Amen Charitable Organization አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት
Open in Telegram
~💢አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት#ንግድ ባንክ፦ 1000427953967 በጎነት ለራስ ነው! ~💢 በቴሌብር ለበጎአድራጎት ሚለውን ተጭነው በቀን 1ብር ይለግሱ እናመሰግናለን🙏 ~💢 'no child left behind,every child matters' ~💢 Address : Addis Ababa, Figa mebrat ~💢 አሜን ዳቦና ኬክ አድራሻ: ፊጋ መብራት ~💢 for more info📱0965940498
Show more2 976
Subscribers
No data24 hours
-57 days
+3130 days
Posts Archive
+9
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ከአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመቀናጀት ለቦሌ አጠቃላይ መሰናዶ ትምህርት ቤት ለሚገኙ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል የትምህርት ቁሳቁስ (ደብተር፣ ቦርሳና እስክርቢቶ) ድጋፍ አደረገ፡፡
***
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሴቶችና ህጻናት አገልግሎት የሚውሉ የትምህርት ቁሳቁሶችን በማዘጋጀትና በተጨማሪ ከአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት የተረካባቸውን የደብተር ድጋፍ በዋናነት ሴቶችና ህጻናትን ከትምህርት ገበታቸው እንዳይስተጓጎሉ ለማገዝ የተደረገ ነው ሲሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ የትምህርት ቁሳቁሶቹን ከአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት ተቀብለው ለቦሌ አጠቃላይ መሰናዶ ትምህርት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዜና ስጦታውን ባስረከቡበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ገልፀዋል።
የአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾችም ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር በመተባበር ለትምህርት ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ መሰል ድጋፎችን ማድረጉን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
በስጦታ ርከክቡም ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ ፣ የበጎ ፈቃድ ማጎልበትና ትብብር ስራ አስፈፃሚ አቶ ደጀኔ ጌታቸው እና ሌሎች የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾችና ዋና ሀላፊዎች በተገኙበት ርክክቡ ተፈፅሟል።
ኢትዮ ቴሌኮምን ከልብ እናመሰግናለን
በጎነት ለራስ ነው!
አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት።
መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም
ውድ የአሜን ቤተሰቦች! እና
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ እያልን፤ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
በጎነት ለራስ ነው!
አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት።
+5
#ለነገ_ተስፋዎች
ኢትዮ ቴሌኮም በበጎነት ፕሮግራሙ ለነገ ተስፋዎች በሚል መሪ ሀሳብ በዋና ሥራ አስፈጻሚያ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ባስጀመረው ሀገር አቀፍ የመማሪያ ደብተር ልገሳ መርሐ ግብር መሠረት በድርጅታችን በአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት ከፍተኛ የኢትዮ ቴሌኮም የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ድርጅቱ በማእከሉ ለሚያሳድጋቸው ህፃናትና ከማእከሉ ውጪ ለሚረዳቸው 400 የሚሆኑ ህፃናት ለ2018 አዲስ ዓመት የትምህርት ዘመን ለሚማሩ ተማሪዎች የመማሪያ ደብተር ልገሳ አከናውኗል፡፡
የምንግዜም አጋራችን የሆነው ኢትዮቴሌኮምን ከልብ እናመሰግናለን!!!
መልካም አዲስ ዓመት!
በጎነት ለራስ ነው!!
#በአዲስ_ጅማሮ_በአዲስ_ተስፋ_በአዲስ_ዕይታ
#ኢትዮቴሌኮም#አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት
“የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም።”
— ምሳሌ 10፥22
ውድ የአሜን ቤተሰቦቻችን እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያልን ለሀገራችን እንዲሁም ከመላው ቤተሰቦቻችሁ ጋር መጪው ዘመን ሀዘን የሌለበት የእግዚአብሔር በረከት እንዲያገኛችሁ እንመኛለን!!
ኢትዮጵያ ወደ እግዚአብሔር በረከት የምትገባበት ዓመት እንዲሆን ከልብ ተመኘን።
በጎነት ለራስ ነው!
አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት።
መስከረም 1ቀን 2018ዓ.ም
👆👆👆
ውድ የአሜን የቴሌግራም ቤተሰቦቻችን የቪዲዮ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የቲክቶክ ቻናላችንን ፎሎው በማድረግ የተወደደ ቤተሰብነትዎን ያጠናክሩ!
ስለ ቅን ልብዎ ከልብ እናመሰግናለን።
በጎነት ለራስ ነው!
አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት።
ደረሰ!!
የፈለጉትን እቃ በመግዛትዎ ምክንያት ብቻ
አሜን የሚያሳድጋቸውን ህፃናትን መርዳት የሚችሉበት ቀን ደረሰ!
የ2018 አዲስ አመት የንግድ ኤክስፖ ባዛር
ከነሀሴ 17 - ጷግሜ 5 2017 ዓ.ም
በአ.አ ኤግዚቢሽን ማእከል
አዳራሽ ቁ3 ያገኙናል!
ይምጡ ይጎብኙ
ይግዙና ይርዱ!
በጎነት ለራስ ነው!
አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት።
በኢትዮ ቴሌኮም አዘጋጅነት ከግንቦት 1 -30 በቆየው "ግንቦትን ለአሜን" ካምፔይን ላይ ለተሳተፋችሁ ውድ የአሜን ቤተሰቦች ሁሉ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ! 🙌🙏🙌
ኢትዮ ቴሌኮምን ከልብ እናመሰግናለን!!🙏
በኢትዮ ቴሌኮም አዘጋጅነት ከግንቦት 1 -30 በቆየው "ግንቦትን ለአሜን" ካምፔይን ላይ ለተሳተፋችሁ ውድ የአሜን ቤተሰቦች ሁሉ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ! 🙌🙏🙌
ኢትዮ ቴሌኮምን ከልብ እናመሰግናለን!!🙏
ውድ የተወደዳችሁ የአሜን ቤተሰቦች ግንቦት ሊያልቅ በቀሩት እነዚህ 3ቀናቶች የእጅዎን ስልክ ብቻ በመጠቀም የኢትዮቴሌኮምና ቴሌብር ኦፊሻል ሶሻል ሚዲያዎችን ምንም አይነት ዋጋ ሳያወጡ ፎሎውና ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ ሼር በማድረግ ብቻ የበጎነት አሻራዎን ያሳርፉ!
ፎሎው ሲያደርጉ 30ብር እና በ1 ሼር 10ብር ኢትዮ ቴሌኮም ለአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት ድጋፍ ያደርጋል።
ዘላቂ የጋራ ማህበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ! እናመሰግናለን።
ኢትዮቴሌኮም / ቴሌብር እና / አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት በጋራ
ውድ የተወደዳችሁ የአሜን ቤተሰቦች ግንቦት ሊያልቅ በቀሩት እነዚህ 3ቀናቶች የእጅዎን ስልክ ብቻ በመጠቀም የኢትዮቴሌኮምና ቴሌብር ኦፊሻል ሶሻል ሚዲያዎችን ምንም አይነት ዋጋ ሳያወጡ ፎሎውና ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ ሼር በማድረግ ብቻ የበጎነት አሻራዎን ያሳርፉ!
ፎሎው ሲያደርጉ 30ብር እና በ1 ሼር 10ብር ኢትዮ ቴሌኮም ለአሜን በጎ አድራጎት ድርጅት ድጋፍ ያደርጋል።
ዘላቂ የጋራ ማህበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ! እናመሰግናለን።
#ኢትዮቴሌኮም #ቴሌብር እና #አሜን በጎ አድራጎት ድርጅት በጋራ
Repost from Ethio telecom
ግንቦትን ለአሜን የበጎ አድራጎት ድርጅት!!
በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ Share ልክ 10 ብር ለአሜን የበጎ አድራጎት ድርጅት እንለግሳለን!
🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!
ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ
በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!
🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!
#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
