መጽሐፈ ግጻዌ
ይህ ቻናል በየእለቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚባሉትን ምስባክና የሚነበቡትን የወንጌል ንባባት የሚያስተላልፍ ነው።
Show more3 342
Subscribers
+1224 hours
+447 days
+14230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 13:1-31፡ "ወበይእቲ ዕለት ወፂኦ ኢየሱስ" - "1፤በዚያን፡ቀን፡ኢየሱስ፡ከቤት፡ወጥቶ፡በባሕር፡አጠገብ፡ተቀመጠ፤ ርሱም፡በታንኳ፡ገብቶ፡እስኪቀመጥ፡ድረስ፡ብዙ፡ሰዎች፡ወደ፡ርሱ፡ተሰበሰቡ፥ሕዝቡም፡ዅሉ፡በወደቡ፡ቆመው፡ነበር። በምሳሌም፡ብዙ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አላቸው፦እንሆ፥ዘሪ፡ሊዘራ፡ወጣ።
4፤ርሱም፡ሲዘራ፡አንዳንዱ፡በመንገድ፡ዳር፡ወደቀ፥ወፎችም፡መጥተው፡በሉት። ሌላውም፡ብዙ፡መሬት፡በሌለበት፡በጭንጫ፡ላይ፡ወደቀ፤ ጥልቅ፡መሬትም፡ስላልነበረው፡ወዲያው፡በቀለ፥ ፀሓይ፡በወጣ፡ጊዜ፡ግን፡ጠወለገ፥ሥርም፡ስላልነበረው፡ደረቀ። ሌላውም፡በሾኽ፡መካከል፡ወደቀ፥ሾኽም፡ወጣና፡ዐነቀው። ሌላውም፡በመልካም፡መሬት፡ወደቀ፤አንዱም፡መቶ፥ አንዱም፡ስድሳ፥አንዱም፡ሠላሳ፡ፍሬ፡ሰጠ። የሚሰማ፡ዦሮ፡ያለው፡ይስማ። ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፦ስለ፡ምን፡በምሳሌ፡ትነግራቸዋለኽ፧አሉት። ርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ለእናንተ፡የመንግሥተ፡ሰማያትን፡ምስጢር፡ማወቅ፡ተሰጥቷችዃል፥ለእነርሱ፡ግን፡አልተሰጣቸውም። ላለው፡ይሰጠዋልና፥ ይበዛለትማል፤ከሌለው፡ግን፡ያው፡ያለው፡እንኳ፡ይወሰድበታል። ስለዚህ፥እያዩ፡ስለማያዩ፥ እየሰሙም፡ስለማይሰሙ፥ስለማያስተውሉም፡በምሳሌ፡እነግራቸዋለኹ። መስማት፡ትሰማላችኹና፡አታስተውሉም፥ማየትም፡ታያላችኹና፡አትመለከቱም። በዐይናቸው፡እንዳያዩ፥በዦሯቸውም፡እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም፡እንዳያስተውሉ፥ተመልሰውም፡
እንዳልፈውሳቸው፥የዚህ፡ሕዝብ፡ልብ፡ደንድኗልና፥ዦሯቸውም፡ደንቍሯል፥ ዐይናቸውንም፡ጨፍነዋል፡የሚል፡
የኢሳይያስ፡ትንቢት፡በእነርሱ፡ይፈጸማል። የእናንተ፡ግን፡ዐይኖቻችኹ፡ስለሚያዩ፡ዦሮዎቻችኹም፡ስለሚሰሙ፡ብፁዓን፡ናቸው። እውነት፡እላችዃለኹ፥ብዙዎች፡ነቢያትና፡ጻድቃን፡የምታዩትን፡ሊያዩ፡ተመኝተው፡አላዩም፥ የምትሰሙትንም፡ሊሰሙ፡ተመኝተው፡አልሰሙም። እንግዲህ፡እናንተ፡የዘሪውን፡ምሳሌ፡ስሙ። የመንግሥትን፡ቃል፡ሰምቶ፡በማያስተውል፡ዅሉ፥ክፉው፡ይመጣል፥በልቡ፡የተዘራውንም፡ይነጥቃል፤በመንገድ፡ዳር፡የተዘራው፡ይህ፡ነው። በጭንጫ፡ላይ፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡ወዲያው፡በደስታ፡የሚቀበለው፡ነው፤ ነገር፡ግን፥ለጊዜው፡ነው፡እንጂ፡በርሱ፡ሥር፡የለውም፥በቃሉ፡ምክንያትም፡መከራ፡ወይም፡ስደት፡
በኾነ፡ጊዜ፡ወዲያው፡ይሰናከላል። በሾኽ፡መካከል፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡የሚሰማ፡ነው፥የዚህም፡ዓለም፡ዐሳብና፡የባለጠግነት፡
መታለል፡ቃሉን፡ያንቃል፥የማያፈራም፡ይኾናል። በመልካም፡መሬት፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡የሚያስተውል፡ነው፤ርሱም፡ፍሬ፡ያፈራል፡
አንዱም፡መቶ፡አንዱም፡ስድሳ፡አንዱም፡ሠላሳ፡ያደርጋል። ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡በዕርሻው፡መልካም፡ዘርን፡የዘራን፡ሰው፡ትመስላለች። ሰዎቹ፡ሲተኙ፡ግን፡ጠላቱ፡መጣና፡በስንዴው፡መካከል፡እንክርዳድን፡ዘርቶ፡ኼደ። ስንዴውም፡በበቀለና፡ባፈራ፡ጊዜ፥እንክርዳዱ፡ደግሞ፡ያን፡ጊዜ፡ታየ፡ የባለቤቱም፡ባሪያዎች፡ቀርበው፦ጌታ፡ሆይ፥ መልካምን፡ዘር፡በዕርሻኽ፡ዘርተኽ፡
አልነበርኽምን፧እንክርዳዱንስ፡ከወዴት፡አገኘ፧አሉት። ርሱም፦ጠላት፡ይህን፡አደረገ፡አላቸው።ባሮቹም፦እንግዲህ፡ኼደን፡ብንለቅመው፡ትወዳለኽን፧አሉት። ርሱ፡ግን፦እንክርዳዱን፡ስትለቅሙ፡ስንዴውን፡ከርሱ፡ጋራ፡እንዳትነቅሉት፡አይኾንም። ተዉአቸው፤ እስከ፡መከር፡ጊዜ፡ዐብረው፡ይደጉ፤በመከር፡ጊዜም፡ዐጫጆችን፦እንክርዳዱን፡አስቀድማችኹ፡ልቀሙ፡በእሳትም፡ለማቃጠል፡በየነዶው፡እሰሩ፥ስንዴውን፡ግን፡በጐተራዬ፡ክተቱ፡እላለኹ፡አለ። ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ሰው፡ወስዶ፡በዕርሻው፡የዘራትን፡የሰናፍጭ፡ቅንጣት፡ትመስላለች።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
👍 1
07/11/2016 ዓ.ም (፯/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
አርውዮ ለትለሚሃ።
ወአሥምሮ ለማዕረራ።
ወበነጠብጣብከ ትበቊል ተፈሢሓ። መዝ. 64፥10
🕯 ትርጉም
ትልሟን ታረካለህ።
ቦይዋንም ታስተካክላለህ።
በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
👍 3
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ዮሐ. 1:1-6 "ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ" - "በመዠመሪያው፡ቃል፡ነበረ፥ቃልም፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ፥ቃልም፡እግዚአብሔር፡ነበረ። ይህ፡በመዠመሪያው፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ። ዅሉ፡በርሱ፡ኾነ፥ከኾነውም፡አንዳች፡ስንኳ፡ያለርሱ፡አልኾነም። በርሱ፡ሕይወት፡ነበረች፥ሕይወትም፡የሰው፡ብርሃን፡ነበረች። ብርሃንም፡በጨለማ፡ይበራል፥ጨለማም፡አላሸነፈውም። ከእግዚአብሔር፡የተላከ፡ስሙ፡ዮሐንስ፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ነበረ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
7/11/2016 ዓ.ም (፯/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልዐ ምድረ።
ወበቃለ እግዚአብሔር ጸንዐ ሰማያት።
ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ፡፡ መዝ 32፡
🕯 ትርጉም
የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።
በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ።
ሰራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 24: 15-36 "ወይእተ ዓሚረ ይበጽሕ ሕልቀት " - "15፤እንግዲህ፡በነቢዩ፡በዳንኤል፡የተባለውን፡የጥፋትን፡ርኵሰት፡በተቀደሰችው፡ስፍራ፡ቆሞ፡ስታዩ፥አንባቢው፡
ያስተውል፥
16፤በዚያን፡ጊዜ፡በይሁዳ፡ያሉት፡ወደ፡ተራራዎች፡ይሽሹ፥
17፤በሰገነትም፡ያለ፡በቤቱ፡ያለውን፡ሊወስድ፡አይውረድ፥
18፤በዕርሻም፡ያለ፡ልብሱን፡ይወስድ፡ዘንድ፡ወደ፡ዃላው፡አይመለስ።
19፤በዚያችም፡ወራት፡ለርጕዞችና፡ለሚያጠቡ፡ወዮላቸው።
20፤ነገር፡ግን፥ሽሽታችኹ፡በክረምት፡ወይም፡በሰንበት፡እንዳይኾን፡ጸልዩ፤
21፤በዚያን፡ጊዜ፡ከዓለም፡መዠመሪያ፡ዠምሮ፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡ያልኾነ፡እንግዲህም፡ከቶ፡የማይኾን፡
ታላቅ፡መከራ፡ይኾናልና።
22፤እነዚያ፡ቀኖችስ፡ባያጥሩ፡ሥጋ፡የለበሰ፡ዅሉ፡ባልዳነም፡ነበር፤ነገር፡ግን፥እነዚያ፡ቀኖች፡
ስለተመረጡት፡ሰዎች፡ያጥራሉ።
23፤በዚያን፡ጊዜ፡ማንም፦እንሆ፥ክርስቶስ፡ከዚህ፡አለ፡ወይም፦ከዚያ፡አለ፡ቢላችኹ፡አትመኑ፤
24፤ሐሰተኛዎች፡ክርስቶሶችና፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያት፡ይነሣሉና፥ቢቻላቸውስ፡የተመረጡትን፡እንኳ፡እስኪያስቱ፡
ድረስ፡ታላላቅ፡ምልክትና፡ድንቅ፡ያሳያሉ።
25፤እንሆ፥አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ።
26፤እንግዲህ፦እንሆ፥በበረሓ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትውጡ፤እንሆ፥በዕልፍኝ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትመኑ፤
27፤መብረቅ፡ከምሥራቅ፡ወጥቶ፡እስከ፡ምዕራብ፡እንደሚታይ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና፤
28፤በድን፡ወዳለበት፡በዚያ፡አሞራዎች፡ይሰበሰባሉ።
29፤ከዚያች፡ወራትም፡መከራ፡በዃላ፡ወዲያው፡ፀሓይ፡ይጨልማል፥ጨረቃም፡ብርሃኗን፡
አትሰጥም፥ከዋክብትም፡ከሰማይ፡ይወድቃሉ፥
30፤የሰማያትም፡ኀይላት፡ይናወጣሉ።በዚያን፡ጊዜም፡የሰው፡ልጅ፡ምልክት፡በሰማይ፡ይታያል፥በዚያን፡
ጊዜም፡የምድር፡ወገኖች፡ዅሉ፡ዋይ፡ዋይ፡ይላሉ፥የሰው፡ልጅንም፡በኀይልና፡በብዙ፡ክብር፡በሰማይ፡ደመና፡
ሲመጣ፡ያዩታል፤
31፤መላእክቱንም፡ከታላቅ፡መለከት፡ድምፅ፡ጋራ፡ይልካቸዋል፥ከሰማያትም፡ዳርቻ፡እስከ፡ዳርቻው፡ከአራቱ፡
ነፋሳት፡ለርሱ፡የተመረጡትን፡ይሰበስባሉ።
32፤ምሳሌውንም፡ከበለስ፡ተማሩ፤ጫፏ፡ሲለሰልስ፡ቅጠሏም፡ሲያቈጠቍጥ፥ያን፡ጊዜ፡በጋ፡እንደ፡ቀረበ፡
ታውቃላችኹ፤
33፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡ይህን፡ዅሉ፡ስታዩ፡በደጅ፡እንደ፡ቀረበ፡ዕወቁ።
34፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡እስኪኾን፡ድረስ፡ይህ፡ትውልድ፡አያልፍም።
35፤ሰማይና፡ምድር፡ያልፋሉ፥ቃሌ፡ግን፡አያልፍም።
36፤ስለዚያች፡ቀንና፡ስለዚያች፡ሰዓት፡ግን፡ከአባት፡ብቻ፡በቀር፡የሰማይ፡መላእክትም፡ቢኾኑ፡ልጅም፡
ቢኾን፡የሚያውቅ፡የለም።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
06/11/2016 ዓ.ም (፭/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
እስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት።
ወለአእይንትየኒ እምአንብዕ።
ወለአገርየኒ እምዳህፅ። መዝ 55፥13
🕯 ትርጉም
ነፍሴን ከሞት እግሮቼን ከመውደቅ አድነኻልና።
በሕያዋን ብርሃን እግዚአብሔርን ደስ አሠኘው ዘንድ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯👍 2👏 1
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.