፍ፡አደረግኸኝ።
ጽኑ፡ግንብ፡በጠላት፡ፊት፡ተስፋዬም፡ኾነኸኛልና፥መራኸኝ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
9 587
መልክዐ ጊዮርጊስ
ሰላም ለሕሊናከ ዘመከረ በልባዌ። በሞቱ ወበተንሥኦቱ ለተሳትፎ መርዓዌ። ዓቃቤ ሥራይ ጊዮርጊስ መፈውሰ ደዌ። ለወለት ከመ ቤዘውካ እምአፈ ደራጎን አርዌ። ተረፈ ሕይወትየ ቤዙ እምኲሉ ምንሳዌ።
ዚቅ
ጸርሐ ጊዮርጊስ በዓቢይ ቃል : ወይቤ እፎ ኢይኄሊ ከመ አምላኪየ ተሰቅለ ዲበ ዕፀ መስቀል።
ትርጉም
ጊዮርጊስ በታላቅ ቃል አምላኬ በዕፀ መስቀል ላይ እንደተሰቀለ እንዴት አላስብም እያለ ጮኸ ።
ትርጓሜ
ስድስት ሰአት በሆነ ጊዜ ጊዮርጊስ ራሱን ዝቅ አደረገ መንፈሱም ያን ጊዜ ወጣች ።
ዚቅ ዓዲ (ወይም)
ሰኪቦ ለወልድ ትንሣኤ ሞቶ : ጊዮርጊስ ወረሰ ሰማያዊተ መንግሥቶ።
ትርጉም
ጊዮርጊስ የወልድ ትንሣኤ ሞቱን አስተምሮ ሰማያዊ የሆነች መንግሥቱን ወረሰ ።
@EOTCmahlet
ዓዲ ዚቅ
ቀዊሞ ገሃደ ውስተ ዓውደ ስምዕ : ጊዮርጊስ ሰበከ ትንሣኤ ሞቱ ለበግዕ።
ትርጉም
ጊዮርጊስ በምስክር አደባባይ ላይ በግልጥ ቆሞ የበግዕ ክርስቶስ የሞቱን ትንሣኤ አስተማረ ።
ወረብ
ወይቤ ጊዮርጊስ በዓቢይ ቃል ጸርሐ በዓቢይ ቃል ወይቤ/፪/
እፎ ኢይኄሊ ከመ አምላኪየ ተሰቅለ ዲበ ዕፀ መስቀል/፪/
@EOTCmahlet
ዓዲ (ወይም)
ጸርሐ ጊዮርጊስ በዓቢይ ቃል ወይቤ በዓቢይ ቃል/፪/
እፎ ኢይኄሊ ከመ አምላኪየ ተሰቅለ ዲበ ዕፀ መስቀል/፪/
ትርጉም
ጊዮርጊስ በታላቅ ቃል አምላኬ በዕፀ መስቀል ላይ እንደተሰቀለ እንዴት አላስብም እያለ ጮኸ ።
መልክዐ ጊዮርጊስ
ሰላም ለፀዓተ ነፍስከ ጽዋዓ ደመ ስምዕ ሰሪቦ። እማኅፈደ ሥጋ በገድል መከራ ስቃይ ድኅረ ረከቦ። ጊዮርጊስ ስመከ ሶበ እጼውእ በአስተርክቦ። ረድኤትከ ኀበ ሀሎኩ በአርአያ ብእሲ ቀሪቦ። ለትካዘ ልብየ ዘልፈ ያሰስል ዕፅቦ።
ዚቅ
ጊዜ ፮ቱ ሰዓት : አጽነነ ርዕሶ #ጊዮርጊስ ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ።
ስድስት ሰአት በሆነ ጊዜ ጊዮርጊስ ራሱን ዝቅ አደረገ መንፈሱም ያን ጊዜ ወጣች ።
ወረብ
ጊዜ ፮ቱ ሰዓት "ጊዜ"/፪/ ፮ቱ ሰዓት/፪/
አጽነነ ርዕሶ ጊዮርጊስ ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ/፪/
ትርጓሜ
ስድስት ሰአት በሆነ ጊዜ ጊዮርጊስ ራሱን ዝቅ አደረገ መንፈሱም ያን ጊዜ ወጣች ።
@EOTCmahlet
መልክዐ ጊዮርጊስ
ሰላም ለበድነ ሥጋከ እምርጢነ ገለአድ ዘተኃርየ። በላዕለ ድውያን ፈወሰ እስመ ፈድፋደ አርአየ። ጊዮርጊስ ለከ ትብለከ ነፍስየ። በበድነ ሥጋከ ተማኅጸንኩ ኢታስተኀፍር ተስፋየ። ስዕለተ ከናፍርየ ስማዕ ወፈጽም ጻህቅየ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
ፈወሰ ዱያነ ወከሠተ አዕይንት ዕውራን : ወኲሎ ፈጺሞ አዕረፈ ጊዮርጊስ ሰማዕት።
ትርጓሜ
ሰማዕት ጊዮርጊስ ሕመምተኞችን ፈወሰ ። የዕውራን ዐይንንም አበራ ። ሁሉን ፈጽሞ አረፈ ።
@EOTCmahlet
መልክዐ ጊዮርጊስ
ሰላም ለግንዘተ ሥጋከ በዕደ አግብርቲከ ፪ኤ። ድኅረ ሰለጥከ መዊተ እንዘ ብከ ተስፋ ትንሣኤ። ጊዮርጊስ ዘፆርከ ሥቃየ ዓመታት ሱባኤ። ስመከ በተአምኖ ሶበ አወትር ጽዋዔ። አስራበ ረድኤትከ ያጥልል ዘዚአየ ጒርኤ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
፯ ዓመተ ዘኮነንዎ : ለቅዱስ ጊዮርጊስ ኢመሰሎ ከመ አሐቲ ዕለት : ብእሲ ጻድቅ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር።
ትርጉም
ቅዱስ ጊዮርጊስን ሰባት ዐመታትን ቢፈርዱበት እግዚአብሔር የመረጠው ጻድቅ ሰው እንደ አንዲት ቀን አልመሰለውም ።
መልክዐ ጊዮርጊስ
ሰላም ለመቃብሪከ ምክሐ አድያሚሃ ወዓጸዳ። ለምድረ ሙላድከ ልዳ። ጊዮርጊስ ዘልፈ ሀብተ በረከት ዘእፈቅዳ። ከመ ትጸጊ ሕንባበ ረዳ ለኢያሪኮ በዓውዳ። በዲበ ድማኅየ ትጽጊ እምሰማይ ወሪዳ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
ወረደ ብርሃን ኀበ መቃብሩ ለብእሴ እግዚአብሔር : ወኮነ መቃብሩ ዘየሐዩ ዱያነ : ጸሎቱ ለጊዮርጊስ ወበረከቱ የሃሉ ምስሌነ።
ትርጉም
ብርሃን ወደ እግዚአብሔር ሰው መቃብር ላይ ወረደ ። መቃብሩም ለሕመምተኞች ሕይወትን የሚሰጥ ሆነ ። የጊዮርጊስ ጸሎቱ ከበረከቱ ጋራ ከእኛ ጋረሠ ይኑር ።
ምልጣን
ዮም ተጽሕፈ እምነገሥት ከላሌሁ በመጥባሕት ለጊዮርጊስ ሰማዕት : ጸለየ ጊዮርጊስ ወአውዓዮሙ በነበልባል : አማን ኃያል ገባሬ ኃይል።
ትርጉም
በቢላዋ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቆረጥ ከነገሥታት ዛሬ ተጻፈ ። ጊዮርጊስ ጸለየ በእሳትም አቃጠላቸው ። በእውነ፦ ኃይልን የሚያደርግ ኃያል ነው ።
አመላለስ
አማን በአማን ኃያል 'አማን በአማን'/፪//፪/
ኃያል ገባሬ ኃይል/፬/
ትርጉም
እውነት በእውነት ኃያል ነው እውነት በእውነት ኃይልን የሚያደርግ ኃያል ነው ።
ወረብ፦
ዮም ተጽሕፈ እምነገሥት ከላሌሁ በመጥባሕት ለጊዮርጊስ/፪/
ጸለየ ጊዮርጊስ ወአውዓዮሙ በነበልባል አማን ገባሬ ኃይል/፪/
ትርጉም
በቢላዋ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቆረጥ ከነገሥታት ዛሬ ተጻፈ ። ጊዮርጊስ ጸለየ በእሳትም አቃጠላቸው ። በእውነ፦ ኃይልን የሚያደርግ ኃያል ነው ።
@EOTCmahlet
እስመ ለዓለም
ወሰበረ ኆኃተ ብርት ሞዖ ለሞት : ተንሥእ ወልድ በሣልስት ዕለት : ወአግዓዘ ነፍሰ ጻድቃን እምጽልመት ወጽላሎተ ሞት : ካዕበ ይቤሎሙ ለአርዳኢሁ : ገሊላ እቀድመክሙ።
ትርጉም
የብረት ደጆችን ሰበረ ። ሞትን አሸነፈው ወልድ በሦስተኛው ቀን ተነሣ ። ከሞት ጥላ እና ከጨለማ የጻድቃን ነፍስን ነጻ አወጣ ። ዳግመኛም ደቀ መዛሙርቱን ወደ ገሊላ እቀድማችሗለሁ አላቸው ።
እስመ ለዓለም (ዓዲ)
ንግበር በዓለ በትፍሥሕት :በአስተሐምሞ ቅድስተ ፋሲካ ተዝካረ ትንሣኤሁ ለጊዮርጊስ ነገሮ ኅቡዓተ ኲሎ ሥርዓተ ምሥጢር በደኃሪ ይትገበር ዘሀሎ በንዝኃተ ደሙ ለክርስቶስ ለመፃጉዕ ዘአሕየዎ በቃሉ ወለዕውርኒ ዘከሠተ ዓይኖ ተንሥአ እሙታን ለአልዓዛር ተንሥእ ዘይቤሎ ወለያዕቆብ ዘአዕተዎ ብሔሮ ተንሥአ እሙታን ምዕረ ሦዓ ርእሶ ወተዓውቀ በመንፈሱ በፈቃዱ ወልድ አቅተለ ርእሶ ተንሥአ እሙታን ሲኦለ ወሪዶ ሰበከ ግዕዛነ በመስቀሉ ወልድ ገብረ መድኃኒተ ተንሥአ እሙታን ጸርሐት ሲኦለ ወትቤ ሰማያዊ ዝስኩ ዘለኪፎቶ ኢይክል።
ትርጉም
የትንሣኤውን ማሰብያ የተለየች ፋሲካን በማዘጋጀት በደስታ በዓልን እናድርግ ። ለጊዮርጊስ የተሸሸገውን ሁሉ ነገረው ። በክርስቶስ በደሙ መረጨት ያለ የምሥጢር ሥርአት በመጨረሻ ይሠራ ። በቃሉ መጻጕዕን ያዳነው ለዕውር ዓይኑን ያበራለት ከሙታን ተነሣ ። አልዓዛርን ከሙታን ተነሳ ያለው ፤ ያዕቆብን ወደ አገሩ ያስገባው ከሙታን ተነሣ ።አንድ ጊዜ ራሱን መስዋዕት አደረገ ። በመንፈሱ ታወቀ ወልድ በፈቃዱ ራሱን አስገደለ ። ከሙታን ተነሣ ። ወደ ሲኦል ወርዶ ነጻነትን ሰበከ ። ወልድ በመስቀሉ መድኃኒትን አደረገ ። ከሙታን ተነሣ ። ሲኦል መንካቱን የማይችል ያው ሰማያዊ እያለች ጮኸች ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 10:16-32 "ወናሁ አነ እፌንወክሙ ከመ አባግዕ" - "እንሆ፥እኔ፡እንደ፡በጎች፡በተኵላዎች፡መካከል፡እልካችኋለሁ፤ስለዚህ፥እንደ፡እባብ፡ልባሞች፡እንደ፡ርግብም፡የዋሆች፡ሁኑ። ነገር፡ግን፥ወደ፡ሸንጎ፡አሳልፈው፡ይሰጧችኋል፥በምኵራቦቻቸውም፡ይገርፏችኋልና፥ከሰዎች፡ተጠበቁ፤ ለእነርሱና፡ለአሕዛብም፡ምስክር፡እንዲሆን፥ስለ፡እኔ፡ወደ፡ገዢዎች፡ወደ፡ነገሥታትም፡ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም፡ሲሰጧችሁ፥የምትናገሩት፡በዚያች፡ሰዓት፡ይሰጣችኋልና፥እንዴት፡ወይስ፡ምን፡እንድትናገሩ፡አትጨነቁ፤ በእናንተ፡የሚናገር፡የአባታችሁ፡መንፈስ፡ነው፡እንጂ፥የምትናገሩ፡እናንተ፡አይደላችሁምና። ወንድምም፡ወንድሙን፥አባትም፡ልጁን፡ለሞት፡አሳልፎ፡ይሰጣል፥ልጆችም፡በወላጆቻቸው፡ላይ፡ይነሣሉ፡ይገድሏቸውማል። በሁሉም፡ስለ፡ስሜ፡የተጠላችሁ፡ትሆናላችሁ፤እስከ፡መጨረሻ፡የሚጸና፡ግን፡እርሱ፡ይድናል። በአንዲቱ፡ከተማም፡መከራ፡ቢያሳይዋችሁ፡ወደ፡ሌላዪቱ፡ሽሹ፤እውነት፡እላችኋለሁና፥የሰው፡ልጅ፡እስኪመጣ፡ድረስ፡የእስራኤልን፡ከተማዎች፡አትዘልቁም። ደቀ፡መዝሙር፡ከመምህሩ፥ባሪያም፡ከጌታው፡አይበልጥም። ደቀ፡መዝሙር፡እንደ፡መምህሩ፥ባሪያም፡እንደ፡ጌታው፡መሆኑ፡ይበቃዋል።ባለቤቱን፡ብዔል፡ዜቡል፡ካሉት፥ቤተ፡ሰዎቹንማ፡እንዴት፡አብዝተው፡አይሏቸው! እንግዲህ፡አትፍሯቸው፤የማይገለጥ፡የተከደነ፥የማይታወቅም፡የተሰወረ፡ምንም፡የለምና። በጨለማ፡የምነግራችሁን፡በብርሃን፡ተናገሩ፤በጆሮም፡የምትሰሙትን፡በሰገነት፡ላይ፡ስበኩ። ሥጋንም፡የሚገድሉትን፡ነፍስን፡ግን፡መግደል፡የማይቻላቸውን፡አትፍሩ፤ይልቅስ፡ነፍስንም፡ሥጋንም፡በገሃነም፡ሊያጠፋ፡የሚቻለውን፡ፍሩ። ሁለት፡ድንቢጦች፡በዐምስት፡ሳንቲም፡ይሸጡ፡የለምን፧ከእነርሱም፡አንዲቱ፡ያለአባታችሁ፡ፈቃድ፡በምድር፡ላይ፡አትወድቅም። የእናንተስ፡የራሳችሁ፡ጠጕር፡ሁሉ፡እንኳ፡ተቈጥሯል። እንግዲህ፡አትፍሩ፡ከብዙ፡ድንቢጦች፡እናንተ፡ትበልጣላችሁ። ስለዚህ፥በሰው፡ፊት፡ለሚመሰክርልኝ፡ሁሉ፥እኔ፡ደግሞ፡በሰማያት፡ባለው፡በአባቴ፡ፊት፡እመሰክርለታለሁ። በሰው፡ፊትም፡የሚክደኝን፡ሁሉ፡እኔ፡ደግሞ፡በሰማያት፡ባለው፡በአባቴ፡ፊት፡እክደዋለሁ። በምድር፡ላይ፡ሰላምን፡ለማምጣት፡የመጣኹ፡አይምሰላችኹ፤ሰይፍን፡እንጂ፡ሰላምን፡ለማምጣት፡አልመጣሁም። ሰውን፡ከአባቱ፥ሴት፡ልጅንም፡ከእናቷ፥ምራትንም፡ከአማቷ፡እለያይ፡ዘንድ፡መጥቻለሁና፤ ለሰውም፡ቤተ፡ሰዎቹ፡ጠላቶች፡ይሆኑበታል። ከእኔ፡ይልቅ፡አባቱን፡ወይም፡እናቱን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገባውም፤ከእኔ፡ይልቅም፡ወንድ፡ልጁን፡ወይም፡ሴት፡ልጁን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገባውም፤ መስቀሉንም፡የማይዝ፡በኋላዬም፡የማይከተለኝ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገባውም። ነፍሱን፡የሚያገኝ፡ያጠፋታል፥ነፍሱንም፡ስለ፡እኔ፡የሚያጠፋ፡ያገኛታል። እናንተን፡የሚቀበል፡እኔን፡ይቀበላል፥እኔንም፡የሚቀበል፡የላከኝን፡ይቀበላል። ነቢይን፡በነቢይ፡ስም፡የሚቀበል፡የነቢይን፡ዋጋ፡ይወስዳል፥ጻድቅንም፡በጻድቅ፡ስም፡የሚቀበል፡የጻድቁን፡ዋጋ፡ይወስዳል። ማንም፡ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡ለአንዱ፡ቀዝቃዛ፡ጽዋ፡ውሃ፡ብቻ፡በደቀ፡መዝሙር፡ስም፡የሚያጠጣ፥እውነት፡እላችኋለሁ፥ዋጋው፡አይጠፋበትም።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ቅዳሴ ዘወልደ ነጎድጓድ አው ዘዲዮስቆሮስ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
23/08/2018 ዓ.ም (፳፫/፰/፳፻፲፰ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ።
በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ።
ይባእ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን፡፡ መዝ 78:10
🕯 ትርጉም
አሕዛብ አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ።
የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል።
በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ይወቁ፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🕯2ኛ ቆሮ. 1፥1-10 - "ጳውሎስ ሐዋርያሁ ለኢየሱስ።"
🕯1ኛ ጴጥ. 1፥7-10፡ - "ወባሕቱ ኀዳጠ ይእዜ ሀለውክሙ።"
🕯ግብ: ሐዋ: 14፥1-23፡ -"ወበሀገረ ኢቆንዮን ቦኡ ምኲራብ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
9 587
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 12፥1-13 "ወተጋብኡ ኀቤሁ አእላፍ ሰብእ" - "በዚያን፡ጊዜ፡የሕዝብ፡አእላፍ፡ርስ፡በርሳቸው፡እስኪረጋገጡ፡ድረስ፡ተሰብስበው፡ሳሉ፥ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንዲህ፡ይል፡ዠመር። አስቀድማችኹ፡ከፈሪሳውያን፡ርሾ፡ተጠበቁ፥ ርሱም፡ግብዝነት፡ነው። ነገር፡ግን፥የማይገለጥ፡የተከደነ፥የማይታወቅም፡የተሰወረ፡ምንም፡የለም። ስለዚህ፥በጨለማ፡የምትናገሩት፡ዅሉ፡በብርሃን፡ይሰማል፥በዕልፍኝም፡ውስጥ፡በዦሮ፡የምትናገሩት፡በሰገነት፡ላይ፡ይሰበካል። ለእናንተም፡ለወዳጆቼ፡እላችዃለኹ፥ሥጋን፡የሚገድሉትን፡በዃላም፡አንድ፡ስንኳ፡የሚበልጥ፡ሊያደርጉ፡የማይችሉትን፡አትፍሩ። እኔ፡ግን፡የምትፈሩትን፡አሳያችዃለኹ፤ከገደለ፡በዃላ፡ወደ፡ገሃነም፡ለመጣል፡ሥልጣን፡ያለውን፡
ፍሩ።አዎን፡እላችዃለኹ፥ርሱን፡ፍሩ። ዐምስት፡ድንቢጦች፡በዐሥር፡ሳንቲም፡ይሸጡ፡የለምን፧ ከነርሱም፡አንዲቱ፡ስንኳ፡በእግዚአብሔር፡ፊት፡
አትረሳም። ነገር፡ግን፥የእናንተ፡የራሳችኹ፡ጠጕር፡ዅሉ፡እንኳ፡የተቈጠረ፡ነው፤እንግዲያስ፡አትፍሩ፡ከብዙ፡ድንቢጦች፡ትበልጣላችኹ። እላችኹማለኹ፥በሰው፡ፊት፡የሚመሰክርልኝ፡ዅሉ፥የሰው፡ልጅ፡ደግሞ፡በእግዚአብሔር፡መላእክት፡ፊት፡ይመሰክርለታል፤ በሰውም፡ፊት፡የሚክደኝ፡በእግዚአብሔር፡መላእክት፡ፊት፡ይካዳል። በሰው፡ልጅም፡ላይ፡ቃል፡የሚናገር፡ዅሉ፡ይሰረይለታል፤መንፈስ፡ቅዱስን፡የሚሰድብ፡ግን፡አይሰረይለትም። ወደ፡ምኵራቦችና፡ወደ፡መኳንንቶችም፡ወደ፡ገዢዎችም፡ሲጐትቷችኹ፥እንዴት፡ወይም፡ምን፡
እንድትመልሱ፡ወይም፡እንድትናገሩ፡አትጨነቁ፤ መንፈስ፡ቅዱስ፡በዚያች፡ሰዓት፡ልትናገሩ፡የሚገ፟ባ፟ችኹን፡ያስተምራችዃልና። ከሕዝቡም፡አንድ፡ሰው፦መምህር፡ሆይ፥ርስቱን፡ከእኔ፡ጋራ፡እንዲካፈል፡ለወንድሜ፡ንገረው፡አለው።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
